06/09/2018
ዕብራውያን 10:17 ብሎ ከተናገረ በኃላ ኃጥአታቸውንና ዓመፃቸውንም ደግሜ አላስብም ይላል::
ስለ እንናተ ባላውቅም ነገር ግን ዕብራውያን 10:17 መልካም ዜና ነው
ስለዚህ እግዚአብሔርን እያለ ያለው የትላንትና የዛሬ እንዲሁም ለወደፊት የምትሰሩትን ሀጥያት ደግሜ አላስበውም ነው :: ደግሜ አላስበው የሚለው ቃል በግሪኩ እጥፍ አሉታዊ double negative ነገርን ያመለክታል :: በሌላ ቋንቋ እግዚአብሔር የእናንተን ሀጥያት አያስታውሰውም ::
ታዲያ እግዚአብሔር ራሱን ዝቅ አድርጎ እንዳይመስላችሁ እርሱ ቅዱስ እና ትክክል ነው ::እርሱ ሀጥያትን የሚያስታውሰው ከ 2000 ዓ.ም በፊት በመስቀል ላይ ነው :: ስለዚህ የትኛውም የሰራነው ወይንም የምንሰራው ሀጥያት በክርስቶስ አካል በመስቀል ተከፍሏል አሜን:: ስለዚህ እኛ ላይ የሚያስበው ሀጥያት
የለውም ከዚህ የተነሳ የሀጥያትን አስተሳሰብ አስወግዷቸው:: ሁልግዜ ሀጥያት ስንሰራ
እግዚአብሔር አንድ ነገር እንድናስታውስ ይፍልጋል ;እርሱም ጌታ እየሱስ ሆይ
አሁን ለሰራሁት ሀጥያት አንተ ላይ ተፈርዶብሀል ስለዚህ እግዚአብሔር እኔ ላይ አይፍርድብኝም
እንደውም እንተ ስለ እኔ ተኮንነካል ስለዚህ እግዚአብሔር እኔን አይኮንነኝም ::
መስቀሉን መመልከት ካልቻላችሁ በሀጥያት እሳቤና እግዚአብሔር የሚፍርድባችሁ ወይም የሚኮንናችሁ እየመስላችሁ እንዲው ፍርድን በመጠባበቅ ለሰይጣን እድል ፍንታን ትሰጡታላችሁ ምክንያቱም እግዚአብሔር ከሰራችሁት ሀጥያት የተነሳ ከእናንተ ጋር የተጣላ ይመስላችሀል::
ስለዚህ ሀጥያታችሁ ይቅር እንደተባለ ልታውቁት ና ልታምኑ ወደዚህም መርዳት ልትገቡ ያስፍልጋችሀል ::
ምንም ሀጥያት የለም እናንተን ከእግዚአብሔር በረከት የሚያስቀራችሁ እንዲሁም ምንም ሀጥያት
የለም እናንተን ወደ ገሀነም የሚከታችሁ እናንተ ለዘለዓለም ይቅር ተብላችኃል::
ዕብራውያን 10:12,14 እርሱ ግን ስለ ኃጥአት አንዴ መሰዋት ለዘላለም አቅርቦ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ .......14,አንድ ግዜ በማቅረብ የሚቀደሱትን ለዘለዓለም ፍፁማን አድርጎቸዋልና::
እኔ እና እናንተ ለዘለዓለም ፍፁማን ተደርገናል:: ፍፁም በሆነው በመስቀል ስራ በእግዚአብሔር ፍፁማን ተደርገናል :: ስለዚህ የተወደዳችሁ እግዚአብሔር እያላችሁ ያለው ምህረት አድርጌላችኃል :: ኃጥአታችሁንና አመፃችሁን ለዘለዓለም ደግሜ አላስበውም :: አሜን