Mihur aklil woreda revenue authority branch office

Mihur aklil woreda revenue authority branch office ስለ ግብርና ታክስ

21/10/2021

ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብርን ቀንሶ ስለማስቀረት 1ከመቀጠር ከሚገኝ ገቢ ላይ ግብርን ቀንሶ ማስቀረት ።ማንኛውም ቀጣሪ ከመቀጠር ከሚገኝ ገቢ ላይ ግብር ስለመጣል በተደነገገው መሰረት የቅጥር ገቢ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ለተቀጣሪው በሚከፍልበት ጊዜ በሚገኝ ገቢ ላይ ተፈፃሚ በሚሆኑ መጣኔዎች መሰረት በእያንዳንዱ የክፍያ ጊዜ መከፈል የሚኖርበትን የገቢ ግብር ከጠቅላላው ክፍያ ላይ ቀንሶ የማስቀረት ግዴታ አለበት:: ።ቀጣሪውተቀጣሪው ከአንድ በላይ የሆነ ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ እንዳለው ያወቀና ሌላው ቀጣሪ በጠቅላላው የተቀጣሪው ገቢ ላይ ተመስርተው የገቢ ግብሩን ቀንሰው እንደማያስቀሩ ያወቀ እንደሆነ ቀጣሪው የተቀጣሪውን ገቢ በማጠቃለል የገቢ ግብር ቀንሶ የማስቀረት ግዴታ አለበት:: ።ቀጣሪው ለተቀጣሪው ከሚከፍለው ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ላይ ግብር ቀንሶ የማስቀረት ግዴታው ለሰራተኛው ከሚፈፅማቸው ክፍያዎች ላይ በቀጣሪው ተቀናሽ መደረግ ካለባቸው ሌሎች ግዴታዎች ቅዲሚያ ይኖረዋል::

21/10/2021

ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብርን ቀንሶ ስለማስቀረት 1ከመቀጠር ከሚገኝ ገቢ ላይ ግብርን ቀንሶ ማስቀረት ።ማንኛውም ቀጣሪ ከመቀጠር ከሚገኝ ገቢ ላይ ግብር ስለመጣል በተደነገገው መሰረት የቅጥር ገቢ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ለተቀጣሪው በሚከፍልበት ጊዜ በሚገኝ ገቢ ላይ ተፈፃሚ በሚሆኑ መጣኔዎች መሰረት በእያንዳንዱ የክፍያ ጊዜ መከፈል የሚኖርበትን የገቢ ግብር ከጠቅላላው ክፍያ ላይ ቀንሶ የማስቀረት ግዴታ አለበት:: ።ቀጣሪው ተቀጣሪው ከአንድ በላይ የሆነ ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ እንዳለው ያወቀና ሌላው ቀጣሪ በጠቅላላው የተቀጣሪው ገቢ ላይ ተመስርተው የገቢ ግብሩን ቀንሰው እንደማያስቀሩ ያወቀ እንደሆነ ቀጣሪው የተቀጣሪውን ገቢ በማጠቃለል የገቢ ግብር ቀንሶ የማስቀረት ግዴታ አለበት:: ።ቀጣሪው ለተቀጣሪው ከሚከፍለው ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ላይ ግብር ቀንሶ የማስቀረት ግዴታው ለሰራተኛው ከሚፈፅማቸው ክፍያዎች ላይ በቀጣሪው ተቀናሽ መደረግ ካለባቸው ሌሎች ግዴታዎች ቅዲሚያ ይኖረዋል::

05/10/2021

ማስታወቅያ ለደረጃ "ሀ" ግብር ከፋዮች በሙሉ የደረጃ "ሀ" ግብር ከፋዮች የግብር መክፈያ ወቅት ከሀምሌ1እስከ ጥቅምት30 ድረስ መሆኑን ይታወቃል:: በዚህም መሰረት የወረዳችን የደረጃ"ሀ" ግብር ከፋዮች በሙሉ ጊዜው ሳያልፍ የግብር ግዴታችሁን እንድትወጡ የም\አ\ወ\ገ\ቅ\ፅ\ቤት በጥብቅ ያሳስባል::

06/07/2021

ማስታወቂያ
የም/አ/ወ ግብር ከፋዮች በሙሉ ለግብር መክፈያ ወቅት በሠላም አደረሳችሁ እያልን አሁን ጊዜው ለጋራ ልማታችን ሁላችንም የሚጠበቅብንን የድርሻችን የምንወጣበት ጊዜ በመሆኑ
የደረጃ "ሐ "ግብር ከፋዮች ከሐምሌ1 እስከ ሐምሌ 30/2013 ድረስ
የደረጃ "ለ"ግብርከፋዮችከሐምሌ1እስከፖጉሜ5/6 2013 ድረስ
የደረጃ "ሀ "ግብር ከፋዮች ከሐምሌ1እስከ ጥቅምት30/2014ዓ.ም ድረስ የ2013ዓ.ም ዓመታዊ ግብራችሁ በመክፈል የዜግነት ግዴታና ሃላፊነት በወቅቱ እንድትወጡ የም/አ/ወ/ገ/ባ/ቅ/ጽ/ቤት በአክብሮት ያሳስባል፡፡
ግብር በወቅቱ መክፈል ያዋቂነት ምልክት ነው፡፡
ሰኔ 29/2013ዓ.ም

24/06/2021
26/05/2021

ማስታወቂያ
የተከበራችሁ የሀዋርያት ከተማ ነዋሪዎች በሙሉ ማንኛውም ግለሰብም ሆነ ድርጅት ባገኘው ገቢ ላይ ግብር መክፈል እንዳለበት በገቢ ግብር አዋጅ 165/2009 ላይ ተደንግጎል፡፡ በመሆኑም ውዝፍና የዘመኑ የሊዝ ጨረታ ክፍያ እና የጣራና ግድግዳ ያልከፈላችሁ
እጅግ ቢዘገይ እስከ ሰኔ30/2013 ዓ.ም ጽ/ቤቱ ድረስ በአካል በመቅረብ ግዴታችሁን እንድትወጡ የም/አ/ወ/ገ/ባ/ቅ/ጽ/ቤት በጥብቅ ያሳስባል:: በዚህም መሰረት ግዴታችሁን ባልተወጣችሁ ነዋሪዎች ከፍያለ ወለድና ቅጣት እንደሚኖረው አውቃችሁ በተቀመጠለት ጌዜ ግዴታችሁን እንድትወጡ እናሳስባለን፡፡
ግንቦት 18/2013ዓ.ም

17/05/2021

የሒሳብ መዝገብ መያዝ ያለበት ማነው?
፨በክልሉ የገቢ ግብር አዋጅ አንቀጽ 80 መሠረት የሠንጠረዥ "ለ" እና የሠንጠረዥ "ሐ" ግብር የመክፈል ኃላፊነት ያለበት የደረጃ "ሀ" ፣ "ለ" እና በፈቃደኝነት የሒሳብ መዝገብ የሚይዝ የደረጀ" ሐ"ግብር ከፋይ እንዲሁም የካፒታል ሀብት በማስተላለፍ ጥቅም የሚያገኝ ሰው የሒሳብ መዝገብ መያዝ አለበት፡፡

11/05/2021

የታክስ መርሆች
፦የመክፈል አቅም(ability to pay)
፦ተመጣጣኝነት(fairness)
፦ፍትሀዊነት(equitability)
፦ተገማችነት(predictability)
፦ወጥነት(consistency)
፦ግልጽነትና አመቺነት(clarity&simplicity)

Address

Mihur Aklil
Wolkite
1234

Telephone

3430750

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mihur aklil woreda revenue authority branch office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share