Atse Minilik II

Atse Minilik II We believe in Ethiopian God

20/04/2025

𝕙𝕒𝕡𝕡𝕪 𝕖𝕥𝕙𝕚𝕠𝕡𝕚𝕒𝕟 𝕖𝕒𝕤𝕥𝕖𝕣 !!!

17/08/2024
16/08/2024
የጥቁር ህዝብ አባትእመዬ ሚኒሊክ ‼
01/03/2023

የጥቁር ህዝብ አባት
እመዬ ሚኒሊክ ‼

14/10/2021

ሁሉም ኢትዮጵያዊ ኘሮፋይሉን ጥቁር ምስል በማድረግ ወለጋ ለተጨፈጨፋ ንፁሃን ሀዘናችንን እየገለፅን መንግስት ደግሞ የዜጎችን ህይወት ይታደግ ዘንድ ተዕፅኖ እንፍጠር። እስከ መቼ ወለጋ የወንበዴ መፈንጫ ይሁን። ምንም ማያውቁ ንፁህ ዜጎች እንዴት ይታረዳሉ። እውን መንግስት ቅን ልብ ካለው መተከል ላይ የተገበረውን መፍትሄ ወለጋ ላይ ማይተገብረው።
ያሳዝናል። ልብ ይሰብራል። ነው የዜጎች ሞት ከስንዴ አረም አነሰ። ግን እስከ መቼ።
There is a solution ‼
we need a solution ‼
No more Genocide ‼
መንግስት አቅም አለው። የአንድ ዜጋ ህይወት ዋጋ ሊኖረው ይገባል። ግፍ ነው። አርሶ የሚያበላን ምስኪን ገበሬ ከታረደ የት ላይ ነው የመንግስት በምግብ ራስን መቻል። ቅዠት ላይ ነን። መማራችን የት ላይ ነው። ሀገራት በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ እየተፎካከሩ ባሉበት ጊዜ እኛ ወደ ኋላ ከእንስሳት የአዕምሮ እድገት በታች እየተምዘገዘግን ነው። እንስሳት እርስ በእርሳቸው በሚተዛዘኑበት በዚህ ጊዜ እኛ ሰው በሚመስሉ ጭራቅ እና ዝንጀሮ ፍጥረቶች እንታረዳለን። ወለጋን ማረጋጋት እና ህግን ማስከበር የሚቻልበት ብዙ መንገድ እያለ የመንግስት ዳተኝነት አይገባኝም።
ይበቃል መንግስት አስቸኳይ መፍትሄ እንዲወስድ ሁሉም ዜጋ ሊጠይቅ ይገባል።ሰፊ ሀገር ይዘን መጥበብ ይብቃ።
ይበቃል‼
Enough‼

14/10/2021

ወለጋ የሚገኙ አማራ ወገኖቻችን በኦሮሚያ መንግስት እና በኦነግ አሸባሪ ቡድን ከበባ ውስጥ ገብተው መውጫ አጥተዋል። የአማራ ክልል መንግስት ችልተኝነት ሊገባኝ አልቻለም። ሚኒሻ እና ልዩ ሀይሉ ገብቶ ሊታደጋቸው ይገባል።

በንፁሀን ህይወት የሚቀልድ ባለስልጣን ኦሮሚያ ክልል ላይ ተቀምጧል። ያሳዝናል። ኢግዚአብሔር ይፈርዳል። ወንበራችሁ እሾክ ሁኖ ይውጋችሁ። አንደበታችሁ ይዘጋ። አሸባሪ ቡድን አቅሙ እዚህ ግባ የማይባል ግን ሆን ተብሎ አማራ ወለጋ ላይ ከበባ ውስጥ በማስገባት የማጽዳት ስራ እየተሰራ ነው። ብልጽግና የገባኸውን ቃል ተወጣ። ቃል ከገባህ ሳምንት አልሆነህም። ስልጣን የማይፈልጉ ሰርቶ አደር ገበሬ መጨፍጨፍ ግፍ ነው።

ኢግዚአብሔር ደግ ቀን አምጣ ‼

በከተማዋ አምስቱም በሮች በሦስት ቢሊዮን ብር የመገበያያ ማዕከላትና መጋዘኖች እንደሚገነቡ ተጠቆመ ***************(ኢ ፕ ድ) በአዲስ አበባ የሚስተዋለውን የዋጋ ንረት ለማቃለል እና ...
06/08/2021

በከተማዋ አምስቱም በሮች በሦስት ቢሊዮን ብር የመገበያያ ማዕከላትና መጋዘኖች እንደሚገነቡ ተጠቆመ
***************
(ኢ ፕ ድ)
በአዲስ አበባ የሚስተዋለውን የዋጋ ንረት ለማቃለል እና የሸማቾችን ጥቅምና ፍላጎት ያማከሉ ግዙፍ የመገበያያ እና የማከማቻ መጋዘኖች በከተማዋ አምስቱም የመግቢያና መውጫ በሮች እንደሚገነቡ የአዲስ አበባ ህብረት ሥራ ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሲሳይ አረጋ አስታወቁ።

አቶ ሲሳይ በተለይም ለአዲስ ዘመን እንደገለፁት፤ የፌደራል ህብረት ሥራ ኤጀንሲ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ እና በአዲስ አበባ ህብረት ሥራ ኤጀንሲ በጋራና በተጠና ጥናት በአምስት ዋና ዋና የአዲስ አበባ መግቢያና መውጫዎች ላይ ዘላቂ የሆኑ ትልልቅ የገበያ ማእከላትና መጋዘኖች ለመገንባት ታቅዷል።

ግንባታዎቹ ዓመቱን ሙሉ ያለማቋረጥ አገልግሎት የሚሰጡ የገበያ ማዕከላት መገንባት አለባቸው ተብሎ ታምኖ አምራቹ ያመረተውን ምርት በፈለገው ጊዜ አምጥቶ አስመዝግቦ የሚያስገባበትና መሸጥ በሚፈልግበት ጊዜ የሚሸጥበት የከተማው ማህበረሰብም በፈለገ ጊዜ መገብየት አለባቸው ተብሎ የገበያ ማዕከላት ግንባታ የቦታ ርክክብ እየተከናወነ ነው።

በዋናነት በጥናት የተለዩት ሦስት ችግሮች አሉ፤ አንደኛው የመጋዘን ችግር ሁለተኛው የፋይናንስ ችግር ሶስተኛው የምርት እጥረት ናቸው ያሉት አቶ ሲሳይ፣ ችግሮቹን ለመፍታት ሰፊ ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑን አመልክተዋል። የምርት እጥረት እንዳያጋጥም ከክልል አምራች ዩኒዮኖች እና ከፌደራል ህብረት ሥራ ኤጀንሲ ጋር ተደጋጋሚ የምክክር መድረኮች መካሄዳቸውን ገልጸዋል።
https://www.press.et/ama/?p=52949

ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችን ‼
ዩቲዩብ 👇
https://youtube.com/channel/UCoH2CVwWn9suWP7q0u2L7MA
ቴሌግራም 👇
https://t.me/ethpress
ትዊተር 👇
https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ 👇
https://www.press.et/

Featured በከተማዋ አምስቱም በሮች በሦስት ቢሊዮን ብር የመገበያያ ማዕከላትና መጋዘኖች እንደሚገነቡ ተጠቆመ — August 5, 2021 comments off አዲስ አበባ፡- በአዲስ አበባ የሚስተዋለውን የዋጋ ንረት ለ...

06/08/2021

መከላከያ ሚኒስቴር ህብረተሰቡ ከሀሰት የፕሮፓጋንዳ መረጃዎች እንዲጠበቅ ጥሪ አቀረበ

መከላከያ ሚኒስቴር ህብረተሰቡ በሀሰት ከሚሰራጩ የፕሮፓጋንዳ መረጃዎች ሊጠበቅ እንደሚገባ አስታወቀ።
የሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮሎኔል ጌትነት አዳነ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ኢትዮጵያን ለማዳን እየተደረገ ያለው የህልውና ዘመቻ ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል ።

አሸባሪው የህወሓት ቡድን በሚነዛው የሀሰት ፕሮፓጋንዳ ምክንያት ህብረተሰቡ መረበሽ እንደሌለበት ተናግረዋል ።
አያይዘውም በሙጃና ድልብ አካባቢ ሰርገው የገቡ የሽብር ቡድኑ ሀይሎችን የመከላከል ስራም እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

ህብረተሰቡ ከትክክለኛ የመንግስት አካል ብቻ ምንጩን አረጋግጦ መረጃ መከታተል አለበትም ነው ያሉት ።
በተከዜ ወንዝ በጣለው በራሱ አስክሬን መንግስት ላይ የፕሮፓጋንዳ ጫና ለመፍጠር መሞከሩ ቡድኑ ያደገበት የማደናገር አካሄድ አካል ነው ብለዋል ።

በተኩስ አቁም ላይ የሚገኘው የመከላከያ ሰራዊት በመከላከል ወሳኝ ተልዕኮ ላይም እንደሚገኝም አስረድተዋል።

የሽብር ቡድኑ በምዕራብ ግንባርና በአፋር በኩል ሰብአዊና ቁሳዊ ከፍተኛ ኪሳራ እንደደረሰበትም ነው የገለጹት ።
ህዝቡም ኢትዮጵያን ለማዳን እያደረገ ያለውን ሁሉን አቀፍ ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል ።/fbc/

06/08/2021

እንደ አድዋ ድል እንታገል

የዛሬው  የግንባር ዉሎና ድል  እነሆ ‼ከወታደራዊ ሃይሉ ጋር መረጃ በመለዋወጥ ተወጥረን ነው የዋልነው። አሁን በተለያዩ ቦታዎች ተደራጅቶ የነበረው ጦር ተደቁሶ በመበታተን ያልተደራጀ፣ መላው ...
05/08/2021

የዛሬው የግንባር ዉሎና ድል እነሆ ‼

ከወታደራዊ ሃይሉ ጋር መረጃ በመለዋወጥ ተወጥረን ነው የዋልነው። አሁን በተለያዩ ቦታዎች ተደራጅቶ የነበረው ጦር ተደቁሶ በመበታተን ያልተደራጀ፣ መላው የጠፋው እና ተስፋ የቆረጠ ሆኗል።

ነገር ግን ሲበተንም የተለያዩ ስትራቴጂካዊ ቦታዎችን መጠጊያ አድርጎ ብቻ መቅረቱን መካድ የለብንም። አሁን ነው መጠንቀቅ። ምክንያቱም ተስፋ ቆርጧል። በመቄት መስመር በብ/ጄ/ተፈራ ማሞ እና በብ/ጄ አዳምነህ መንግስቴ የሚመራው ልዩ ሃይል፣ በጣም የተለየ የሚባል እና የሚያስጨበጭብ የመከላከያ ኋይል እንዲሁም ሚሊሻው እንዳይተርፍ አድርገው እንደ ሰርግ ቤት ጌሾ በትብብር ወቅጠውት አሁን ወደ ማልናገረው አቅጣጫ እየተጓዘ ሲሆን ያም ጥቆማ ሰጥተን ዝግጅቱ አልቋል።

ልዩ ኮማንዶዎችም ወደ ፊት የምንገልጸው ታሪክ ሰርተዋል።
እውነታውንም መናገር ግድ ስለሚልና አሳሳቢነቱም ከፍ ያለ ስለሆነ ከወደ ተለያዩ ቦታዎች የተጨናገፈው ሃይል ከአይናችን ብሌን በላይ ከምንሳሳለት እና እንኳን ከባድ መሳሪያ ጡርንባም ሊጮኽበት የማይገባው ቅርሳችን ላሊበላ ከተማ ላይ አይዟችሁ የእናንተ ነን የሚል ማደናገሪያ ለህዝቡ በመስጠት ዘይት ወይራ ተራራ ላይ ስለተንጠለጠለ በጥንቃቄ መመታት ይኖርበታል።

ራያ ቆቦ ላይ ሸዎች ማርያም ማዘዣውን አድርጎ ወደ ተኩለሽ መስመር የሚፈነጨው ርዝራዡ ጦር መሄጃው እና የሃይል ሚዛኑ እንዲሁም በተለያዩ አቅጣጫዎች የዘረጋው የሸረሪት ድር ተበጣጥሶበት እስትንፋሱም ሊበጠስ ደርሷል።

ጥይት በደስታ አናባክን ፣ የዋግ ጀግና ሚሊሾች ጀግንነት ሳያጡ ጠላትን ሲደቁሱ ውለው በጥይት እጦት ምን እንደሆኑ የማንረሳው የቅርብ ጊዜ ሁናቴ ነው።

ደስታችን ሙሉ የሚሆነው ከእኛ መሬት ወጥቶ ውጊያውን በራሱ ምድር ስናደርግ ነው።

አትርሱ ባለ ከዘራው የአሁኑ ኮሎኔል የወደፊቱ ጀኔራል ሻምበል በየነ የተለየ ገድል እየፈጸመ ነው ወደፊት እንገልጸዋለን ብያችኋለሁ ።

ከዚህ ቀደም 24ኛ እና 25ኛ ክፍለጦሮችን በእርሱ በሚመራው 23ኛ ክፍለጦር በአግበ በኩል የነበረውን አጥር እየፈነቀለ አበርገሌ ሲያደርሳቸው " ፈንቅል" የሚባል ስም ለክፍለ ጦሯ ተሰጥቷታል። ፈንቅልነቱን በአፋርም አስመስክሮ አፍ አስጭኖ አሁንም በሌላ ወደፊት በሚገለጽ የጦር አውድ በኩል መፈንቀሉን ቀጥሏል።

ከዚያ ክፍለ ጦር እሳት የላሱ የእኔ ጓደኞችም አሉበትና ኩራቴን ድርብርብ ያደርገዋል።

ደስታችን ሙሉ ሲሆን፣ መሬት ላይ መውረድ የጀመረው ስትራቴጂያችን ተከውኖ ሲያበቃ የደስታ ዶሴየን ይዤ እመለሳለሁ።

ብዙ ብልም ከዚህ በላይ ማለቱን ለጊዜው ልተወውና ጁንታው ከአይናችን ብሌን፣ ከላሊበላ ላይ እንዲወጣ ከፍተኛ ጥንቃቄ ይደረግ‼ ይሄን አምኜበት፣ አውጥቼ አውርጄ ነው የጻፍኩት። እጄን ይዘህ ይሄን ጻፍ፣ ይሄን አትጻፍ ለምትለኝ ከእኔ ገጽ በብሎክ አሰናብትሃለሁ። የጁንታ እስትንፋሱ አጭር፣ የእኛም ደስታ ዘላቂ እንደሚሆን አልጠራጠርም። አለቀ ይሄው ነው‼

ክብር አሁንም የሚሸሸውን ትተን በጀግንነት ለቆመው ለመከላከያ፣ ለልዩ ሃይላችን፣ ለሚሊሻችን እና ወያኔን አላፈናፍን ላለው አጠቃላይ ለወሎ ህዝብ ሲሆን በተለይ ዛሬ ገድላቸው ከፍ ላለው ለጮሬ ሰዶማ፣ ለጎብየ፣ ለሃራ፣ ለላስቴ ገራዶ፣ ለወርቄ፣ ለላስታ፣ ለየጁ፣ ለመቄት እና ለራያ ይሁንልን‼

ቸር እንገናኝ፣ ቸር ያሰማን‼
©ተዋጊዉ Mengesha ከስፍራዉ

Address

Addis Ababa
2116

Telephone

+251913727344

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Atse Minilik II posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share