03/11/2021
ጋዜጠኛው ክሪስቲያኖ ሮናልዶን እንዲህ ሲል ጠየቀው:-
ለምንድነው እናትህ አሁንም ከአንተ ጋር የምትኖረው? ለምን የራሷን ቤት አትገዛላትም?’
ክሪስቲያኖ መለሰ:- እናቴ የራሷን ህይወት መስዋዕት አድርጋ ነው እኔን ያሳደገችኝ፡፡ ራቴን በልቼ እንድተኛ ፆሟን ታድር ነበር፡፡ ገንዘብ የሚባል ነገር ጭራሽ አልነበረንም፡፡ የመጀመሪያውን የእግር ኳስ ትጥቄን አሟልቼ እንድጫወት በሳምንት ሰባት ቀን፤ ቀን እና ምሽቱን ጽዳት ሠራተኛ ሆና አሳልፋለች፡፡ የኔ ጠቅላላ ስኬት ለእሷ የተሰጠ መታወሻ ነው፡፡ እኔ በህይወት እስካለሁ ሁልጊዜም ከጎኔ ትኖራለች፡፡ ከእኔ ማግኘት ያለባትን ሁሉ እሰጣታለሁ:: መሸሸጊያዬና የህይወቴ ታላቋ በረከት ናት::
ክብር ለእናቶች❤️❤️❤️