25/08/2026
ነሐሴ/19/2018/ ዓመተ ምህረት
👉በስመ አሐዱ አምላክ አሜን አምላካችን መድኃኒታችን ለምናመሰግንበት ለመልአኩ ወርሐዊ መታሰቢያ ክብረ በዐል እንኳን አደረሰን
እኔ #በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው #ገብርኤል ነኝ
ሉቃ.1፥19
👉ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን አባቶቻችን እንዳስተማሩን ዘመኑ ጣኦት የሚመለክበት ንጉስ ናቡከደነፆር በባቢሎን ምርኮ የወሰዳቸው #የእግዚአብሔር ሰዎች አናንያ፤ አዛርያ፤ ሚሣኤል እጅግ ይወዳቸው ነበር
👉ከባቢሎናውይን ይልቅ በትንቢተ ዳንኤል ምዕራፍ ሦስት ሰፍሮ በምናገኘው ታሪካቸው እንደሚግረን ንጉሱ የጣኦት ምስል አሰራ በገሊላ አውራጃ ያለውን ሕዝብ ጠርቶ ለጣኦቴ ያልሰገደ ወደ እሳት ውስጥ ይጣላል ብሎ አወጀ የንጉስ ትዕዛዝ ነውና ሕዝቡ ሁሉ ለጣዖቱ ሲንበረከክ እነርሱ ግን ቆመው ያዩ ነበር
👉ናቡከደነፆር እርሱ ላስቆመው ጣኦት አለመስገዳቸውን ሲሰማ ተናደደ፤ ተበሳጨም እሳቱን 7 እጥፍ እንዲነድ አስደረገ ሦስቱንም አስሮ እሣቱን እያሳየ "ከመቃጠል ወይስ ለእኔ ጣኦት መስገድ የቱ ይሻላል ቢላቸውም #የእግዚአብሔር የሆነ ሰው ምንም ነገር አያስፈራውምና የምናመልከው አምላካችን ከሚነደው ከእሳቱ እቶን ሊያድነን ይችላል ባያድነንም ግን አንተ ላቆምከው ጣኦት አንሰግድም አሉት
👉በዚህ ጊዜ ጉልበት ያላቸው ሠዎች ተፈልገው ሦስቱን ወጣቶች አስረው ወደ እሳት ቶን ውስጥ ጣሏቸው አስረው የጣሉቸው ወታደሮች የእሳቱ ወላፈን አቃጠላቸው ግን መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ እሳቱን አበረደላቸው አጠፋላቸው
👉በዚህም ጊዜ ንጉስ ናቡከደነፆር እንዲህ በማለት መሰከረ "እኛ አስረን የጣልናቸው ሦስት ነበሩ አሁን ግን አራተኛው ሰው በእሳቱ ሲመላለስ ይታየኛል የአራተኛው መልክ ደግሞ #የአማልክትን መልክ ይመስላል አለ
👉 #የእግዚአብሔር የማዳኑ ስራ ሲገለጥ ቅዱስ ገብርኤል ሲታይ አዋጁ ሁሉ ተሻረ ጉልበት ሁሉ ለጣኦት ይስገድ ተብሎ የነበረው አዋጅ ተሽሮ ጉልበት ሁሉ ለሠለስቱ ደቂቅ አምላክ የሚል አዋጅ ታወጀ
👉የስሙ ትርጓሜ ታማኝ አገልጋይ የሆነው በዘመናችንም ለበርካቶች ታላቅ ተአምራት ሰርቷል ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ጥበቃው ረድኤት በረከቱ አይለየን
👉 #የእግዚአብሔር አብ ፀጋ የወልድ ፍቅር የመንፈስ ቅዱስ አንድነት የእናታችን ማርያም አማላጅነት የቅዱሳን መላዕክት ጥበቃ የቅዱሳን አባቶቻችን እናቶቻችን ረድኤት በረከት ጥርጥር የሌለባት የመንግስተ ሰማያት መዉረሻ ንፅህት ቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነታቸው ከኛ ጋር ፀንታ ትኑር "አሜን"