24/08/2025
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ስለ ኩርሙክ የወርቅ ፋብሪካ የተናገሩት…
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘውን የኩርሙክ ዘመናዊ የወርቅ ፋብሪካ የግንባታ ሂደት ተመልክተዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጉብኝታቸው በኋላ ስለ ፋብሪካው የተናገሩት…
👉 በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ የወርቅ ፋብሪካ ይሆናል፤
👉 ከሚቀጥለው ዓመት አጋማሽ በኋላ ወደ ምርት እንደሚገባ ይጠበቃል፤
👉 በዚህ አካባቢ የሚመረተው ወርቅ በዓመት እስከ 1 ቢሊየን ዶላር ገቢ ያስገኛል፤
👉 ከ20 ኪሎ ሜትር ራዲየስ በላይ ቦታ ይዟል፤
👉 ሦስት ግድቦች እና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የሚኖሩበት የመኖሪያ ካምፕ የያዘ ነው፤
👉 በዘርፉ ለኢትዮጵያ የእውቀት ሽግግር ያመጣ ፋብሪካ ነው፤
👉 ፋብሪካው የተገነባው ያለንን ሀብት በአግባቡ ለመጠቀም ባለን ፍላጎት መሰረት ነው፤
👉 በሁሉም ዘርፎች የተሟላ ልማት ለማረጋገጥ መሰረት የሚጥል ስራ ነው፤ Via Ministry of Mines - Ethiopia