ጽንዓ Media

ጽንዓ Media Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ጽንዓ Media, Business service, Bole, Addis Ababa.

ጽንዓ ትዩብ | Tsinia Tube ኦርቶዶክሳዊ የቪድዮ ትምህርቶች፣ መዝሙራት፣ ምክረ አበው፣ ብሒለ አበው፣ ወቅታዊ የቤተክርስቲያን መረጃዎች፣ ሃይማኖታዊ ጥቅሶችና አባባሎች እንዲሁም ትምህርታዊ የቀጥታ ሥርጭቶች የሚቀርቡበት መድረክ ነው። ማንኛውንም ኦርቶዶክስ ተዋሕዶን የተመለከተ ቁም ነገር ሲፈልጉ የመጀመሪያ መድረሻዎን ጽንዓ ቲዩብ | ጽንዓ Tube ቢያደርጉ ይጠቀማሉ።

03/06/2026

ሰዓሊ እና ገጣሚ ቸርነት 💔💔💔💔💔🖤🖤🖤🖤 ባለቤት የሌለው ሀገር..........💔 ምስራቅ አርሲ 💔

"እባካችሁ ድምፅ ሁኑን!" ሌላው ኦርቶዶክሳዊም የሞት ቀኑን እየጠበቀ ነወ🖤🖤 — ከምስራቅ አርሲ ጫካዎች የተሰማ የድረሱልን ጥሪ! መላው አገር በምርጫው ትኩረት በተጠመደበት በዚህ ወቅት፣ በም...
03/06/2026

"እባካችሁ ድምፅ ሁኑን!" ሌላው ኦርቶዶክሳዊም የሞት ቀኑን እየጠበቀ ነወ🖤🖤 — ከምስራቅ አርሲ ጫካዎች የተሰማ የድረሱልን ጥሪ!

መላው አገር በምርጫው ትኩረት በተጠመደበት በዚህ ወቅት፣ በምስራቅ አርሲ አሰኮ ወረዳ በንጹሐን ኦርቶዶክሳውያን ላይ ዘግናኝ ጥቃት እየተፈጸመ ይገኛል።

ከ37 በላይ ንጹሐን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል።
234 መኖሪያ ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተቃጥለዋል።

ታሪካዊው የጠላታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል እና የኩፍቴና መድኃኔዓለም አብያተ ክርስቲያናት ወድመዋል።

ጥቃቱ አሁንም በተለያዩ ቀበሌዎች (ዘዲቡ፣ እሬቻ ሚካኤል፣ ሱንቴ ማርያም...) የቀጠለ ሲሆን፣ አቅመ-ቢስ እናቶችና ሕፃናት ሕይወታቸውን ለማዳን ንብረታቸውን ጥለው በጫካዎች ውስጥ ተደብቀው ይገኛሉ።

የቀሩት በሕይወት እንዲተርፉ የንጹሐንን ድምፅ ለዓለም እናሰማ!

👉 ይህ መረጃ ለሁሉም እንዲደርስ በማድረግ የተጎጂዎች መጠጊያ እና ድምፅ እንሁን! 🙏

ነፍስ ይማር!

🌹🍇2️⃣1️⃣ ቅድስት ድንግል ማርያም 2️⃣1️⃣🍇🌹           የሰማያዊቷ ንግሥት መገለጥ በደብረ ምጥማቅግንቦት ፳፩ ቀን የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመናን ልባቸው በደስታ የሚሞላበት፣ የሰማ...
29/05/2026

🌹🍇2️⃣1️⃣ ቅድስት ድንግል ማርያም 2️⃣1️⃣🍇🌹

የሰማያዊቷ ንግሥት መገለጥ በደብረ ምጥማቅ

ግንቦት ፳፩ ቀን የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመናን ልባቸው በደስታ የሚሞላበት፣ የሰማይና የምድር ንግሥት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በግብጽ ምድር በደብረ ምጥማቅ ያደረገችውን ድንቅ ተአምርና መገለጥ የሚያስቡበት ታላቅ ዕለት ነው፡፡

የታሪኩ ምስጢራዊ ውበት

ድንግል ማርያም ከልጇ ከወዳጇ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጋር በስደት ዘመኗ ያረፈችበት ሰላማዊው የደብረ ምጥማቅ ገዳም፣ የብርሃን መጋረጃ ተጋርዶለት ሰማያዊ ከተማ ሆነ።

ለ፳፭ ቀናት ያህል በተከታታይ በግርማ መለኮት ስትገለጥ፣ ምድር በሰማያውያን መላእክት፣ በብርሃን ፈረሶች ላይ በተቀመጡ ሰማዕታትና በጻድቃን ተሞላች።

ሱራፌል ማዕጠንታቸውን ይዘው እያጠኑላት፡ «አብ በሰማይ አይቶ እንዳንቺ ያለ አላገኘም፤ ባንቺም ሰው ሆነ» እያሉ በውበት አመሰገኗት። በሄሮድስ የተጨፈጨፉት ንጹሐን ሕፃናትም በፈገግታ እያሸበሸቡ በፊቷ ተጫወቱ።

የበረከትና የፍቅር ማዕድ
ይህ መገለጥ የሃይማኖትና የዘር ልዩነት ሳይኖር ክርስቲያኑን፣ እስላሙንና አረማውያኑን በአንድነት ያስደሰተ፣ የቅድስት ድንግል ማርያም ፍቅር ሰማያዊ ሰላምን ያደለበት ነበር።

እናትና አባታቸውን ያጡ የናፈቋቸውን በሕያው ገጽ አሳየቻቸው፤ ምእመናን መሀረባቸውን ወደ ሰማይ ሲወረውሩ በቅድስት እጇ እየተቀበለች ባረከችላቸው።

ታላቁ ሊቅ አባ ጽጌ ድንግል በማኅሌተ ጽጌ ድርሰቱ የዚህን ታላቅ ምስጢር ውበት እንዲህ ሲል ይገልጸዋል፡

«በቀን የታየው የፍቅርሽ አበባ ይቅርና፣ ሌሊት በሕልሙ ያየሽ ሰው ምስጉን ነው!»

የቅዱሳን ናፍቆትና የልብ መሻት

እንደ አፄ ዘርዓ ያዕቆብ ያሉ ቅዱሳን ነገሥታትና አባቶች ፊቷን ለማየት በብርቱ ተማጽነዋል። በተለይም ቅዱስ አባ ይስሐቅ ለሰባት ዓመታት ሳይታክት፣ በዕንባና በስግደት «ጌታዬ ሆይ! ለአንዲት ሰዓት እናትህን አሳየኝ» እያለ ከለመነ በኋላ፣ ድንግል ማርያም በታላቅ ግርማ ተገልጻለት የልቡን መሻት ፈጽማለች።


የሕዝቡን እምባ ያበሰች፣ የቅዱሳንን ናፍቆት የሞላች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፤ ዛሬም የእኛንና የሀገራችንን በጎ መሻት ሁሉ ትፈጽምልን! አሜን።

#ደብረምጥማቅ #ግንቦት21 #ድንግልማርያም #የእመቤታችንመገለጥ #ማኅሌተጽጌ #ኦርቶዶክስ #ተዋሕዶ #መንፈሳዊ #የቅዱሳንታሪክ #ተአምር

እንኳን ለመናኙ ሙሽራለቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ዓመታዊበዓል አደረሰን።ግንቦት 14 ቀንኀዲጎ ብእሲቶ።በዓሉን በአዲስ አበባ ደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊ ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ተገኝ...
22/05/2026

እንኳን ለመናኙ ሙሽራ
ለቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ዓመታዊ
በዓል አደረሰን።
ግንቦት 14 ቀን
ኀዲጎ ብእሲቶ።

በዓሉን በአዲስ አበባ ደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊ
ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ተገኝተን እናክብር
በበዓሉን ታሪክ የቅዱሱን ተጋድሎ ከአውደ ምሕረቱ እንሰማለን እንማራለን የምንሰማውን ለሕይወት ለበረከት ያድርግልን።

"ራሱን ባዶ አደረገ።"
ፊሊ 2፤7

ወልደ ንጉሥ
ገብረ መርአዊ
ብእሴ እግዚአብሔር
የትእግስት መድብል
የጽናት ተምሳሌት
ኹሉ በእጁ በደጁ ሆኖ ሳለ
ዛሬ አለም የሚባላበትን የሚጋደልበትን ምድራዊ
ሥልጣን "ሹመት ሺሞት" ብሎ አለምን የናቀ
ከጫጉላ ቤቱ ከትዳሩ ጎጆ ወጥቶ የሰማይ ቤቱን የሠራ
ለብዙ ዓመታት በቤተ እግዚአብሔር የኖረ ኋላም
አካሉ ተለውጦ ከአባቱ በንጉሥ ቴዎዶስዮስ ደጃፍ ተጥሎ የአባቱ ውሾች አውቀውት ቁስሉን ሲልሱ የአባቱ ወታደሮች እጣቢ ውሐ የምግብ የአጥንት ትራፊ ሲደፉበት በብዙ ተጋድሎ ገድሉን የፈጸመ።
መናኙ ሙሽራ ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ
በረከቱ ይደርብን በቃልኪዳኑ ይጠብቀን
ከዘረኝነት ደዌ ከፍቅር ረሐብ ከዝሙት እሳት ከክሕደት አሽክላ በአማላጅነቱ ይሰውረን አሜን አሜን አሜን

ዛሬ  ቅዱስ ሩፍኤል ነው 13♥ሩፋኤል ማለት «እግዚአብሔር ፈዋሽ» ነው። ማለት ነው።•••••>ሩፋኤል ማለት «ፈታሄ ማኀፀን» ማለት ነው። ሣልሳይ ሊቀ መላእክት ነው። በኃያላት ላይ የተሸመ የ...
21/05/2026

ዛሬ ቅዱስ ሩፍኤል ነው 13♥
ሩፋኤል ማለት «እግዚአብሔር ፈዋሽ» ነው። ማለት ነው።
•••••>ሩፋኤል ማለት «ፈታሄ ማኀፀን» ማለት ነው። ሣልሳይ ሊቀ መላእክት ነው። በኃያላት ላይ የተሸመ የመላእክት አለቃ ሩፋኤል ነው።
ቅዱስ ሩፋኤል «መራኄ ፍኖት» መንገድ መሪም ይባላል፡፡
""ከበሩት ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ እኔ ሩፋኤል ነኝ""።
(ጦቢት 12 ፥13)
ቅዱስ ሩፋኤል ሆይ የጦቢትን አይን እንደፈወስህ እኛንም ከዚህ አለም ፈተና ከሃጥያት እስራት የተፈውስን አድርገን ምህረት ከአምላካችን ለምንልን🤲 አሜን 👏💒🙏

ሥ ጋ ህ ን : አ ፍ ል ሰ ው : በ ው ስ ጡ : ያ ኖ ራ ሉግንቦት 12 ቀን ቅዱስ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቅዱስ ዐፅማቸው ቀድሞ ካረፉበት (ከተቀበረበት) ሥፍራ (ደብረ አስቦ) አሁ...
20/05/2026

ሥ ጋ ህ ን : አ ፍ ል ሰ ው : በ ው ስ ጡ : ያ ኖ ራ ሉ

ግንቦት 12 ቀን ቅዱስ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቅዱስ ዐፅማቸው ቀድሞ ካረፉበት (ከተቀበረበት) ሥፍራ (ደብረ አስቦ) አሁን ወዳለበት ሥፍራ (ደብረ ሊባኖስ) የተዘዋወረበት ቀን ነው፡፡

ስለ ቀናች ሃይማኖትህ
ስለ ልብህ ንጽሕናና ቅድስና
ስለ ብዙ ጾም ጸሎት ስግደትህ
ሃይማኖትን ለማስተማር መላዋን ኢትዮጵያን ስለመዞርህ
በሰባት ዓመታት ቁመት የአንዱ አገዳ እግርህ ስለ መሰበሩ
ወደ ኢየሩሳሌም ወርደህ ልዩ ልዩ የቅዱሳን ቦታዎች ስለ መሳለምህ
ከአረማውያን ሕዝብ ጋር በሃይማኖት ስትታገል ደምህን ስለ ማፍሰስህ

በማለት የሕይወት አክሊላትን ካቀዳጃቸው በኋላ

ዝክራቸውን በማዘከር መታሰቢያቸውን የሚያደርጉ ሁሉ በዚህ ዓለምም ሆነ በወዲያኛው ዓለም ፍጹም ዋጋና ፍጹም ክብር እንደሚሰጣቸው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለጻድቁ አባታችን ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቃል ኪዳን ገባላቸው ።

ደግሞ « በስምህ ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ልጆችህ ሠርተው ሥጋህን አፍልሰው በውስጡ ያኖራሉ ›› አላቸው ።

https://youtu.be/IYb8pc7L2Gw
17/05/2026

https://youtu.be/IYb8pc7L2Gw

Join this channel to get access to perks:https://linktw.in/UdjJVtጽንዓ Tube | Tsinia Tube ኦርቶዶክሳዊ የቪድዮ ትምህርቶች፣ መዝሙራት፣ ምክረ አበው፣ ብሒለ አበው፣ ወቅታዊ የቤተክርስቲያን መረጃዎች፣ ሃ...

https://youtu.be/npWTh913mrk
15/05/2026

https://youtu.be/npWTh913mrk

🟢ተወዳጅ የቅዱስ ገብርኤል መዝሙሮች ስብስብJoin this channel to get access to perk...

https://youtu.be/En3oHik4_7w
15/05/2026

https://youtu.be/En3oHik4_7w

Join this channel to get access to perks:https://linktw.in/UdjJVtጽንዓ ትዩብ | Tsinia Tube ኦርቶዶክሳዊ የቪድዮ ትምህርቶች፣ መዝሙራት፣ ምክረ አበው፣ ብሒለ አበው፣ ወቅታዊ የቤተክርስቲያን መረጃዎች፣ ሃይ...

. ❤ጥር 18 ” ዝርዎተ አጽሙ ” ቅዱስ ጊዮርጊስ❤✔💟ዳግመኛም ያ ከሃዲ ንጉስ ዱድያኖስ ግንድ አምጥተው ቅዱስ ጊዮርጊስን በግንዱ ላይ እንዲቸነክሩት አዘዘ፤በላዩም ላይ ሰም አፍስሰው እሳት እ...
26/01/2026

. ❤ጥር 18 ” ዝርዎተ አጽሙ ” ቅዱስ ጊዮርጊስ❤
✔💟ዳግመኛም ያ ከሃዲ ንጉስ ዱድያኖስ ግንድ አምጥተው ቅዱስ ጊዮርጊስን በግንዱ ላይ እንዲቸነክሩት አዘዘ፤በላዩም ላይ ሰም አፍስሰው እሳት እንዲያነዱበት አደረገ ፤ ከዚህም በኃላ እንደመጭመቂያ ሆኖ ከተሰራ የስቃይ መሳሪያ ላይ አወጡት ሰውነቱን እንዲሰነጥቁት እንዲጨምቁት አዘዘ፤

✔💟አንጀቱ ሁሉ ወጥቶ ከምድር ላይ እስኪዘረገፍ ድረስ እንዲሁ አደረጉበት ነፍሱ ከስጋው ተለየች የሰማእቱን ሰጋ አቃጠሉት ፈጩት አመድም ሆነ በቀፎ አድርገው ይድራስ ወደሚባል ተራራ ላይ በነፋስ ዘሩት ደብረ ይድራስ ማለት ምድረ በዳ ነው ወታደሮቹ የታዘዙትን ፈጽመው ተመለሱ።

✔💟ያንጊዜም መብረቅ ነጎድጓድ ታላቅ ንውጽውጽታ ሆነ ምድርም ከመሰረቷ እስክትናወጽ ድረስ ከሰማይ ድምጽ ተሰማ ጌታችን መድሐኒታችን እየሱስ ክርስቶስ መላእክትን አስከትሎ በብሩ ደመና ወረደ በተራራውም ላይ ተቀመጠ አራቱን የምድር ነፋሳት የሰማእቱን ስጋ እንዲሰበሰቡ አዘዛቸው ከሞትም አስነሳው ኃይሉን አሳደረበት ባርኮትም ወደ ሰማይ አረገ፤

✔💟ከዚህ በኃላ ቅዱስ ጊዮርጊስ እየሮጠ ወታደሮቹን ተከተላቸው ወንድሞቼ ቆዩኝ ከናንተ ጋር ልሂድ እያለ ተጣራ የነዚህ የወታደሮች ቁጥር አራት ነው ስማቸው ህልቶን፤አግሎሲስ፤ሶሪስና አስፎሪስ ነው፤

✔💟ይህንን ታላቅ ተአምራት አይተው አምነዋል፤ በኃላም በሰማእትነት ሞተዋል፤ ይህ የሆነው ጥር 18 በዛሬዋ ቀን ነው ይህንንም ቀን ” ዝርዎተ አጽሙ ” ስትል ቤተክርስቲያን ሰማእቱን አዘክራ ትውላለች፤

✔💟በስሙ በታነጹለት አብያተክርስቲያናት በሙሉ ታቦተ ህጉ ውጥቶ በደማቁ ተከብሮ ይውላል።

✔💟አራዳ ጊዮርጊስን የተከሉት ደጉ ንጉስ እምዬ ምኒሊክ ናቸው ታዲያ የዚህን ታላቅ ደብር መሰረቱን ሲጥሉ የቅዱስ ጊዮርጊስ መቃብር ከሚገኝበት ቦታ አፈሩን በመርከብ አጓጉዘው በበቀሎ በፈረስ አስጭነው መሰረት አድርገውታል፤ይህንን ከአባቶቻችን የሰማነው ነው፤ ከበዓሉ በረከት ያሳትፈን።

↪❤ምንጭ ገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ 《ምዕራፍ 6 ፤: 15 – 18》

Address

Bole
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጽንዓ Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share