Ethio Canada Visa

Ethio Canada Visa Canada Visa

በጉጉት ከሚጠበቀው የዓለም ዋንጫ በፊት ለኔይማር ልዩ ፀሎት ተደረገ! 🇧🇷በፊታችን ከሚጀምረው የዓለም ዋንጫ ውድድር አስቀድሞ፣ ለታዋቂው ብራዚላዊ የፊት መስመር ተጫዋች ኔይማር ዳ ሲልቫ ሳንቶ...
29/05/2026

በጉጉት ከሚጠበቀው የዓለም ዋንጫ በፊት ለኔይማር ልዩ ፀሎት ተደረገ! 🇧🇷

በፊታችን ከሚጀምረው የዓለም ዋንጫ ውድድር አስቀድሞ፣ ለታዋቂው ብራዚላዊ የፊት መስመር ተጫዋች ኔይማር ዳ ሲልቫ ሳንቶስ ጁኒየር (Neymar Jr) ልዩ የባርኮት እና የፀሎት ሥነ-ሥርዓት ተደርጎለታል።

ኳስ እና እምነት ሲገናኙ! በርካታ እግርኳስ ተጫዋቾች ከመጫወታቸው በፊትም ሆነ ካሸነፉ በኋላ ፈጣሪያቸውን በሜዳ ላይ ሲያመሰግኑና ክብር ሲሰጡ ማየት የተለመደ ነው።

ይህ "Worshipers on the pitch" የተሰኘው መንፈሳዊ እንቅስቃሴ ስፖርቱ ከሜዳም ባለፈ ጥልቅ መንፈሳዊ ትስስር እንዳለው ያሳያል።

ለንጉሱ ኔይማር እና ለብራዚል ብሄራዊ ቡድን መልካም እድል እንመኛለን! 🏆

⚽️⚽️⚽️

Dylan Page መጥቶ ከሄደ በኋሏ የ ጃኒ እና የአዶናይ የፍቅር ግንኙነት አበቃ ለምን ይመስላችኋል?🤔🤔🤔🙄
29/05/2026

Dylan Page መጥቶ ከሄደ በኋሏ የ ጃኒ እና የአዶናይ የፍቅር ግንኙነት አበቃ ለምን ይመስላችኋል?🤔🤔🤔🙄

03/05/2026

የሆነ ጊዜ ትዝ አለኝ ታክሲ ውስጥ የ 1 ብር ከ 50 መንገድ 2 ብር ከፍለን መውረጃችን ደርሶ 50 ሳንቲም መልስ አትመልስ ከ እረዳቱ ጋር ስንደባደብ
አይ ጊዜ (8አመት በፊት)

የሚሸጥ ፎቶ ኮፒ canon 2022 አሁኑኑ ይደውሉልን 0923214485
20/04/2026

የሚሸጥ ፎቶ ኮፒ canon 2022 አሁኑኑ ይደውሉልን 0923214485

ከየት ሰማህ እንዳትሉኝ ARS 4 -3  MCITY እንኳን ደስ አላችሁ ከ ሀያ አመት በኋላ🥳🥳
19/04/2026

ከየት ሰማህ እንዳትሉኝ ARS 4 -3 MCITY
እንኳን ደስ አላችሁ ከ ሀያ አመት በኋላ🥳🥳

ዛሬ ምሽት ግዮን ሆቴል እንገናኝ ‘’የልቤን’’ ኮንሰርትተወዳጁ መሳይ ተፈራ ለመጀመሪያ ጊዜ በታላቅ የሙዚቃ ኮንሰርት ሊያገኘን ቀጠሮ ይዟል ፣ ወጣቱ ድምፃዊ ልዑል ሲሳይ ሌላኛዉ የኮንሰርቱ ድ...
18/04/2026

ዛሬ ምሽት ግዮን ሆቴል እንገናኝ

‘’የልቤን’’ ኮንሰርት

ተወዳጁ መሳይ ተፈራ ለመጀመሪያ ጊዜ በታላቅ የሙዚቃ ኮንሰርት ሊያገኘን ቀጠሮ ይዟል ፣ ወጣቱ ድምፃዊ ልዑል ሲሳይ ሌላኛዉ የኮንሰርቱ ድምቀት ነዉ

ፍልቅልቋ ማህሌት ወንድሙ ለምሽቱ ሌላ ዉበት ሆና ብቅ ትላለች

በመድረኩ በድንገት ተገኝቶ ስራውን የሚያቀርበው አንጋፋው ድምፃዊ ማን ይሆን?

ትኬቶች በቴሌብር ሽያጭ ላይ ናቸው!

መደበኛ በ1,500 ብር፣ በር ላይ በ1,700 ብር ያገኛሉ።

ቪአይፒ (VIP) 3,000 ብር... ልዩ መስተንግዶ ከእራት እና የኮክቴል መጠጥ ጋር VVIP) በ10,000 ብር ብቻ ተዘጋጅቷል።

16/04/2026

አሁን በኢትዬጰያ ሰአት አቆጣጠር 11:00 ሰአት ሁኗል።
የቴዲ አፍሮ የጀንበር ሙዚቃ የመጨረሻው ቅኔ። የገባው ካለ🤔 (ቴዲን ግን ማንም አይችለውም ቅኔው ላይ)🤭

የቴዲ አፍሮ እና ሰዋሰው መልቲሚዲያ ውል የፈረሰበት ምክንያት ታወቀ!ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ከአራት አመት በፊት ቀጣዩን አልበሙን በሰዋሰው መልቲሚዲያ በኩል ለማሰራጨት እና ለመልቀቅ ...
15/04/2026

የቴዲ አፍሮ እና ሰዋሰው መልቲሚዲያ ውል የፈረሰበት ምክንያት ታወቀ!

ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ከአራት አመት በፊት ቀጣዩን አልበሙን በሰዋሰው መልቲሚዲያ በኩል ለማሰራጨት እና ለመልቀቅ ውል ተፈራርሞ እንደነበር ይታወቃል፡፡ ሆኖም የድምፃዊው አልበም ሊለቀቅ ጥቂት ቀናት ሲቀሩት ይህ የሁለቱ አካላት ውል ፈርሷል፡፡

ውሉ የፈረሰበትን ምክንያት በተመለከተ በርካታ ምክንያቶች ሲነሱ የነበር ሲሆን፤ ሰዋሰው አልበሙ ውስጥ የተካተቱ ሶስት ዘፈኖች እንዲወጡ ጥያቄ በማቅረቡ ውሉ ፈርሷል የሚሉ አሉባልታዎች በስፋት ሲሰራጭ ሰንብቷል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ኢትዮፒካሊንክ በዛሬው ዕለት ምንጮቹን ዋቢ በማደረግ ውሉ የፈረሰበትን እውነተኛ ምክንያት ይዞ ወጥቷል፡፡

እንደ ኢትዮፒካሊንክ ምንጮች የቴዲ እና ሰዋሰው ውል የፈረሰበት አንዱ ምክንያት፣ በድምፃዊው እና በአሳታሚው በኩል ውሉ ውስጥ የተካተቱ አዳዲስ ጉዳዮች ዋነኛ መንስኤ መሆናቸው ይናገራሉ፡፡ በሁለቱ አካላት መካከል በተደጋጋሚ የተደረጉ ውይይቶች የውሉን ባለቤቶች ሳያግባቡ ቀርተዋል የሚለው ኢትዮፒካሊንክ፤ ሰዋሰው መልቲሚዲያ የቴዲ አፍሮ ነባር ሙዚቃዎች ድጋሜ በሰዋሰው ገጽ ላይ እንዲለቀቁ መጠየቃቸው ለውሉ መፍረስ አንድ ምክንያት ነው ብሏል፡፡ ድርጅቱ የድምፃዊውን ነባር ስራዎች በራሱ ገጽ ላይ ለማሰራጨት በየዓመቱ የሚከፈል ከፍተኛ ገንዘብ በቅድመ ሁኔታ መልክ አቅርቧል፡፡ ሆኖም ይህ የድርጅቱ ሀሳብ በቴዲ ዘንድ ውድቅ ተደርጓል፡፡

በተጨማሪም ከአራት ዓመት በፊት በተፈረመው ውል ላይ ከስልክ ድምጽ ማሳመሪያ ጥሪ ላይ የሚገኝ ገቢ ለሰዋሰው እንዲሰጥ የተወሰነው የውል ስምምነት ማሻሻያ እንዲደረግበት በቴዲ አፍሮ በኩል እንደቀረበ አንዳፍታ ሚዲያ ከኢትዮፒካሊን ዘገባ ሰምቷል፡፡ ሆኖም ይህ የቴዲ ሃሳብ ከሰዋሰው በኩል ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል፡፡ እነዚህን ልዮነቶች ባለመጥበባቸው እና እየሰፉ በመሄዳቸው ውሉ ሊፈርስ በቅቷል፡፡

ውሉ በተፈረመበት ወቅት ሰዋሰው ባጠቃላይ ለቴዲ አፍሮ 50 ሚሊዮን ብር ለመክፈል ተስማምቶ ነበር፡፡ በወቅቱም ለድምፃዊው ግማሽ ያህል ማለትም 25 ሚሊዮን ብር ተከፍሎት እንደነበር ከድምፃዊው የማኔጅመንት ክፍል አባላት የተገኘው መረጃ አረጋግጧል፡፡ ነገር ግን ከሁለት ሳምንት በፊት ውሉ በመፍረሱ ድምፃዊው ቀድሞ የተቀበለውን 25 ሚሊዮን ብር ከአራት አመታት ወለድ ጋር ታሳቢ ተደርጎ፤ በድምሩ 33 ሚሊዮን ብር ለሰዋሰው እንደመለሰ ተረጋግጧል፡፡

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው  | ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚ...
15/04/2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

| ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጥምረት ቦርድ ሊቀ መንበር ኃይለማርያም ደሳለኝ ገለጹ።

የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጥምረት የተመሰረተበትን 20ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ የከፍተኛ ባለሙያዎችና የሥራ ኃላፊዎች ውይይት እየተካሄደ ነው።

የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጥምረት (አግራ) የአነስተኛ አርሶ አደሮችን በግብዓትና በቴክኖሎጂ በመደገፍ የግብርና እድገትን ለማሳለጥ እንደ አውሮፓውያኑ ዘመን አቆጣጣር በ2006 የተመሰረተ አፍሪካ መር ተቋም ነው።

ተቋሙ የተሻሻለ የዘር ብዜትን፣ የአፈር ጤናማነትን በማስጠበቅና ለግብርና ምርቶችን የገበያ ዕድል በማመቻቸት ዘርፉን በማዘመን የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ግብ ይዟል።

የኢትዮጵያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትርና የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጥምረት ቦርድ ሊቀ መንበር ኃይለማርያም ደሳለኝ በዚህ ወቅት እንደተናገሩት፤ ግብርና ለአፍሪካ የምግብ ዋስትና እና የኢኮኖሚ ዕድገት ለማረጋገጥ የጀርባ አጥንት ነው።

አግራ ከ20 ዓመት በፊት ሲቋቋም ለአፍሪካ የስርዓተ ምግብ ዕጣ ፋንታ ወሳኝ የሆነውን ግብርና በማዘመን የዜጎችን ምርታማነት ለማሳደግ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።

ግብርና ለአፍሪካ ብልፅግና መሰረት መሆኑን ገልጸው፤ ለስኬታማነቱ የተቋማት ትብብርና ግልፅ የፖሊሲ አተገባበር ያስፈልጋል ብለዋል።

ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የግብርና ኤክስቴንሽን ስርዓት በማጠናከርና ቁርጠኛ አመራር በመስጠት ምርትና ምርታማነትን በማሻሻል የወጭ ንግዷን ማሳደግ መቻሏን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ ምርትና ምርታማነት እየጨመረ መምጣቱን ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች በምሳሌነት የሚጠቀስ ስኬት አስመዝግባለች ብለዋል።

ኢትዮጵያ በሰብል ልማት ብቻ ሳይሆን በእንስሳት ሀብት እና ሌሎች የግብርና ዘርፎች የአርሶ አደሮችን ተሳትፎ በማሳደግ በአህጉሪቷ ተጠቃሽ ለውጥ ማምጣቷን ገልጸዋል።

በአፍሪካ የግብርና ሽግግር በመፍጠር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ዘላቂ እድገትን ለማስፈን ለችግሮች መፍትሔ ማፈላለግ እንደሚገባም ተናግረዋል።

በአፍሪካ የምግብ ስርዓትን ብሔራዊ አጀንዳ ማድረግ ይገባል ያሉት የቦርዱ ሊቀ መንበር፤ አግራ የአፍሪካ ግብርና ሽግግር አቀጣጣይ ሆኖ እያገለገለ ነው ብለዋል።

አርሶ አደሩ ዘላቂ የአሰራር ስርዓት እንደሚፈልግ ገልጸው፤ ለሥርዓቱ ቀጣይነት ያለው የተቋማት ትብብር እንደሚያስፈልግ በአጽንኦት ገልጸዋል።

በአፍሪካ ህብረት የገጠር ልማት ክፍል እና የግብርናና ምግብ ዋስትና ዘርፍ ኃላፊ ጃኔት ኢደሜ (ዶ/ር)፤ህብረቱ የምግብ ስርዓትን አሕጉራዊ አጀንዳ አድርጎ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በአፍሪካ የግብርና ሽግግር ለመፍጠርና የማህበራዊ ዋስትናን ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።

የግብርና ሽግግር የኢኮኖሚ ዕድል ብቻ አይደለም ያሉት ኃላፊዋ፤ የደህንነትና ሉዓላዊነት ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል።

ለዚህ ደግሞ አካታች፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር፣ ጠንካራ ተቋማት መገንባትና የፖሊሲ ማዕቀፍ ማውጣት እንደሚገባ አመልክተዋል።

የአፍሪካን ትርክት በፈጠራና በጥምረት መገንባት እንደሚገባ ገልጸው፤ታሪክ ያለፈ ብቻ ሳይሆን ነገን መገንባት ጭምር መሆኑን ተናግረዋል።

በቀጣይ 20 ዓመታት አርሶ አደሮችን በማጠናከር ግብርናን ለአፍሪካ ዘላቂ ዕድገትና ልማት መጠቀም እንደሚገባ ማብራራታቸዉን ኢዜአ ዘግቧል።

Inbox 🐂👇"ለትንሳኤ በዓል በባህር ዳር አባይ ማዶ ገብርኤል ገበያ፣ የበሬ ዋጋ 115 ሺህ ሲደመር 5 ሺህ ለማረጃ ሆኗል፤ በአጠቃላይ 120 ሺህ ብር  እንዴት አያችሁት?"Via የዋህ ምን ...
11/04/2026

Inbox 🐂👇

"ለትንሳኤ በዓል በባህር ዳር አባይ ማዶ ገብርኤል ገበያ፣

የበሬ ዋጋ 115 ሺህ ሲደመር 5 ሺህ ለማረጃ ሆኗል፤ በአጠቃላይ 120 ሺህ ብር

እንዴት አያችሁት?"

Via የዋህ ምን ይሆናል ከስፍራው

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Canada Visa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio Canada Visa:

Share