18/04/2025
ከዘጠኙ አበይት በአላት አንዱ ስቅለት ሲሆን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአለም ቤዛ ሊሆን መከራ የተቀበለበት፣ስለሃጢአታችን በቀራንዮ ኮረብታ በእፀ መስቀል ላይ ስጋውን የቆረጠበት፣ደሙን ያፈሰሰበት ራሱን ስለእኛ አሳልፎ የሰጠበት እለት ነው:: የሚከበረውም በስግደት፣ በፆም፣ በፀሎት፣ በንባብና በትምህርት ነው፡፡ "አምላክ አለምን ከፈጠረበት ጥበቡ ይልቅ ሰው ሆኖ አለሙን ያዳነበት ጥበቡ ይበልጣል" እንዲል የሰው ልጅ በበደለና ባልታዘዘ ጊዜ "እሱን የማትሰማ ነፍስ ትሞታለች" እንደተባለ ዘዳ 18፤15 የሃጢአት ደመወዝም ሞት ነውና ሰው የስጋ ሞትንና የነፍስ ሞትን አገኘ፡፡ ይህንንም ሞቱን ኢየሱስ ክርስቶስ በሞቱ የገደለው::
እኛ ልጆቹን ሁሉ ከሞት ወድ ህይወት ከድቅድቅ ጨለማ ወድ ብርሃን አፈለሰን::
#ተሰቀለ #ሞተ
1. የእኛን ሞት ለመሞት፡፡ ሮሜ 5፣15
2. ፈውስን እናገኝ ዘንድ ፡፡ ኢሳ 53፣5
3. 7ነትን እንወርስ ዘንድ መርገማችንን ወስዶ ተሰቀለ፡፡ ዘዳ 21፣23
4. የእኛን የበደል ቅጣት እርሱ ሊቀጣ፡፡ ኢሳ 53፣6
#በሞቱም
1. ህይወትን አግኝተናል- ሞት ነግሶብን ነበርና ያጣነውን ህይወት አገኘን፡፡ 1ቆሮ 5፣12
2. የህይወትን ምግብ አግኝተናል- ስጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ህይወት አለው፡፡ ዮሃ 6፣53
3. ሰላምን አግኝተናል- "ሰላምን እተውላችሁ፣ሰላሜን እሰጣችሁ..." የሐ 14:27
4. አዲስ ሰው ሆነናል- "ከእንግዲህ ወዲያ ለሃጢአት እንዳን7ዛ የሃጢአት ስጋ ይሻር ዘንድ አሮጌው ሰውነታችን ከእርሱ ጋር እንደተሰቀለ እናውቃለን። ሮሜ 6፣6
5. ታርቀናል- "ጠላቶቹ ሳለን ከእግዚአብሄር ጋር በልጁ ሞት ታረቅን.." ሮሜ 5፣10፡፡
በነፃነት ልንኖር ነፃ ያወጣንን ጌታ በማሳዘን እና ፍሬ ቢሶች በመሆን ዳግም በባርነት ቀንበር እንዳንያዝ እግዚአብሄር ይርዳን::