27/05/2026
👉 የቢዳራ ከተማ መዘጋጃ ቤት ስራ አስኪያጅ የተከበሩ አቶ መሀመድ ነጋሽ ናሲር !!
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም፣ በጤና እና በደስታ አደረሳችሁ ።
የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ታላቅ መንፈሳዊ ቦታና የላቀ ትርጉም የሚሰጠው በዓል ነው።
የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል የታላቅ ፍቅር፣ የደግነትና የበረከት መገለጫ በመሆኑን ሕዝበ ሙስሊሙ ካለው ለሌለው በማካፈልና የተቸገሩትን ወገኖች በመደገፍ የእምነቱን አስተምህሮ በተግባር ሊተገብሩ ይገባል።
የሀገር ግንባታው ስኬታማ ሊሆን የሚችለው ማኅበራዊ እሴቶቻችንን ስናሳድግ በመሆኑ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ በምናደርገው ጉዞ ውስጥ እርስ በእርስ መደጋገፍን ወንድማማችነትንና ይቅር ባይነትን የዕለት ተዕለት ባህላችን በማድረግ የአንድነታችንን መሠረት ይበልጥ ማላቅ ይጠበቅብናል።
በመሆኑም መላው የከተማችን ሕዝበ ሙስሊም በበዓሉ ድባብ ሳይዘናጋ የነገውን ሀገራዊ ራዕይ ለመወሰን ግንቦት 24 ቀን በጥዋቱ ካርድ ወደ ወሰደበት ምርጫ ጣቢያዎች በመሄድ ድምፁን መስጠት ይጠበቅበታል።
የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል ለመላው የከተማችን ማህበረሰብ እንዲሁም በዓለም ዙሪያ ለምትገኙ የእስልምና እምነት ተከታዮች በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅርና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን።
በድጋሚ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
!! ቢዳራ ከተማ 🌷🌷