Amaz Advert and Media

Amaz Advert and Media We write true Updated International News more usefully Ethiopia country people's.

ዶ/ር  .➡ ዶ/ር አለማየሁ ዋሴ ይባላል.  #የእመጓ፣  #የዝጎራና  #መርበብት መፃሕፍት ደራሲ ነው። የሚኖረውን የሚያስተምር ብርቱ ሰው ነው።1. በሚሰራበት መስሪያቤት  ተብሎ በቦርድ የተወ...
29/04/2020

ዶ/ር .

➡ ዶ/ር አለማየሁ ዋሴ ይባላል. #የእመጓ፣ #የዝጎራና #መርበብት መፃሕፍት ደራሲ ነው። የሚኖረውን የሚያስተምር ብርቱ ሰው ነው።

1. በሚሰራበት መስሪያቤት ተብሎ በቦርድ የተወሰነለትን ደመወዝ አልቀበልም ብሎ በደብዳቤ መልሷል።

2. ከአንድ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ውስጥ ለስራ ተወዳድሮ ካለፈ በኋላ፣ ደመወዙ ስለበዛ ቅጥሩን ሰርዞ ያውቃል(80,000 ብር)።

3. ከወር የቤትና የራሱ ወጪ ውጪ ያለውን የባንክ ገንዘቡን በየወሩ ለነዳያንና ለገዳማት ይሰጣል።

4. ዶ/ር አለማየዉ ዋሴ እመጓ መፀሀፍን መጀመሪያ ያሳተመዉ በቤተሰብ ወጪ ነበር

5. እመጓ የታተመበትን ዋና ብሩ ከመለሰ በኃላ ጠቅላላ ትርፉን መፅሀፉ ላይ ለተጠቁሱት project ሰጥቷል ዶ/ር አለማየዉ ዋሴ

⭕ የዶክተር አለማየሁ መርህ ምን መሰላችሁ? የራሱንና የቤተሰቡን ኑሮ ስታንዳርድ አበጅቷል።

"ቤት አለኝ" ይልህና፤ "የቤቴን አይነት ግን አትጠይቁኝ" ይልሀል።

"መኪና አለኝ" ይልህና፣ "የመኪናዬን አይነት ግን አትጠይቁኝ" ይልሃል።

"የምኖረው ከተማ ነው" ይልህና፣ "የት ከተማ ግን እንዳትለኝ" ይልሀል።
ምክንያቱም ይላል "ከቤት በላይ ቤት፣ ከመኪና በላይ መኪና፣ ከከተማ በላይ ከተማ አለ፤ ከቀበቶ በላይ እንኳን ቀበቶ አለ፣ የቀበቶ ስራው ግን ሱሪ እንዳይወልቅ ማድረግ ነው።" ይላል...

በአጠቃላይ ዶክተር አለማየሁ ምኞትን በጥልቅ ጉድጓድ ቆፍሮ የቀበረ፣ የገንዘብን አቅም ያሰነሰ ምርጥ ሰው ነው። ሲናገር እና ሲያስተምር ደግሞ አዝናኝ ነው። የፃፋቸው አስደማሚ መፃሕፍት የሱን ህይወት ቁልጭ አድርገው ያሳያሉ።

   #ተነስቷልየክርስቶስ ትንሳኤ ከሞት በኋላ ሕይወት፣ ከመቃብር ባሻገር ትንሳኤ ከሀዘን ማግሥት ደስታ እንዳለ፤ ስለዚህም በተሥፋ እንድንኖር አብነት ሆኖናል።የሰው ዘር በሙሉ አሁን ያለንበት ...
19/04/2020

#ተነስቷል

የክርስቶስ ትንሳኤ ከሞት በኋላ ሕይወት፣ ከመቃብር ባሻገር ትንሳኤ ከሀዘን ማግሥት ደስታ እንዳለ፤ ስለዚህም በተሥፋ እንድንኖር አብነት ሆኖናል።

የሰው ዘር በሙሉ አሁን ያለንበት በደዌ ዳኛ፣ በአልጋ ቁራኛ የመያዝ፣ በፍርሐትም በር ዘግቶ የመቀመጥ ጊዜ አክትሞ ወደቀደመ ሠላማዊ ሕይወት እንድንመለስ አምላካችን መዓቱን በምህረት ቁጣውንም በትእግስት ይመልስልን።

እንኳን ለጌታችን እና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ ትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ።

 #ኢትዮጵያ ሚያዝያ 9-2012 ዓ.ም
17/04/2020

#ኢትዮጵያ ሚያዝያ 9-2012 ዓ.ም

 #ዓድዋ124  124ኛው የዓድዋ የድል በዓል በአዲስ አበባ ዳግማዊ ሚኒልክ አደባባይ በደማቅ ስነ-ስርዓት በመከበር ላይ ነው። በአዲስ አበባ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ከየአቅጣጫው መፈክሮ...
02/03/2020

#ዓድዋ124

124ኛው የዓድዋ የድል በዓል በአዲስ አበባ ዳግማዊ ሚኒልክ አደባባይ በደማቅ ስነ-ስርዓት በመከበር ላይ ነው። በአዲስ አበባ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ከየአቅጣጫው መፈክሮችን በማንገብ፣ ጋሻና ጦር በመያዝ እንዲሁም ነጋሪት እየጎሰሙ ወደ ዳግማዊ ሚኒልክ አደባባይ አቅንተዋል።

በማለዳው ከሜክሲኮ አደባባይና ለገሃር አቅጣጫ ወደ ሚኒልክ አደባባይ በሚወስዱ ሁሉም አቅጣጫዎች በርካታ ወጣቶች እና የበዓሉ ታዳሚዎች ወደ ቦታው አቅንተዋል።

በጠዋቱ በሰዎች የተሞላው የዳግማዊ ሚኒሊክ አደባባይ ወጣቶቹ የተለያዩ መፈክሮችን፣ ጋሻና ጦር አንግበው፣ ነጋሪት እየጎሰሙ የዳግማዊ ሚኒልክና የእቴጌ ጣይቱን ምስል የያዙ ቲሸረቶችን ለብሰው በፉከራና ሽለላ በአሉን እያከበሩ ነው።

በጉዞው ወቅት በርካታ ወጣቶች፤ የአባትና እናት አርበኞችን ታሪክ ለማሰብ በሚል በባዶ እግራቸው ሲጓዙ ነበር። የወቅቱን የአርበኞች ታሪካዊ ኩነት ለማስታወስም በአህዮች ስንቅ ጭነው ወደ ሚኒልክ አደባባይ በማምራት በዓሉን በልዩ ሁኔታ እያከበሩት ነው። በዓሉ እየተከበረ ባለበት ዳግማዊ ሚኒልክ አደባባይ በርካታ ታዋቂ ሰዎች፣ አርበኞች፣ ወጣቶችና የተለያዩ የመንግስት ሃላፊዎች እንዲሁም የከተማዋ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ

  5-6-2012 .በአረቡ ዓለም በተለያዩ የሥራ መስኮች ተሠማርተው ለሚኖሩ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች የአምልኮ መፈጸሚያ ቤተክርስቲያን ለማነጽ ላለፉት ሠላሳ ዓመታት ጥያቄ ሲያቀርቡ ቢኖሩም እስ...
14/02/2020

5-6-2012

.
በአረቡ ዓለም በተለያዩ የሥራ መስኮች ተሠማርተው ለሚኖሩ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች የአምልኮ መፈጸሚያ ቤተክርስቲያን ለማነጽ ላለፉት ሠላሳ ዓመታት ጥያቄ ሲያቀርቡ ቢኖሩም እስካሁን ሳይሳካ ቆይቷል።

ሰሞኑን ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐብይ ወደኤሜሬት ባቀኑበት ወቅት ይህንኑ የምእመናን የዘመናት ጥያቄ በመፍታት በአረቡ ዓለም ቤተክርስቲያኒቱ ሕንጻ መሥሪያ ቦታ እንድታገኝ አድርገዋል።

ጠቅላይ ሚንስትር ለቤተክርስቲያኒቱ የግንባታ ቦታ በማስፈቀድዎ እያመሠገንን በነካ እጅዎ እንደ ሀገር መቆም ከጀመርንበት ጊዜ አንስቶ ታሪኳን፣ ቅርስዋን እና ነጻነቷን አስጠብቃ ባቆየቻት ሀገር መቆሚያ መቀመጫ የከለከሏትን የሀገር ውስጥ "ጉልበተኞች" መንግስትዎ አደብ ያስገዛቸዋል ብለን ተሥፋ እናደርጋለን።

ሁል ጊዜ እንደምንለው በጅምላ መውቀስም ሆነ ጠቅልሎ ማመስገንም ተገቢ አይደለም። በምክንያት መውቀስ በምክንያት ማመስገን አስተዋይነት ነው።

ጠቅላይ ሚንስትሩን ጨምሮ አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎን እና መላውን የኤምባሲውን ሠራተኞች ትውልድ ስለሚዘክረው በጎ ተግባራችሁ ...

እ ና መ ሠ ግ ና ለ ን !

 #ጠ/ሚ_ዐቢይ በዱባይ ከኢትዮጵያውያን ጋር የሚያደርጉት ውይይት ሀገሪቱ በቀጠናው የምትከተለውን የስራ ስምሪት አቅጣጫ ለመወሰን ይረዳል-አምባሳደር ሱሌይማን አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2012...
13/02/2020

#ጠ/ሚ_ዐቢይ በዱባይ ከኢትዮጵያውያን ጋር የሚያደርጉት ውይይት ሀገሪቱ በቀጠናው የምትከተለውን የስራ ስምሪት አቅጣጫ ለመወሰን ይረዳል-አምባሳደር ሱሌይማን

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በዱባይ ከኢትዮጵያውያን ጋር የሚያደርጉት ውይይት በቀጣይ ኢትዮጵያ በመካከለኛው ምስራቅ የምትከተለውን የስራ ስምሪት አቅጣጫ ለመወሰን እንደሚረዳ በተባበሩት ዓረብ ኢሚሬቶች የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ ተናገሩ።

በዛሬው እለት የተባበሩት ዓረብ ኢሚሬቶች አቡ ዳቢ የገቡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ፥ በቆይታቸውም በሀገሪቱ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን መብት እና ጥቅም የሚያስከብሩ ውይይቶችን እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

አምባሳደር ሱሌይማን ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በስልክ ባደረጉት ቆይታ፥ በዛሬው እለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አቡዳቢ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል የተደረገላቸው መሆኑን ተናግረዋል።

በነገው እለት በዱባይ ስታዲየም ታላቅ መድረክ ይካሄዳል ያሉት አምባሳደሩ፥ በመድረኩ ላይም ቁጥራቸው እስከ 15 ሺህ የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን እንደሚሳተፉ ይጠበቃል።

መድረኩ በርካታ ኢትዮጵያውያን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጋር ፊት ለፊት የመገናኘት እድል የሚፈጥርላቸው መሆኑን አምባሳደር ሱሌይማን ተናግረዋል።

በማግስቱ ቅዳሜ ሴቶች ብቻ የሚሳተፉበት መድረክ እንደሚካሄድም ጠቅሰዋል።

በሪያድ የስልጤ ማህብረሰብ የስራ አመራር ቦርድ አባል እና በሪያድ የህዳሴ ግድብ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል አቶ ኑሪ ኢስማኤል፥ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የዱባይ ጉብኝት ካለው ጠቀሜታ አንጻር ደስታን እንደፈጠረባቸው ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቅርቡ በደቡብ አፍሪካ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጋር ውይይት አድርገው የተለያዩ ውሳኔዎችን ማስቀመጣቸው ይታወሳል።

  ቫይረስ -19በአማራ ክልል የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚያስችል ዝግጅት እየተካሄደ መሆኑን የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል።የኢንስቲትዩቱ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች መ...
13/02/2020

ቫይረስ

-19

በአማራ ክልል የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚያስችል ዝግጅት እየተካሄደ መሆኑን የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል።

የኢንስቲትዩቱ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክተር አቶ አሸናፊ አያሌው ከተናገሩት፦

- የኮሮና ቫይረስ ወደ ክልሉ እንዳይገባ ቀድሞ መከላከል የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ነው።

- የመከላከል ተግባሩን በውጤታማነት ለመምራትም ባለድርሻ አካላትን ያካተተ ክልላዊ ግብረሃይልና የቴክኒክ ኮሚቴ ተቋቁሞ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ተጀምሯል።

- ከተደረጉት ዝግጅቶች መካከል በባህርዳር፣ ጎንደር፣ ላሊበላና ኮምቦልቻ አውሮፕላን ማረፊያዎች የምርመራና ልኬታ ስራዎችን ለማካሄድ የሚያስችል ስራ ተከናውኗል።

- በኢንዱስትሪ ፓርኮችን ጨምሮ በ39 የልማት ፕሮጀክቶች አጠራጣሪ ምልክት የሚታይባቸውን ሰዎች ተለይተው የሚቆይባቸውን ካምፖች ተዘጋጅተው ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነዋል።

- የምርምራ ስራውን የሚያካሄዱ ባለሙያዎችን በመመልመል የማሰልጠን ፣ ቁሳቀስ የማቅረብና የማቆያ ቦታዎችን የመለየት ስራ እየተካሄደ ይገኛል።

- በኢንስቲትዩቱ ስር የሚገኘው የወረርሽኝ ማስተባበሪያ ማዕከል አስፈላጊውን ግብዓት ተሟልቶለት ስራውን እንዲጀምር ተደርጓል።

  ::ከደቂቃዎች በኃላ በታገቱት እህቶቻችን ዙሪያ  ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር አብይ አህመድ  መግለጫ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡የታጋቹቹ ቤተሰቦች አዲስ አበባ ገብተዋል… ከጠቅላይ ሚንስትሩ ጋር...
29/01/2020



::

ከደቂቃዎች በኃላ በታገቱት እህቶቻችን ዙሪያ ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር አብይ አህመድ መግለጫ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የታጋቹቹ ቤተሰቦች አዲስ አበባ ገብተዋል… ከጠቅላይ ሚንስትሩ ጋር እንደሚገናኙም ተነግሯል፡፡

ታጋች ተማሪዎች ከቤተሰቦቻቸው እና ከወገኖቻቸው ጋር ይቀላቀላሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

 #2 ቀን የፈጀው የቻይና  #ሆስፒታል.እኛስ የት ነን???
29/01/2020

#2 ቀን የፈጀው የቻይና #ሆስፒታል.
እኛስ የት ነን???

 19/5/2020
28/01/2020


19/5/2020

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amaz Advert and Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share