09/12/2023
ስለ ሄፓታይተስ ምን ያዉቃሉ?
ሄፓታይተስ( የጉበት መቆጣት)በበርካታ ቫይረሶች (ሄፓታይተስ ቫይረስ) ፣ ኬሚካሎች ፣ መድኃኒቶች ፣ አልኮል ፣ እንዲሁም በአንዳንድ የጄኔቲክ በሽታዎች ወይም ከመጠን በላይ ንቁ በሆነ የበሽታ መከላከል ስርዓት ጉበትን በስህተት በመጠቃት(Autoimmune) ምክንያት ይከሰታል።
የጉበት ጉዳትን የሚያስከትሉ አምስት ዋና ዋና ቫይረሶች አሉ፡- ሄፓታይተስ ኤ ፣ ቢ ፣ ሲ ፣ ዲ እና ኢ።
ሄፓታይተስ ኤ ባብዛኛው በምግብ ወለድ በሽታ ሲሆን በተበከለ ውሃ እና ንጽህናውን ባልጠበቀ ምግብ ሊተላለፍ ይችላል። በተለይም በልጆች ላይ ለመከሰት በጣም ቀላል ነው፣ ነገር ግን ጉበት ላይ ከባድ ጉዳት የማድረስ እድሉ አነስተኛ ሲሆን ዘላቂ ችግር አያስከትልም።
ሄፓታይተስ ቢ በተበከለ ደም፣ መርፌ፣ ወይም የሰውነት ፈሳሽ በመጋለጥ እና ከእናት ወደ ልጅ ሊተላለፍ ይችላል። ሥር የሰደደ በሽታ ሲሆን በአንዳንድ ሁኔታዎች ቫይረሱን ከተሸከሙ ከብዙ ዓመታት በኋላ ለረጅም ጊዜ የሚቆይ የጉበት ጉዳት፣ የጉበት ካንሰር እና ሲሮሲስ ሊያስከትል ይችላል።
ሄፓታይተስ ሲ በተበከለ ደም ወይም ከእናት ወደ አራስ ልጅ በወሊድ ጊዜ ብቻ ይተላለፋል። እንዲሁም ለረጅም ጊዜ ሂደት ወደ ጉበት ካንሰር እና ለሲሮሲስ ይዳርጋል።
ሄፓታይተስ ዲ በሄፐታይተስ ቢ በተያዙ ሰዎች ላይ ተቆራኝቶ ብቻ ይከሰታል።
ኢንፌክሽኑን ለመከላከል ልጆች ወይም ቀደም ሲል ያልተከተቡ ሰዎች የሄፐታይተስ ቢ እና ሄፐታይተስ ኤ ክትባት መከተብ አለባቸው። የሄፐታይተስ ሲ, ዲ እና ኢ ምንም ዓይነት ክትባቶች የሉም። ከላይ የተጠቀሱትን የመተላለፊያ መንገዶች በመገንዘብ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል።
በ9806 ይደውሉ
ስለማንኛውም በሽታ ከመማከር ባሻገር ወደ ትክክለኛው የህክምና ተቋምና ባለሙያ እንመራለን።
ፈዉስ ዲጂታል ሜዲካልሶሉሽንስ
ስለጤናዎ እናስባለን !