Zemen Construction Corporation/ZCC/ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን

  • Home
  • Ethiopia
  • Bahir Dar
  • Zemen Construction Corporation/ZCC/ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን

Zemen Construction Corporation/ZCC/ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን/Zemen Construction Corporation/ZCC/

20/03/2026




👉ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ !!እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን!በዓሉ የሰለም፣ የፍቅር ፣ የጤና እና የተቸገሩ ወገኖቻችንን የምንጠይቅ...
20/03/2026

👉ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ !!
እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን!

በዓሉ የሰለም፣ የፍቅር ፣ የጤና እና የተቸገሩ ወገኖቻችንን የምንጠይቅበትና ያለንን የምናካፍልበት ያማረ በዓል ይሁንልን።

!!
!!

🌙 መልካም የኢድ አልፈጥር በዓል!! 🌙

ZCC
Delivering Excellence!!




ክፍት የስራ ቅጥር ማስታወቂያ
19/03/2026

ክፍት የስራ ቅጥር ማስታወቂያ

ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን በአዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙ የኮንስትራክሽን ግብዓት አቅራቢዎች፣ ትራንስፖርተሮች፣ አማካሪዎች እና አጋር አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ፤አዲስ አበባ፤ የ...
07/03/2026

ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን በአዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙ የኮንስትራክሽን ግብዓት አቅራቢዎች፣ ትራንስፖርተሮች፣ አማካሪዎች እና አጋር አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ፤

አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018 ዓ.ም

ኮርፖሬሽናችን በአዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙ
የኮንስትራክሽን ግብዓት አቅራቢዎች፣ ትራንስፖርተሮች፣ አማካሪዎች እና አጋር አካላት ጋር የምክክር መድረክ በኢሊሌ ኢንተርናሽናል ሆቴል እያካሄደ ይገኛል።

ለመድረኩ የተዘጋጀ ሰነድ የኮርፖሬሽኑ አጭር መግለጫ፣ ተቋማዊ ሪፎርም፣ በግብዓት አቅርቦቱ በኮርፖሬሽኑ፣ በአቅራቢዎች፣ ትራንስፖርሮች እና አማካሪዎች ያጋጠሙ ተግዳሮቶችና መፍትሄዎቻቸው እንዲሁም የቀጣይ የስራ ዕድሎች በሚል በኮርፖሬሽናችን ዋና ስራ አስፈፃሚ የተከበሩ አቶ ታደሰ ግርማ ቀርቦ በተሳታፊዎች በኩል ገንቢ የሆኑ ሀሳብና አስተያየት ተጥቶበት በአማካሪዎች፣ አጋር አካላትና ሌሎች የሚመለከታቸው የኮርፖሬሽኑ አመራሮች ምላሽና ማብራሪያ ከተሰጠ በኃላ በኮርፖሬሽናችን ዋና ስራ አስፈፃሚ የተከበሩ አቶ ታደሰ ግርማ የማጠቃለያ ሀሳብ የግንባታ ግብዓት አቅርቦት ደንበኞቻችን ለኮርፖሬሽኑ ስኬት ጉልህ አስተዋፅኦ ያላቸው መሆኑን ተገንዝበን የአሰራር ማሻሻያዎችን አካሂደናል በቀጣይም የተሰጡ ሀሳብና አስተያየቶችን እንደ ግብዓት ወስደን ተጨማሪ ማሻሻያዎችን ለማድረግ ጥረት እናደርጋለን ለቀጣይ ዕቅዶቻችን ስኬት ከጎናችን እንድትሆኑ እና የላቀ አስተዋፅኦችሁን እንድትወጡ በማለት የዕለት መድረክ ተጠናቋል።

ZCC
DELIVERING EXCELLENCE!!

ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube https://www.youtube.com/
Facebook https://www.facebook.com/share/1F3JxayD5r/
Telegram https://t.me/ZemenCC
Instagram https://www.instagram.com/zemencc
Website http://www.zcc.org.et/
TikTok https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZM-92eNgkmVsrM
Email [email protected]

በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

 #ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን በግንባታው የተጠበበት  #የአብክመ ጤና ቢሮ እድሳት፣ ማስፋፊያና ዲጂታላይዜሽን በክቡር ር/መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ተጎበኘ።~~~~~~~~~~~~~~~~~~...
06/03/2026

#ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን በግንባታው የተጠበበት #የአብክመ ጤና ቢሮ እድሳት፣ ማስፋፊያና ዲጂታላይዜሽን በክቡር ር/መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ተጎበኘ።
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
የአብክመ ጤና ቢሮ እድሳት በዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን በልዩ የፕሮጀክት አመራር ስርዓት በጥራት ተከናውኗል።
የጤና ቢሮ እድሳት የግንባታው ዘርፍ በደረሰበት አዲስ የሸኔል ሆም ቴክኖሎጂን በመጠቀም ተጨማሪ ግንባታ እንዲሁም በተለይም ደግሞ የነበረበትን የቢሮ እጥረት የሚፈታ ማስፋፊያ፣የዲጂታላይዜሽንና የተሳለጠ አገልግሎት ለመስጠት ታስቦ የተሰራ ነው።

የቢሮው እድሳት ወቅቱን ከግምት ውስጥ በማስገባት ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችንና አሰራሮችን እስከታች ለመዘርጋት አመቺ የሆነ የመረጃ ስርዓትን ያሳለጠ እንዲሁም የተቋሙን የስልጠናዎችና ስብሰባዎች የአዳራሽ ወጪዎች የሚያስቀር ዘመናዊ አዳራሽን የያዘ ነው።

የቢሮ እድሳት ስራው በጥራትና ፍጥነት እንዲሁም በኃላፊነት መንፈስ ሰርቶ በማስረከብ በሚታወቀው ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን በልዩ የፕሮጀክት ስራ አመራር ተከናውኗል።
#ዘመንኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን

በዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ስራ ተቋራጭነት የተገነባው የደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል  የዲያግኖስቲክ ማዕከል ባለ 4 ወለል ሕንጻ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የማህበራዊ ዘ...
25/02/2026

በዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ስራ ተቋራጭነት የተገነባው የደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የዲያግኖስቲክ ማዕከል ባለ 4 ወለል ሕንጻ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) እና የክልሉ ጤና ቢሮ ሀላፊ አቶ አብዱከሪም መንግስቱ በተገኙበት በዛሬ ዕለት በደማቅ ዝግጅት ተመርቋል።
በዝግጅቱ ላይ የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊዎች፣ የደቡብ ወሎ ዞንና የደሴ ከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ የወሎ ዪኒቨርስቲ ፕሬዝደንት፣ የሀይማኖት መሪዋች፣ ልዩ ልዪ የሆስፒታሉ የህብረተሰብ ተወካዮች የተገኙ ሲሆን በፕሮግራሙ መሪ በኩል ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን የማዕከሉን ግንባታ በጥራት መስራት የቻለ እና ለክልሉ ጥሪት ፈጣሪ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል።

የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጂ ዶ/ር ሀይማኖት አየለ ተቋራጩ ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖርሽ ሕንጻውን በጥራት ገንብቶ በማስረከቡ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።






ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube https://www.youtube.com/
Facebook https://www.facebook.com/share/1F3JxayD5r/
Telegram https://t.me/ZemenCC
Instagram https://www.instagram.com/zemencc
Website http://www.zcc.org.et/
TikTok https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZM-92eNgkmVsrM
Email [email protected]

በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

እንኳን ደስ አለን እንኳን ደስ አላችሁ!!🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉ከዕውቅና ላይ ዕውቅና በመቀዳጀት ላይ ያለውዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ከገቢዎች ሚኒስቴር ባሕር ዳር...
14/02/2026

እንኳን ደስ አለን እንኳን ደስ አላችሁ!!

🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉

ከዕውቅና ላይ ዕውቅና በመቀዳጀት ላይ ያለው

ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ከገቢዎች ሚኒስቴር ባሕር ዳር ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር በተካሄደ የዕውቅና እና የንቅናቄ መድረክ ላይ የፕላቲንየም ግብር ከፋይ በመሆኑ የላቀ ዕውቅና ተሰጠው!!

።።።።፨፨፨።።።።
(የካቲት 07/2018 ዓ.ም) የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ከገቢዎች ሚኒስቴር ባሕር ዳር ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር የዕውቅና እና የንቅናቄ መድረክ አካሂዷል።

በዕውቅና እና ንቅናቄ መድረኩ ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር)፣ የገቢዎች ሚኒስትር ድኤታ ዳዊት ውብሸት፣ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የማኅበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ.ር)፣ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአሥተዳደር ዘርፍ አስተባባሪ አማኑኤል ፈረደ (ዶ.ር) ጨምሮ ሌሎችም ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል።

በመርሐ ግብሩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር) ግብር እና የግብር ስርጭትን ማዘመን ለአንድ ሀገር ሥርዓተ መንግሥት መቀጠል እና መጽናት ቁልፍ ከኾኑ ጉዳዮች መካከል አንዱ ነው ብለዋል።

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ከገቢዎች ሚኒስቴር ባሕር ዳር ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር የዕውቅና እና የንቅናቄ መድረክ የምስጉን፣ የነሀስ፣ የብር፣ የወርቅ እና የፕላቲንዬም ደረጃ ተሸላሚዎችን ዕውቅና የተሰጠ ሲሆን ኮርፖሬሽናችን በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው እያበረከተው ካለው አስተዋጽኦ በተጨማሪም ግብር የሀገር ዋልታ እና ማገር መኾኑን አምኖ በሚገነባቸው ግንባታዎች እና በሚያመርታቸው የግንባታ ግብዓቶች ህጋዊ አሰራሩን ተከትሎ በመስራት ሀገራዊ ግዴታውን በአግባቡ ስለተወጣ እና ታማኝ ግብር ከፋይ በመሆኑ ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን በተከታታይ ዓመታት ደረጃውን አሰጠብቆ የፕላቲንዬም ተሸላሚ በመሆን ዋና ስራ አስፈፃሚው ክቡር አቶ ታደሰ ግርማ ከዕለቱ የክብር እንግዳ ዕውቅና ተሰጥቷል።

በአባይ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ስር ካሉ የልማት ድርጅቶች መካከል ዳሽን ቢራ ፋብሪካ በተመሳሳይም የፕላቲንዬም ተሸላሚ ሲሆን በሆልዲንጉ ስር ካሉ የልማት ድርጅቶች መካከል ከኮንስትራክሽን ዘርፉ ብቸኛ ተሸላሚ ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ሆኗል።

በመጨረሻም የዕለቱ የክብር እንግዳ ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር)
እናንተን ያመሰገነው ግብርን ላለመክፈል የሚደበቁ ባሉበት ሁኔታ በታማኝነት ስለከፈላችሁ ነው ብለዋል። ሌሎችም በታማኝነት ግብርን እንዲከፍሉ አሳስበዋል።

የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ ክቡር አቶ ታደሰ ግርማ ለዚህ ውጤት መገኘት አስተዋጽኦ ለነበራቸው የኮርፖሬሽናችን ስራ አመራር ቦርድ አመራሮች፣ የአባይ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ አመራርና ሰራተኞች እንዲሁም ለኮርፖሬሽናችን መላ ሰራተኞች የላቀ ምስጋና አቅርበዋል።






ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube https://www.youtube.com/
Facebook https://www.facebook.com/share/1F3JxayD5r/
Telegram https://t.me/ZemenCC
Instagram https://www.instagram.com/zemencc
Website http://www.zcc.org.et/
TikTok https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZM-92eNgkmVsrM
Email [email protected]

በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ጥበበኛው ኢንጅነር ንጋት ዘውዱ
12/02/2026

ጥበበኛው ኢንጅነር ንጋት ዘውዱ

የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ጸጋ በጥበብ እያደሰ ካለው የ"ገበታ ለትውልድ" ፕሮጀክቶች ጀርባ፣ ስሙ በሥራው የሚጠራ ድንቅ ባለሙያ አለ። በጎርጎራ ምድር ውበትን የከተበው፣ በሎጎ ሐይቅ ዳርቻ .....

የዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን የ"ሪፎርም 2017" አንዱ አካል የሆነውን የቢሮ ኢንተሪየር ዲዛይን ማስወብ ምረቃ እንዲሁም የተቀናጀ የአሰራር ስርዓት(ERP) ሲስተም የዕወጃ ፕሮግራም በአብ...
10/02/2026

የዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን የ"ሪፎርም 2017" አንዱ አካል የሆነውን የቢሮ ኢንተሪየር ዲዛይን ማስወብ ምረቃ እንዲሁም የተቀናጀ የአሰራር ስርዓት(ERP) ሲስተም የዕወጃ ፕሮግራም በአብክመ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱ ሁሴን(ዶ/ር) አማካኝነት ተመርቆ ወደ ትግበራ ገባ።

ቀን፡ ማክሰኞ፣ [የካቲት 03/2018 ዓ.ም ባህርዳር

በአዲስ መልክ ኢንተርየር ዲዛይን ተውቦ የተጠናቀቀው ቢሮ ጉብኝት በማድረግ ምረቃ በማካሄድ ፕሮግራሙ የተጀመረ ሲሆን።

በመቀጠልም በአዳራሽ ፕሮግሩሙ ቀጥሎ የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ታደሰ ግርማ የመክፈቻ ንግግር የተከፈተው ፕሮግራም ዛሬ የአንድ ተቋም ዕድገት ብቻ ሳይሆን፣ የክልላችንን የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ወደ አዲስ ከፍታ የሚያሸጋግር የለውጥ ጉዞን ለማብሰር ነው። ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን "ዘመኑን የዋጀ ተቋም" የመሆን ራዕዩን ሰንቆ፣ በ2017 በጀት ዓመት የጀመረውን የተቀናጀ የሪፎርም ፍኖተ ካርታ ወደ ተግባር በመቀየር ዛሬ የመጀመሪያዎቹን ፍሬዎች ቀማስመርቅ
የሪፎርም ጉዞአችን ስኬቶችን ጀምሯል በማለት ንግግራቸውን የጀመሩት ዋና ስራ አስፈፃሚው በመቀጠልም "ዘመን ሪፎርም 2017" በወረቀት ላይ የሰፈረ ዕቅድ ብቻ ሳይሆን፣ የተቋማችንን ነፍስና ስጋ የለወጠ ሂደት ነው። በዚህ ጉዞ ውስጥ አምስት ዋና ዋና ምሶሶዎችን ትኩረት ሰጥተን እየሰራን እንገኛለን፦
1- የማንነት ለውጥ(Rebranding)፦ ተቋማችን ከጊዜው ጋር እንዲራመድ የስያሜ፣ የንግድ ምልክት (Logo) እና የራዕይ ክለሳ በማድረግ አዲስ ማንነትን ተላብሰናል።
2- ሰው-ተኮር መዋቅር፦ ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በሳይንሳዊ ጥናት ላይ የተመሰረተ መዋቅራዊ አደረጃጀት ዘርግተናል። ሰራተኞቻችንን በብቃት (Merit) መርህ ከመመደብ ባለፈ፣ አዳዲስና ውጤታማ አመራሮችን ወደ ፊት በማምጣት ተቋማዊ ጉልበቱን አድሷል።
3- ዲጂታላይዜሽን (ERP እና BIM)፦ የERP (Enterprise Resource Planning) ሶፍትዌር አሰራራችንን ግልጽ፣ ፈጣንና የተሳለጠ ያደርገዋል። ከዚህ በተጨማሪም፣ በክልላችን ቀዳሚና ብቸኛ የሚያደርገንን የBIM (Building Information Modeling) ቴክኖሎጂን ለምህንድስና ባለሙያዎቻችን በማስተማርና የስራ ክፍሉን በዘመናዊ ቁሳቁስ በማደራጀት፣ የግንባታ ጊዜንና ወጪን ለመቀነስ እንዲሁም ጥራትን ለማረጋገጥ ዝግጁ ሆነናል።
4- ዘመናዊ የአሰራር ስርዓት፦ ከፌዴራልና ከዓለም አቀፍ ተቋማት ልምድ በመቅሰም፣ ነባር ችግሮችን የሚፈቱ የአሰራር መመሪያዎችን አሻሽለን ወደ ስራ ገብቷል።
5- ዓለም አቀፋዊነት (Internationalization)፦ ደረጃችንን የጠበቀ አገልግሎት ለመስጠትና የISO Certification ባለቤት ለመሆን የጀመርነው ዝግጅት በጥሩ ሂደት ላይ ይገኛል።

6- የቢሮ ሪኢኖቬሽንና የስራ ከባቢ
ዛሬ በምናስመርቀው የተሻሻለና በዘመናዊ መልኩ የተገነባ (Renovated) ቢሮአችን፣ ለሰራተኞቻችን ምቹ የስራ ከባቢን በመፍጠር የተሻለ ምርታማነትን ለማምጣት ያለን ቁርጠኝነት ማሳያ ነው። ዲጂታላይዜሽንና ምቹ የስራ ቦታ ተደምረው ለደንበኞቻችን የምንሰጠውን አገልግሎት ላቅ ያለ ያደርጉታል።

በመጨረሻም ዘመን ኮንስትራክሽን የክልላችንና የሀገራችን የልማት አጋር ሆኖ እንዲቀጥል፣ የክልላችን አመራር፣ ደንበኞቻችንና አጋር አካላት ከጎናችን እንድትቆሙ፣ ድጋፋችሁና ትብብራችሁ እንዳይለየን በአክብሮት እጠይቃለሁ በማለት የዕለቱ የክብር እንግዳ ዕወጃ እንዲያካሂዱ ገብዘዋል።

በመቀጠልም የERP ሶፍትዌር በዛሬው ዕለት በአብክመ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱ ሁሴን(ዶ/ር) አማካኝነት በይፋ ተመርቆ ወደ ትግበራ መግባቱ አውጀዋል የኮርፖሬሽናችን ICT ክፍል ኃላፊ አቶ አስመሮ ላቂያውና አልሚ ድርጅቱ ERP SOLUTION PLC ስራ አስኪያጅ አቶ ፍቅሩ ተሾመ ስለ ERP ሲስተም ትግበራ ገለፃ አድርገዋል።
በመጨረሻም የአብክመ ምክትል ፕሬዝዳንት የዕለቱ የክብር እንግዳ አብዱ ሁሴን(ዶ/ር) የስራ መመሪያና የመዝጊያ ንግግር በማድረግ የዕለቱን ፕሮግራም ተጠናቋል።


!!

ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube https://www.youtube.com/
Facebook https://www.facebook.com/share/1F3JxayD5r/
Telegram https://t.me/ZemenCC
Instagram https://www.instagram.com/zemencc
Website http://www.zcc.org.et/
TikTok https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZM-92eNgkmVsrM
Email [email protected]

በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ኮርፖሬሽናችን በክልላችን ለሚካሄዱ የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶችን እንዲመራ እና በልዩ ሁኔታ አስተዋፅኦ እንዲያደርግ የተመደበው ወጣቱና ብልሁ እንጅነር ንጋት ዘውዱ ሌሎች አጋር አካላት አስተባ...
08/02/2026

ኮርፖሬሽናችን በክልላችን ለሚካሄዱ የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶችን እንዲመራ እና በልዩ ሁኔታ አስተዋፅኦ እንዲያደርግ የተመደበው ወጣቱና ብልሁ እንጅነር ንጋት ዘውዱ ሌሎች አጋር አካላት አስተባብሮ የወሎ ሎጎ ሀይቅ ሪዞርት በውጤታማነት ተጠናቆ እንዲመረቅ ልዩ አስተዋፅኦ በማድረጉ ኮርፖሬሽናችን የላቅ ክብር ይሰማዋል።

ከዚህ ቀደም ውስብስብ የሆነ ዲዛይንና ወቅታዊ ችግሮችን ተቋቁመው የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርትን በብቃት ያጠናቀቁት ውድ ባልደረባችን ኢንጅነር ንጋቱ ዘውዱ እንደገና የወሎ ሎጎ ሃይቅ ሪዞርት ደግሞ በፕሮጀክት ማኔጅመንት ከፍተኛ የስራ ባህል ለውጥ በማምጣት በተያዘለት ጊዜ፣ ወጭና ጥራት መሰረት ተደርጎ እንዲጠናቀቅ ሙሉ ሃላፊነት ወስዶ ሪዞርቱ በግሩም መሃንዲሳዊ ጥበቡ ለስኬት ያበቃውንና ኮርፖሬሽናችን ለክልላዊና ሀገራዊ አስተዋኦ እንዲያበረክት የተመደበው ወጣቱ ኢንጅነር ንጋት ዘውዱ በዚህ የወጣትነት እድሜው ሃገራዊ ፕሮጀክቶችን በተሻለ ፍጥነትና ብቃት ውጤታማ ማድረግ በመቻሉ ከፍ ያለ ክብርና እውቅና ይገባዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም ይህንን እውቅና በመስጠታቸው ኮርፖሬሽናችን የላቅ ክብር ተሰምቶታል ለውዱ ባለደረባችንና ለመላ ሰራተኞቻችንም እንኳን ደስ አለን አላችሁ!!

በኮርፖሬሽናችን የአሰራር ማሻሻያ በተደረገባቸው መመሪያዎች እና ፖሊስዎች ለዋናው መ/ቤትና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች ስልጠና እየተሰጠ ነው።ዘመን ሪፎርም 2017 በሚል የተቋማዊ ሪፎርም ለማድረ...
08/02/2026

በኮርፖሬሽናችን የአሰራር ማሻሻያ በተደረገባቸው መመሪያዎች እና ፖሊስዎች ለዋናው መ/ቤትና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች ስልጠና እየተሰጠ ነው።

ዘመን ሪፎርም 2017 በሚል የተቋማዊ ሪፎርም ለማድረግ በፍኖተ ካርታ ከተያዙ መካከል አንዱ የኮርፖሬሽኑ የአሰራር መመሪያዎችን ፈጣን አገልግሎት ለመስጠትና ራዕዩን ለማሳካት እንዲያስችለው የፋይናንስ አስተዳደር፣ የንብረት አስተዳደር፣ የግዥና አቅርቦት እና የሰው ሀብት ልማት አመራር ማሻሻያ የተደረገባቸው የአሰራር መመሪያዎችን በራስ አቅም ለስራ አስፈፃሚዎች፣ በስራ አስፈፃሚ ደረጃ የሚገኙ አማካሪዎች፣ የማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊዎች ዳይሬክተሮች፣ የፕሮጀክት ጽ/ቤትና የማምረቻ ማዕከላት ስራ አስኪያጆች እንዲሁም ለቡድን መሪዎች ከቅዳሜ ጀምሮ የፋይናንስ አስተዳደር፣ የንብረት አስተዳደር፣ የግዥና አቅርቦት ዛሬ እሁድ ደግሞ የIFRS Policy ላይ ስልጠናው እየተሰጠ ይገኛል። በነገም ዕለት የስልጠና መርሀግብሩ ቀጥሎ በሰው ሐብት ልማት አመራር መመሪያ፣ በመልካም አስተዳደር እና የተቋማዊ ውስጣዊ አሰራር ቅንጅታዊ አሰራሮች ዙሪያ ስልጠናው በመስጠት ይጠናቀቃል።

ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ በዛሬው ዕለት ተካሄደ።የኮርፖሬሽኑ ስራ አስፈፃሚዎች፣ ሁሉም የስራ መሪዎች፣ የዋናው መ/ቤት ሁ...
06/02/2026

ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ በዛሬው ዕለት ተካሄደ።

የኮርፖሬሽኑ ስራ አስፈፃሚዎች፣ ሁሉም የስራ መሪዎች፣ የዋናው መ/ቤት ሁሉም ሰራተኞች፣ የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስራ አስኪያጆች፣ የፕሮጀክት ስራ አስኪያጆች እና የማምረቻ ማዕከላት አስተባባሪወች በተገኙበት በዋና ቢሮ አዳራሽ የተካሄደ ሲሆን በጠዋቱ መርሀግብር የኮርፓሬሽናችን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ታደሰ ግርማ የግማሽ ዓመቱ አፈፃፀም ሪፖርቱ በዋናው መ/ቤት የስራ መሪ ደረጃ የተገመገመ መሆኑና በዛሬው መድረክም ሁሉም ሰራተኛ እና የተጠሪ ተቋማት የስራ መሪዎች በተገኙበት የሚካሄደ የአፈፃፀም ግምገማ መድረክ ላይ የሚቀረበው ሪፖርት ወደ ውስጣችን በመመልከት መልካም አፈጻጸም የታየባቸውን የምናበረታታበትና ከውጤቱ ተሞክሮ የምንወስድበት እንዲሁም ሌሎች ወደ ተሻለ አፈፃፀም እንዲመጡ ክፍተቶችን የምንለይበት አና ድጋፍ የምናደርግበት መድረክ መሆን እንዳለበት በማሳስበ መድረኩን ከፍተዋል።
በመቀጠልም የኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት የዕቅድ ዝግጅትና ክትትል የስራ ክፍል ኃላፊ አቶ ሙሀመድ ጅብሪል ማራኪ በሆነ ፕረዘንቴሽን የቅድመ ዝግጅትና ምዕራፍ የውጤት ተኮር ስርዓት መሰረት በማድረግ በአራት ዕይታና በ21 ግቦች ተግባራትን በሁለት ክፍል ቀርቧል። የሪፖርቱ ዋና ዋና KPI አፈፃፀም:-
✅ የግንባታ ፕሮጀክቶች አማካይ አፈፃፀም 73.53% ነው፣
✅ የተጠናቀቁ ግንባታ የመጨረሻ ርክክብ ለማድረግ 14 ታቅዶ 13 ፕሮጀክቶችን ጥገና በማድረግ የመጨረሻ ርክክብ ተደርጓል አፈፃፀሙም 92.51% ነው።
✅ የገቢ ዕቅድ አፈፃፀም ከግንባታ ፕሮጀክቶች አፈፃፀም 74.17%
✅ ከልዩ ልዩ ገቢዎች አፈፃፀም 53.6 %
✅ በአጠቃላይ የገቢ አፈፃፀም 73.55 % ነው።
✅ ትርፍና ኪሳራ አፈፃም 70.50% ነው።

🎯 በጥንካሬ የተነሱ ነጥቦች

📌 ታቅደው የተካሄዱ ተቋማዊ ሪፎርሞች
📌 የመዋቅራዊ ሪፎርም መሰረት ተደርጎ የተካሄደ ውጤታማ ሪፎርም ከስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ እስከ ቡድን መሪ በአዳዲስና ወጣት አመራር ምደባ መደረጉ
📌 የአሰራር መመሪያዎች ማሻሻያ መደረጋቸው
📌 የዲጅታላይዜሽን ሪፎርም የERP ትግበራና
📌 የግንባታ መረጃ ሞዴል Building Information Modeling (BIM) ለመተግበር ስልጠና መሰጠቱና የቢሮ ቁሳቁስና ኤሌክትሮኒክስ ለማሟላት የተደረገ ጥረት
📌 አዳዲስ የኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂዎችን ለመተግበር የተደረገው ጥረት
📌 የዋጋ ንረትና የጥሬ ገንዘብ እጥረትን እንዲሁም የመዋቅራዊ አደረጃጀት ሪፎርም ትግበራ ሊያስከትል የሚችለው ችግርን ተቋቁሞ የፊዚካል ስራዎችን 73% መፈፀሙ

የአፈፃፀም ግምገማ መድረኩ ከምሳ ሰዓት በፊትና በኃላ ተሳታፊዎች ሀሳብና አስተያየት እንዲሰጡ ከተደረገ በኃላ በተነሱ ጥያቄዎችና ሀሳቦች የሚመለከታቸው አመራሮች ምላሽ ከሰጡ በኃላ የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ታደሰ ግርማ የማጠቃለያ አቅጣጫ በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል።

በቀጣይ 2 ቀናት በአጋጠሙ የአሰራር ክፍተቶች ዙሪያና የአሰራር ማሻሻያዎች የማነቃቅያ ስልጠናዎች ለዋና መ/ቤት እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች ስልጠና በመስጠት የሚቀጥል ሲሆን ማክሰኞ የካቲት 03/2018 ዓ.ም የተቋማዊ ሪፎርም አንዱ አካል የሆነውን የERP Digitalization የትግበራ ዕወጃና ምቹ የስራ ከባቢ የቢሮ ኢኖቬሽን ስራ የአብክመ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ አረጋ ከበደ እና ሌሎች የክብር እንግዶች በተገኙበት የምረቃ ፕሮግራም በማካሄድ ይጠናቀቃል።

Address

Bahir Dar

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 17:30
Saturday 08:30 - 00:30

Telephone

+2510582180102

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zemen Construction Corporation/ZCC/ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Zemen Construction Corporation/ZCC/ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን:

Share