abe business

abe business ONE STANDARD AFRICA

በዲላ ከተማ በኢንተርናሽናል አስፓልት መንገድ ላይ በደረሰ አሰቃቂ የትራፊክ አደጋ ፍቅረኛሞች የነበሩ ሁለት ወጣቶች ሕይወታቸውን ማጣታቸው ተገለጸ። እንደተገኘው መረጃ፣ በቀን ነሀሴ 17/201...
24/08/2026

በዲላ ከተማ በኢንተርናሽናል አስፓልት መንገድ ላይ በደረሰ አሰቃቂ የትራፊክ አደጋ ፍቅረኛሞች የነበሩ ሁለት ወጣቶች ሕይወታቸውን ማጣታቸው ተገለጸ።

እንደተገኘው መረጃ፣ በቀን ነሀሴ 17/2018 ወንዱ ወጣት ፍቅረኛዋን በዲላ ከተማ ኢንተርናሽናል አስፓልት ላይ ባለሁለት ጎማ ሞተር ሳይክል እያለማመዳት በነበረበት ወቅት 22 ጎማ ያለው ከባድ ጭነት ተሳቢ መኪና በላያቸው በመውጣቱ ከባድ አደጋው መድረሱ ተገልጿል።

በአደጋው ወንዱ ወጣት በአደጋው ቦታ ላይ ወዲያውኑ ሕይወቱን ሲያጣ፣ ሴቷ ወጣት ከባድ ጉዳት ደርሶባት ለሕክምና እርዳታ ብትወሰድም ሕይወቷን ማዳን እንዳልተቻለ ተገልጿል።

ሴቷ ወጣት በዲላ ከተማ ቆፌ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪ እንደነበረችና በትምህርቷ ብርቱና ጎበዝ ተማሪ እንደነበረች ተገልጿል። የወጣቷ ሕይወት ማለፍም በቤተሰቦቿ፣ በጓደኞቿና በመላው የትምህርት ማኅበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ሐዘን ፈጥሯል።

የአደጋው ትክክለኛ መንስኤና ሁኔታ በሚመለከታቸው አካላት በሚደረግ ምርመራ የሚጣራ ሲሆን፣ አሳዛኙ ክስተት ዋና የመንገድ አውራ ጎዳናን ለሞተር ሳይክል ልምምድ መጠቀም እንዲሁም የትራፊክ ሕጎችንና የደህንነት ጥንቃቄዎችን አለመከተል ሊያስከትል የሚችለውን ከባድ መዘዝ ያሳስባል።

በአሰቃቂው አደጋ ሕይወታቸውን ላጡት ወጣቶች ፈጣሪ ነፍሳቸውን ይማር። ለወላጆቻቸው፣ ለዘመዶቻቸውና ለጓደኞቻቸው መጽናናትን እንመኛለን።

abe business Osa Osa

𝐀𝐑𝐒𝐄𝐍𝐀𝐋 ለ 18ኛ ጊዜ  🥰  የ FA 𝐂𝐎𝐌𝐌𝐔𝐍𝐈𝐓𝐘 𝐒𝐇𝐈𝐄𝐋𝐃 ዋንጫ አሼንፋለች   2026 champion       ARSENAL 3 - 0 MANCHESTER CITY
16/08/2026

𝐀𝐑𝐒𝐄𝐍𝐀𝐋 ለ 18ኛ ጊዜ 🥰 የ FA 𝐂𝐎𝐌𝐌𝐔𝐍𝐈𝐓𝐘 𝐒𝐇𝐈𝐄𝐋𝐃 ዋንጫ አሼንፋለች 2026 champion

ARSENAL 3 - 0 MANCHESTER CITY

Manchester city
09/08/2026

Manchester city

አርሰናል
09/08/2026

አርሰናል

የጆኒ እና ሴዶ MMA ፍልሚያ መግቢያ ትኬት VVIP 100 ሺ ብር መሆኑ ተገለፀ::ቀን: ነሐሴ 21ቦታ: አድዋ 00 ሙዚየም (Adwa 00 Museum)ቲኬት ለመግዛት: በ M-Pesaየቲኬት ዓይ...
08/08/2026

የጆኒ እና ሴዶ MMA ፍልሚያ መግቢያ ትኬት VVIP 100 ሺ ብር መሆኑ ተገለፀ::

ቀን: ነሐሴ 21
ቦታ: አድዋ 00 ሙዚየም (Adwa 00 Museum)
ቲኬት ለመግዛት: በ M-Pesa

የቲኬት ዓይነቶች እና ዋጋ:

1. VVIP Ringside - 100,000 የኢትዮጵይ ብር

* ልዩ የሪንግ አጠገብ መቀመጫ
* ያልተገደበ የምግብ እና የመጠጥ አገልግሎት
* ወደ ተወዳዳሪዎች ልብስ መቀየሪያ ክፍል የመግባት እድል
* መቀመጫ የመምረጥ መብት

2. VVIP Premium - 50,000 የኢትዮጵይ ብር

* 2ኛ ተከታታይ ረድፍ መቀመጫ
* 2 የምግብ እና 10 የመጠጥ ኩፖኖች
* መቀመጫ የመምረጥ መብት

3. VVIP Normal - 30,000 የኢትዮጵይ ብር

* ከ 3ኛ እስከ 5ኛ ረድፍ መቀመጫዎች
* 2 የምግብ እና 7 የመጠጥ ኩፖኖች
* መቀመጫ የመምረጥ መብት

4. VIP - 20,000 የኢትዮጵይ ብር

* 1 የምግብ እና 4 የመጠጥ ኩፖኖች
* መቀመጫ የመምረጥ መብት

5. Regular - 10,000 የኢትዮጵይ ብር

6. Early Bird - 4,000 የኢትዮጵይ ብር
(በተወሰነ ቁጥር የቀረበ)
ቲኬትዎን አሁኑኑ በ M-Pesa ይቁረጡ!

ቲኬቱም እያለቀ ነው ተብሏል.......
Via ETFC

PAN-AFRICAN LEADERS WHO CHANGED AFRICA FOREVER🔑🔑🔑🔑🌍
08/08/2026

PAN-AFRICAN LEADERS WHO CHANGED AFRICA FOREVER🔑🔑🔑🔑🌍

በኦሮሚያ ክልል ይመረት የነበረው ዓመታዊ የግብርና ምርት ከ168 ሚሊዮን ኩንታል ወደ 510 ሚሊዮን ኩንታል ማደጉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ...
08/08/2026

በኦሮሚያ ክልል ይመረት የነበረው ዓመታዊ የግብርና ምርት ከ168 ሚሊዮን ኩንታል ወደ 510 ሚሊዮን ኩንታል ማደጉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለፁት፤ በግብርናውና በሌሎች የኢኮኖሚ ዘርፎች የተመዘገበው ስኬት የክልሉን ገቢ በከፍተኛ መጠን ዕድገት ተመዝግቧል።

ከለውጡ በፊት በኦሮሚያ ክልል የሚታረሰው መሬት ከነበረበት 6 ነጥብ 6 ሚሊዮን ወደ 17 ሚሊዮን ሄክታር ማደጉን ጠቁመዋል። ይህም ስኬት አዲስ መሬት ተፈጥሮ ሳይሆን፣ መሬቱን በአግባቡና በስፋት በመጠቀም እንዲሁም አርሶ አደሮችን በኩታ-ገጠም በማደራጀት የተገኘ ውጤት መሆኑን አስረድተዋል።

ላለፉት 100 ዓመታት በላይ ሲታረስ የነበረው መሬት 168 ሚሊዮን ኩንታል ሲያመርት፣ ባለፉት ስምንት ዓመታት ውስጥ ምርቱን ወደ 510 ሚሊዮን ኩንታል ማድረስ መቻሉ ትልቅ ለውጥ መሆኑን ገልጸዋል።

በ2010 ዓ.ም በክልሉ በበጋም ሆነ በበልግ (ቡናን ሳይጨምር) የሚመረተው ምርት 168 ሚሊዮን ኩንታል ብቻ እንደነበር ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በቅርብ ዓመታት በተደረገው ጥረት ወደ 510 ሚሊዮን ኩንታል አድጓል።

በሌላ በኩል የክልሉ ዓመታዊ ገቢ ከለውጡ በፊት 13.5 ቢሊዮን ብር ብቻ የነበረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ወደ 342 ቢሊዮን ብር ከፍ ማለቱን ጠቅሰዋል። ዓመታዊ በጀቱም ከ52 ቢሊዮን ብር ወደ 704 ቢሊዮን ብር አድጓል።

የክልሉ ኢኮኖሚ በዚህ ልክ ያደገውና ስኬቱ የተገኘው የሥራ ነፃነት በመረጋገጡ መሆኑን ገልፀው፣ የክልሉ ሕዝብ ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ተመልሷል ማለት ባይቻልም፣ መሬት ላይ የሚታይ መሠረታዊ ለውጥ መምጣቱን አረጋግጠዋል።

ይህ የኢኮኖሚ ዕድገት የተጎሳቆሉና ጽዱ ያልነበሩ ከተሞች ለኑሮ ምቹ እንዲሆኑ፣ የመሠረተ ልማት ዝርጋታዎች እንዲሻሻሉና የአገልግሎት አሰጣጥ እንዲቀላጠፍ አስተዋጽኦ ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

abe business Osa Osa

AMAZING WORK IN KENYA
07/08/2026

AMAZING WORK IN KENYA

Address

Addis Ababa
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when abe business posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share