02/10/2023
በሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ የቢዝነስ ተሞክሯቸው ጥግ የደረሱትን ምሁራን እና ባለሀብቶች አሰባስቦ አባመላ የንግድ ሥራ አማካሪ ተመሠረተልዎ!
ዓላማው በቢዝነስ ልምድ የሌላቸውን ወጣት ሥራ ፈጣሪዎች ፈጠራቸው ትርፋማ እና በአመርቂ ሁኔታ ውጤታማ እስከሚሆን ድረስ ማነሳሳት፣ ማስጀመር፣ እንዲሁም በስኬት ጎዳና እስከሚንደረደሩበት ጊዜ ያለውን መንገድ አብሮ መጓዝ የሆነ፤ በቢዝነስ ላይ ያሉትን ማነቃቃት፣ ከሀገር አቀፍና አለም ዓቀፍ ተቋማት እና ባለሀብቶች ጋር ማስተሳሰር፣ የቢዝነስ አመራር ክህሎቶቻቸውን በመጨመር እና በማዘመን ድርጅቶቻቸውን በትርፋማነት እና በዘላቂነት እንዲመሩ ማስቻል፣ ንግዶቻቸውን ዘመናዊ እንዲያደጉ መርዳት እና ሌሎችም የሆነ ነው። ተግባራችን ወቅቱን የጠበቀ እና በጥቂት ዓላማዎች ያልታጠረ ነው። ሂደታችንን ስንቀጥል ምርጡን እንደምታጭዱ በመገመት ተሰባስበናል፤ ተቀላቀሉን!