ጎህ ሲቀድ-Goh Siked

ጎህ ሲቀድ-Goh Siked ለህሊናህ መኖር ስትጀምር ለስምህ መጨነቅ ታቆማለ!

አዋሽ ባንክ ከዚህ በታች በተገለፀው ክፍት የሥራ መደብ ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡የሥራ መደብ-              ጥበቃ ሰራተኛየትምህርት ደረጃ-         8ኛ ክፍል...
21/06/2023

አዋሽ ባንክ ከዚህ በታች በተገለፀው ክፍት የሥራ መደብ ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡

የሥራ መደብ- ጥበቃ ሰራተኛ

የትምህርት ደረጃ- 8ኛ ክፍል ያጠናቀቀ

ስራ ልምድ- በወታደርነት ሙያ ስልጠና የወሰደ ሆኖ ቢያንስ ሁለት ዓመት አገልግሎት ያለው

እድሜ- ከ 20 – 40 ዓመት ቢሆን ይመረጣል

የስራ ቦታ- አዲስ አበባ

ደመወዝ- በባንኩ እስኬል መሰረት

ማሳበቢያ፤ አመልካቾች በእጅ የተጻፈ ማመልከቻችሁን እና ከላይ ከተገለፁት ማስረጃዎች በተጨማሪ ስርዝ ድልዝ የሌለበት የ8ኛ የሚኒስትሪ ሰርተፍኬት ኮፒ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
በዚሁ መሰረት ከላይ የተገለጸውን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለሰባት ተከታታይ ቀናት የማስረጃችሁን የማይመለስ ፎቶ ኮፒ በሚከተለው አድራሻ በመላክ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

አዋሽ ባንክ
ዲፒዩቲ ቺፍ – ሂውማን ካፒታል ማኔጅመንት ኦፊሰር ኦፊስ
የፖ.ሳ.ቁ 12638
አዲስ አበባ
ማስታወቂያ የሚያበቃበት ቀን ፡- ሰኔ 19 ቀን 2015 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ባንኮች ተወዳዳሪነታቸውን ለማሳደግ የበለጠ እንዲዘጋጁ ብሔራዊ ባንክ አሳሰበየኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዢ አቶ ሰለሞን ደስታ የኢትዮጵያ ባንኮች በቴክኖሎጂ ፣ ፋይናንስ አቅም...
16/06/2023

የኢትዮጵያ ባንኮች ተወዳዳሪነታቸውን ለማሳደግ የበለጠ እንዲዘጋጁ ብሔራዊ ባንክ አሳሰበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዢ አቶ ሰለሞን ደስታ የኢትዮጵያ ባንኮች በቴክኖሎጂ ፣ ፋይናንስ አቅም እና ሰው ሀይል የበለጠ እንዲዘጋጁም ጥሪ አቅርበዋል።
ለበለጠ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችንን Join አድርጉ https://t.me/Gohsiked

የልጆች የቁጠባ ሳጥን ተጠቃሚ ይሁኑ!.አዋሽ ባንክ በዓይነቱ ልዩ የሆነ የልጆች የቁጠባ ሳጥን ተጠቃሚ እንዲሆኑ በሁሉም ቅርንጫፎቹ አቅርቦሎታል፡፡ለልጆችዎ የቁጠባ ሂሳብ ከፍተው የቁጠባ ሳጥን ...
16/06/2023

የልጆች የቁጠባ ሳጥን ተጠቃሚ ይሁኑ!.
አዋሽ ባንክ በዓይነቱ ልዩ የሆነ የልጆች የቁጠባ ሳጥን ተጠቃሚ እንዲሆኑ በሁሉም ቅርንጫፎቹ አቅርቦሎታል፡፡
ለልጆችዎ የቁጠባ ሂሳብ ከፍተው የቁጠባ ሳጥን በመውሰድ እየጨመረ የሚሄድ የወለድ ምጣኔ ተጠቃሚ ይሁኑ!
https://t.me/Gohsiked

ብሔራዊ ባንክ ከአንድ ባንክ በስተቀር  ሌሎች ባንኮች የጥሬ ገንዘብ  እጥረት እንደሌለባቸው አስታወቀ የፋይናንስ ዘርፉ  አቅርቦቱና ፍላጎቱ የተመጣጠነ እንዳልሆነም ተጠቁሟልከአንድ ባንክ በስተ...
16/06/2023

ብሔራዊ ባንክ ከአንድ ባንክ በስተቀር ሌሎች ባንኮች የጥሬ ገንዘብ እጥረት እንደሌለባቸው አስታወቀ የፋይናንስ ዘርፉ አቅርቦቱና ፍላጎቱ የተመጣጠነ እንዳልሆነም ተጠቁሟል

ከአንድ ባንክ በስተቀር ሌሎች ሁሉም የንግድ ባንኮች የጥሬ ገንዘብ እጥረት (ሊኪዩዲቲ) እንደሌለባቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዢ አቶ ሰለሞን ደስታ አስታወቁ።

ምክትል ገዥው ዛሬ ለስድስተኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ስካይላይት ሆቴል እየተከናወነ ባለው የምስራቅ አፍሪካ የፋይናንስ ስብሰባ(Summit”) እንደገለጹት፣ “የገንዘብ እጥረት አለ ከተባለም ሁለት ወይም አንድ ባንክ ላይ ነው” ብለዋል።

አቶ ሰለሞን የጥሬ ገንዘብ እጥረት እንዳለበት የጠቆሙትና ስሙን ለመጥቀስ ያልፈለጉት ባንክ ግን ማኔጅመንቱ ላይ ማስተካከያ የሚፈልግ መሆኑን ተናግረዋል።

ምክትል ገዢው ምንም እንኳን የጥሬ ገንዘብ እጥረት እንደሌለ ቢናገሩም ፣ አገሪቱ ከብዙ ነገር እንደመውጣቷ፣ ብዙ የገንዘብ ፍላጎት አለ። https://t.me/Gohsiked

07/06/2023
በእናቷ ማህጸን ሁለተኛ ልጇን ያረገዘችው አውስትራሊያዊትየ30 አመቷ ክሪስቲ ብሪያንት የመጀመሪያ ልጇን ስትወልድ ማህጸኗ በመጎዳቱ በቀዶ ህክምና የእናቷን ማህጸን ወስዳለች             ...
06/06/2023

በእናቷ ማህጸን ሁለተኛ ልጇን ያረገዘችው አውስትራሊያዊት
የ30 አመቷ ክሪስቲ ብሪያንት የመጀመሪያ ልጇን ስትወልድ ማህጸኗ በመጎዳቱ በቀዶ ህክምና የእናቷን ማህጸን ወስዳለች በቀዶ ህክምና የአንዱን ማሕጸን ወደ ሌላ ማዛወር በፈረንጆቹ 2012 መጀመሩ ይታወሳል

በቀዶ ህክምና የእናቷን ማህጸን ያገኘችው አውስትራሊያዊት በተወለደችበት ማህጸን ሁለተኛ ልጇን ማርገዟ ገልጻለች።

ክሪስቲ ብሪያንት የተባለችው የኒው ሳውዝ ዌልስ ነዋሪ በ2021 ነበር የመጀመሪያ ልጇን በድንገት ስትወልድ በማህጸኗ ላይ ጉዳት የደረሰባት።

ጉዳቱ ክሪስቲ እና ባለቤቷ ኒክ ሁለተኛ ልጅ ማግኘት እንዳይችሉ የሚያደርግ ነበር።

እናም ክሪስቲ ለእናቷ ፈራ ተባ እያለች አንድ ጥያቄ ተንሳለች፤ ማህጸንሽን ስጭኝ የሚል።

እናት ሚሼልም ክሪስቲን ዘጠኝ ወር ተንከባክቦ ያቆየውን ማሕጸናቸውን ለልጅ ልጃቸው መወለጃ ይሆን ዘንድ ለመስጠት ምንም አልሰሰቱም።

በጥር ወር 2023ም በሲድኒ ሮያል ሆስፒታል 15 ስአት በወሰደ ቀዶ ህክምና የእናት ሚሼል ማሕጸን ወደ ልጅ ክሪስቲ ተዘዋወረ።

ከሰሞኑም ክሪስቲ ከእናቷ ባገኘችው ማሕጸን የሰባት ሳምንት ጽንስ መያዟን አብስራ ቤተሰቡ በደስታ ተሞልቷል።

በጆርዳን የ42 አመቱ ጎልማሳ "ነፍሰ ጡር" ሆኖ ተገኘ
“በድጋሚ ጽንስ መያዝ በመቻሌ ደስታዬ ወደር የለውም፤ እናቴም ውድ ስጦታ ስለሰጠችኝ አመሰግናለሁ” ማለቷንም ዴይሊሜል ዘግቧል።

ክሪስቲ ከእናቷ በተሰጣት ማህጸን የያዘችው ጽንስ ከፍተኛ ክትትል እየተደረገለት ሲሆን፥ በያዝነው የፈረንጆቹ አመት መጨረሻ ሁለተኛ ልጇን እንደምትገላገል ይጠበቃል።

የ30 አመቷ አውስትራሊያዊት በቀጣይም ሶስተኛ እና አራተኛ ልጆችን ለመውለድ ፍላጎት እንዳላት ገልጻለች።

በቀዶ ህክምና የአንዱን ማሕጸን ወደ ሌላ ማዛወር የተጀመረው በፈረንጆቹ 2012 ነበር።

እስካሁንም 90 የተሳካ የማህጸን ዝውውር ቀዶ ህክምና የተደረገ ሲሆን፥ 50 ህጻናትም በዚሁ ዘዴ ተወልደዋል።

06/06/2023

የነዳጅ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል።

የሰኔ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት እንደሚቀጥል ተገልጿል።

የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከግንቦት 29 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ በግንቦት ወር ሲሸጥ በነበረው ዋጋ እንደሚቀጥል የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አሳውቋል።

06/06/2023

የኬንያው ኤንሲቢኤ ባንክ ኢትዮጵያ ውስጥ በዲጂታል ባንክ አገልግሎት ዘርፍ ለመሠማራት ከሳፋሪኮም ኩባንያ ጋር ንግግር መጀመሩን ደይሊ ኔሽን ዘግቧል።

ባንኩ ከኢትዮጵያ ባንኮች ጋር ጥምረት መፍጠርን ሌላ አማራጭ አድርጎ እንደያዘው መናገሩን ዘገባው ጠቅሷል። ባንኩ እና ሳፋሪኮም ኬንያ ውስጥ "ኤም-ሸዋሪ" የተሰኘ በሞባይል የገንዘብ ብድር መስጫ ዘዴ ላይ ላለፉት 10 ዓመታት በጋራ በመስራት ላይ ናቸው።

ኤንሲቢኤ ባንክ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ፣ በዲጂታል ባንክ አገልግሎት ለመሠማራት በዲሞክራሲያዊት ኮንጎና ጋና ላይ ቀልቡን ጥሏል።

በሩዋንዳ የዘር ማጥፋት ተጠርጣሪው በደቡብ አፍሪካ ተያዘእ.አ.አ በ1994 በሩዋንዳ በነበረው የዘር ማጥፋት እልቂት፣ ከጥቃት ለማምለጥ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተሸሸጉ ኹለት ሺሕ ቱትሲዎች እ...
26/05/2023

በሩዋንዳ የዘር ማጥፋት ተጠርጣሪው በደቡብ አፍሪካ ተያዘ

እ.አ.አ በ1994 በሩዋንዳ በነበረው የዘር ማጥፋት እልቂት፣ ከጥቃት ለማምለጥ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተሸሸጉ ኹለት ሺሕ ቱትሲዎች እንዲገደሉ ትዕዛዝ አስተላልፏል፤ በሚል የተጠረጠረው ግለሰብ፣ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ መያዙን፣ የሩዋንዳውን የዘር ማጥፋት የሚከታተለው፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጦር ወንጀል ችሎት አስታውቋል።

የቀድሞው የፖሊስ አባል፣ ፉልጌንሴ ካይሼማ፣ ፍ/ቤቱ በይፋ ክሥ ከመሠረተበት ካለፉት 22 ዓመታት ጀምሮ በሽሽት ላይ ነበር።

በተመድ የተቋቋመው ችሎት፣ ሥራውን ለሩዋንዳ በማስረከቡ፣ ካይሼማ፥ ለሩዋንዳ ተላልፎ እንደሚሰጥ፣ የሮይተርስ ዘገባ አመልክቷል።

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ካይሼማ ያለበትን ለሚጠቁም፣ የአምስት ሚሊዮን ዶላር ጉርሻ እንደሚሰጥ አስታውቆ ነበር።

ሌላው የዘር ማጥፋቱ ጠንሳሽ የተባለው ፌሊሲን ካቡጋ፣ ከ26 ዓመታት ሽሽት በኋላ፣ ከሦስት ዓመት በፊት፣ በፈረንሳይ ውስጥ መያዙ ይታወቃል።

እ.አ.አ በ1994 በሩዋንዳ፣ በአክራሪ ሁቱዎች በተፈጸመ የዘር ማጥፋት፣ 800ሺሕ የሚኾኑ ቱትሲዎች መገደላቸው
ለተጨማሪ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ https://t.me/Gohsiked

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሐረርጌ ገለምሶ ከተማ ሰሞኑን የተሰማው ወሬ ትንሽ አግራሞትን የሚያጭር ነው።ምሽት በጨለማ በመጓዝ የምናውቀው ጅብ በቀትር ከተማይቱ ውስጥ ወደ ሚገኝ አንድ የግል ክሊኒ...
26/05/2023

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሐረርጌ ገለምሶ ከተማ ሰሞኑን የተሰማው ወሬ ትንሽ አግራሞትን የሚያጭር ነው።
ምሽት በጨለማ በመጓዝ የምናውቀው ጅብ በቀትር ከተማይቱ ውስጥ ወደ ሚገኝ አንድ የግል ክሊኒክ ሰተት ብሎ መግባቱ ተሰምቷል።
በገለምሶ ከተማ በሚገኘው ሚልኪ ክሊኒክ የሕክምና ባለሙያ የሆነው አዱኛ አባይነህ፣ የሆነውን እንዲህ በማለት ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ አስረድተዋል።
“ጠዋት ወደ አራት ሰዓት አካባቢ ይሆናል። የክሊኒካችን በር ክፍት ነው። እኛም ገና ሥራ አልጀመርንም ነበር። ጅቡ በቀጥታ በተከፈተው በር ገብቶ ወደ ላብራቶሪ ክፍል አመራ።”
የክሊኒኩ ነርስ የሆነው አዱኛ፣ ሰዎች ጅቡን ሲያዩ ተደናግጠው ለመደብደብ ዱላ ማንሳታቸውን ይናገራል።
የክሊኒኩ ባለቤት ግን ሰዎች ጅቡን እንዳይመቱ ተከላከሉ።
“ወደ አምስት ሰዓት አካባቢ የክሊኒኩ ቅጥር ግቢ በሰው ሞልቶ ነበር። በዚህ ጊዜ በአካባቢው የሚገኙ የትራፊክ ፖሊሶችን ጠርተን ሕዝቡ እንዲረጋጋ አደረግን።”

ጅቡ ግን ላብራቶሪ ክፍል ከገባ በኋላ ጭንቅላቱን አቀርቅሮ እንደተኛ ነበር ይላል አዱኛ።
ሁኔታው የታመመ እንጂ ጉዳት ለማድረስ የመጣ አይመስልም ነበር።
“ጅቡ ታሞ እንደሆነ ጠረጠርን። ከዚያም የእንስሳት ሐኪም ጋር ደወልን። እርሱም የፀረ እብድ ውሻ በሽታ (አንቲ ሬቢስ) መርፌ ስጠው አለኝ። ከዚያም በኋላ መድኃኒት ቤት ሄጄ ገዝቼ ቀስ ብዬ በመርፌ ወጋሁት” ይላል ነርስ አዱኛ።
ነርስ አዱኛ ለጅቡ መርፌውን ለመውጋት ባሰበ ጊዜ ለደኅንነቱ ሰግቶ ነበር። ነገር ግን ጅቡ በጣም ተዳክሞ ለመንቀሳቀስ በማይችልበት ሁኔታ ስለነበረ ሲወጋ ምንም አይነት እንቅስቃሴ አላደረገም ብሏል።
ቢሆንም ግን ለደኅንነቱ የሰጋው ነርስ ጅቡ ተኝቶበት ከነበረው ስፍራ አቅራቢያ የነበረውን ማቀዝቀዣ በከለላነት ተጠቅሞ ነበር መርፌውን የወጋው።
በክሊኒኩ ውስጥ ለአንድ ሰዓት ያህል የቆየው ጅብ መርፌውን ከተወጋ ከ20 ደቂቃ በኋላ ተነስቶ መውጣቱን አዱኛ ይናገራል።
“ጅቡ የታመመ ስለሚመስል እኛ አንድ ባዶ ክፍል ልናስገባው ነበር። ነገር ግን እንዳሰብነው አልሆነም። ልክ መርፌውን ከወጋነው ከደቂቃዎች በኋላ ከተኛበት ቦታ ተነስቶ ወጥቶ ሄደ።” በግል ክሊኒክ መርፌ የተወጋው ጅብ ዳግም አለመመለሱን የህክምና ባለሙያው ያስረዳሉ።
ክሊኒኩ ጅቡ ያረፈበትን የላብራቶሪ ክፍል በሚገባ ካጸዱ በኋላ ወደ ቀድሞ ሥራው ተመልሷል።
እንዲህ ዓይነት አጋጣሚ በአካባቢው የተለመደ አለመሆኑን እና የአካባቢው ነዋሪዎች መደነቃቸውን የህክምና ባለሙያው አቶ አዱኛ ይናገራሉ።
በሐረር ከተማ ለማዳ ጅቦችን ሥጋ መመገብ የተለመደ እና የቱሪስት መስህብ መሆኑ ይታወቃል።

ለአዲስ አበቤዎች ለ70 ዓመት ዳቦ ያቀረቡት የ'ሸዋ ዳቦ' መሥራቹ ዘሙይ ተክሉ አርፈዋል።የአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች ሥያሜውን የተዋሱት የሸዋ ዳቦ መሥራቹ አቶ ዘሙይ ተክሉ ከዚህ ዓለም...
25/05/2023

ለአዲስ አበቤዎች ለ70 ዓመት ዳቦ ያቀረቡት የ'ሸዋ ዳቦ' መሥራቹ ዘሙይ ተክሉ አርፈዋል።

የአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች ሥያሜውን የተዋሱት የሸዋ ዳቦ መሥራቹ አቶ ዘሙይ ተክሉ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ታውቋል።
የኤርትራ መሠረት ያላቸው ዘሙይ ወደ አዲስ አበባ ዘልቀው ያቋቋሙት ሸዋ ዳቦ ለ70 ዓመታት ለአዲስ አበቤዎች ዳቦ ሲያቀርብ የቆየ ነው።
አቶ ዘሙይ አምስት ልጆችን ያፈሩ ሲሆን፣ አንደኛዋ ልጃቸው በአዲስ አበባ ሥማቸው ከሚጠራ ኬክ ቤቶች መካከል የሆነው የ'ቢሎስ ኬክ' ባለቤት ናት።
በደርግ አገዛዝ ዘመን ለኤርትራ መገንጠል የሚዋጉ አማጽያንን በመደገፍ ታስረው የነበሩት ዘሙይ ተክሉ፣ በከተማዋ የሌላኛው ሥመ ጥር ኬክ ቤት መሥራች የበላይ ተክሉ ወንድም ነበሩ።
ለአዲስ አበቤዎች ለ70 ዓመት ዳቦ ያቀረቡት የ'ሸዋ ዳቦ' መሥራቹ ዘሙይ ተክሉ አርፈዋል።
የቴሌ ግራም ቻናላችን ለመቀላቀል https://t.me/Gohsiked

ንስርን የሚገዳደር ብቸኛው የወፍ ዝርያ ቁራ ነው። ቁራ በንስሩ ጀርባ ላይ ይቀመጥና አንገቱን ይነክሰዋል። ንስሩ ምላሽ አይሰጥም ፣ ከቁራ ጋር አይጣላም ፣ ከቁራ ጋር አይታገልም ፣ በቁራ ላይ...
25/05/2023

ንስርን የሚገዳደር ብቸኛው የወፍ ዝርያ ቁራ ነው።
ቁራ በንስሩ ጀርባ ላይ ይቀመጥና አንገቱን ይነክሰዋል። ንስሩ ምላሽ አይሰጥም ፣ ከቁራ ጋር አይጣላም ፣ ከቁራ ጋር አይታገልም ፣ በቁራ ላይ ጊዜና ጉልበቱን አያጠፋም ይልቁንም ክንፉን ዘርግቶ ወደ ሰማይ ከፍ በማለት መብረር ይጀምራል።
በረራው ከፍ ባለ መጠን ቁራው ለመተንፈስ ይቸገራል። በመጨረሻም ቁራው በኦክሲጅን እጥረት ምክንያት ይወድቃል።

ዛሬ በህይወታችሁ የሚገዳደራችሁን ምንም አይነት ነገር አትታገሉት ፣ ጉልበታችሁን እና ጊዜአችሁን በእርሱ ላይ አታጥፉ ይልቁንም ከፍ ባለ አስተሳሰብ በልጣችሁ ውጡ ፣ በእውቀት ጠንክሩ ፣ መልካም ሥራችሁን ጨምሩ።

ንስሩ በጀርባው ላይ የተንጠለጠለውን ቁራ ትቶ ከፍታው ላይ እንደሚያተኩር የሌሎችን አሉባልታ ፣ ሀሜት ፣ ማስፈራሪያ ወደታች ትታችሁ ከፍታችሁ ላይ አተኩሩ።

ቁራው ከፍታውን መቋቋም እንዳቃተው እናንተም ከነገሮች በላይ ከፍ ስትሉ የእናንተም ተግዳሮት ከፍታውን መቋቋም አቅቶት ቁልቁል ይፈጠፈጣል ።

የከፍታ ዘመን ይሁንላችሁ
BA

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጎህ ሲቀድ-Goh Siked posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share