መገናኛ መረዳጃ

መገናኛ  መረዳጃ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from መገናኛ መረዳጃ, Business service, addis abeba, London.

ተማሩ  ሳትማሩ  እየገባችሁ  ኢትዮጵያ  ሗላ ቀር  እና ድሃ አደ!!ኢትዮ ቴሌኮም የአንድ ብሄር ተወላጆች በበላይነት እንዲቆጣጠሩ እየተደረገ መሆኑን ሰራተኞች ገለፁ።================...
05/07/2023

ተማሩ ሳትማሩ እየገባችሁ ኢትዮጵያ ሗላ ቀር እና ድሃ አደ!!ኢትዮ ቴሌኮም የአንድ ብሄር ተወላጆች በበላይነት እንዲቆጣጠሩ እየተደረገ መሆኑን ሰራተኞች ገለፁ።
================================================

ሾልኮ ኦ ኤም ኤን የደረሰው የድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት የአመራር የብሄር ስብጥር መረጃም ከአንድ ብሄር የመጡ አመራር ሰንሰለት ፈጥረው የሚሰሩበት ድርጅት መሆኑንም አመላክቷል።

በኢትዮ ቴሌኮም በዋና ስራ አስፈፃሚ የሚመመራ ሲሆን፣ ከዋና ስራ አስፈፃሚ ቀጥሎ ቺፍ፣ ዳሬክተር፣ ማናጀር፣ ሱፐርቫይዘር የሚባሉ የአመራር እርከን ይገኛሉ።

ሰሞኑን ዋና መስሪያ ቤት ውስጥ ባለው የአመራር እርከን ላይ ባለው የብሄር ተዋፅዖ አስመልክቶ የተደረገው ጥናት ውጤት ለኦ ኤም ኤን ደርሷል።

ጥናቱ እንዳመለከተው ከዋና ስራ አስፈፃሚ ቀጥሎ ባለውና ቺፍ በመባል የሚታወቀው የአመራር ቦታ 10 በአማራ ተወላጅ፣ 6 በኦሮሞ ተወላጅ፣ 2 በካምባታ ተወላጅ እንዲሁም 1 በትግራይ፣ በጉራጌና በጋሞ ተይዟል።

ምክትል ቺፊ የሚባለው የአመራር ቦታ ደግሞ 4ቱ በአማራ ተወላጆች ተይዟል።

ዳይሬክተር የሚባል የሚባል ቦታ ደግሞ 57 በአማራ ተወላጅ፣ 11 በኦሮሞ ተወላጅ፣ 9 በትግራይ ተወላጅ፣ 5 በጉራጌ ተወላጅ፣ 3 በስልጤ፣ 1 በፋር ተወላጅ መያዙን ሰነዱ አመላክቷል።

በሰነዱ መሰረት የማናጀርነት ቦታን በተመለከተ ደግሞ 242 በአማራ ተወላጆች የተያዘ ሲሆን 50 በኦሮሞ፣ 26 በትግራይ፣ 6 በጉራጌ፣ 2 በስልጤ እንዲሁም አንዳንድ በጋሜ፣ በሀረሪ፣ ሀዲያ፣ ዎላይታ ተይዘዋል።

በአጠቃላይ ድምሩ ኢትዮ ቴሌኮም ውስን ቦታ ላይ ያለው የአመራር ስብጥር 313 የአማራ ተወላጆች ሲሆኑ፣ 67 የአሮሞ፣ 36 የትግራይ፣ 12 የጉራጌ፣ 5 የስልጤ፣ 2 የጋሞ፣ 2 የካምባታ ተወላጆች እንደሆኑ ተመላክተዋል።

አንዳንድ የአፋር፣ የሀረሪ፣ የሀድያና ዎላይታ ተወላጆችም እንዳሉ ሰነዱ አመላክቷል።

ጉዳዩን በተመለከተ ኦ ኤም ኤን ያነጋገራቸው የድርጅቱ ሰራተኞች በበኩላቸው ድርጅቱ ውስጥ የተዘረጋው የአንድ አካባቢ ሰዎች የአመራር ሰንሰለት ድርጅቱን የዘረፋና ምዝበራ ማእከል አድርጓል ብለዋል።

በአከባቢ በመደራጀት የተፈጠረው የአመራር ሰንሰለት ሁሉም ብሄሮችና ብሄረሰቦች በድርጅቱ ውስጥ በፍትሃዊነት እንዳይሳተፉ አድርጓል ይላሉ።

የሀገሪቷ ተቋማት ሁሉንም ህዝቦች መምሰል እያለባቸው ዛሬም እንደአሮጌ ዘመን በአንድ አካባቢ ሰዎች በበላይነት እንዲያዙ ማድረግ አሳዛኝ ነው ብለዋል።

በዚህ ላይ በድርጅቱ ውስጥ የተንሰራፋው የሙስናና ዘረፋ ሰንሰለት በጊዜ መላ ካልተበጀለት አደጋው የከፋ መሆኑን ተናግረዋል።

ኦ ኤም ኤን ያነጋገረው ማህበራዊ ኣንቂ በበኩሉ የአማራ ፅንፈኛ የፖሊትካ ቡድኖች በፌዴራል ተቋማትና በፊንፊኔ ከተማ ውስጥ ያለውን ጉድ ለመሸፋፈን አስቀድሞ ሌላውን በውሸት ይወነጅላሉ ብሏል።

በፌዴራል መንግስቱና በፊንፊኔ ከተማ የመንግሥት መዋቅር ውስጥ የያዙትን የበላይነትና ኢፍትሃዊ ተጠቃሚነታቸውን ለመከላከል ቀድመው ተረኛ በማለት የኦሮሞ ህዝብን ባልዋለበት ለመውቀስ እየሞከሩ ነው ይላሉ።

ለእነዚህ ፅንፈኛ ቡድኖች እኩልነትና ፍትሃዊ ተሳታፊነት ተሸናፊነት ይመስላቸዋል ብሏል።

ይህ በፌዴራል መንግስቱና በፊንፊኔ ከተማ የመንግሥት መዋቅር ውስጥ የሚስተዋለው ችግር በአፋጣኝ መፈታት እንዳለበት መክረዋል።

22/05/2023

"ርዕሰ አንቀጽ"

• ትኩረት ለሲኖዶሱ

"…ትናንት ግንቦት በ11/2015 ዓም ብቻ በምዕራብ ወለጋ በሆሮ ጉዱሩ ብዙ ወረዳዎች በኦነግ ሸኔ ተይዟል። አባቦ ጉዱሩ፣ ጉዱሩ ወረዳ ኮምቦልቻ፣ ዓባይ ጮመን ወረዳ፣ የፊንጫ ኃይል ማመንጫ ወዘተ በኦነግ ሸኔ ቁጥጥር ስር እንዲሆኑ ተደርገዋል። በተቆጣጠሯቸው ከተሞችና ወረዳዎችም የግልና የመንግሥት ባንኮች፣ የመንግሥት ቢሮዎች፣ የግለሰብ ሱቆች በሙሉ ተዘርፈዋል ተብሏል። ይኸው ዛሬ ደግሞ የፊንጫ የኃይድሮ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫው እና የስኳር ፋብሪካው በኦነግ ሸኔ ቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጓል።

"…አቶ ስንታየሁ ደምሴ የተባሉ የ80 ዓመት ሽማግሌን አንተ ጎጃሜ ብለው በአደባባይ እንደረሸኗቸው ተነግሯል። ድሮ በኦሮሚያ ልዩ ኃይል፣ በፌደራል ፖሊስና በመከላከያ ይጠበቅ የነበረው የፊንጫ የኤሌክትሪክ ግድብ ሦስቱም ለቀው እንዲወጡ ከፌደራል ተነግሯቸው ግድቡንም የስኳር ፋብሪካውንም፣ ከተማውንም ለሸኔ አስረክበው መውጣታቸው፣ የከተማዋም አስተዳደሮችም ሸሽተው ወደ ሻምቡ መሄዳቸው ተረጋግጧል። የሚገርመው ነገር ከ2 ቀን በፊት የኦዳ ባንኩ የጨረቃ ጳጳሳቱ ፈጣሪ የቃልቻው ልጅ ዋሲሁን አመኑ ወደ ፊንጫ ሄዶ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ካህናቱን ሰብስቦ አስፈራርቶ እንደሄደና ከሁለት ቀን በኋላ ሸኔዎቹ ከተማዋን ሲቆጣጠሩ እዚያው ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሄደው ካህናቱን ሰብስበው "እናንት ጎጃሜዎች ምንአባታችሁ ልትሠሩ ሃገራችን መጣችሁ በማለት እርምጃ ሊወስዱባቸው የነበረ ሲሆን የከተማው ሕዝብ ግልብጥ ብሎ በመውጣት በስንት ተማጽኖ ለጊዜው ከሞት መትረፋቸው ነው የተነገረው። ዋሲሁን አመኑ አሁን አዲስ አበባ ተመልሶ አቡነ ሩፋኤል ጠርንፎ በመጪው ሰኞ የኦሮሙማው ጳጳሳት ሹመት በሲኖዶሱ እንዲጸድቅ እየተጋጋጠ ነው። አይ ዋሲሁን። የቃልቻ ልጅ።

"…በፊንጫ የሠራዊቱ አዛዥም "አጋዥ ኃይል ከፌደራል መንግሥቱ የጠየቀ ቢሆንም ከእነ ብራኑ ጁላ፣ ይልማ መርዳሳ ምንም ዓይነት ምላሽ የሚሰጠው ባለማግኘቱ ለወታደሮቹ "በዚህ ግማታም ሴራ ሕይወታችሁ በከንቱ እንዳይጠፋ የቻላችሁትን ያህል ሩጣችሁ ሽሹ፣ ወደኋላም አፈግፍጉ" ሲል እንደነበርና ኋላ ላይ አዛዡ ራሱ ሳይመታ እና ሳይሞት አልቀረም ተብሏል። ምዕራብ ሸዋ፣ ምስራቅ ሸዋ ናዝሬት፣ ደብረ ዘይት፣ ወለንጪቲ፣ ሶደሬ መስመር፣ ዓለምጤና፣ እዚህ ሰበታ ወጨጫ ተራራውን ይዞ ሸኔ እንዲሰፍር ተደርጓል። ይሄን ሁሉ መንግሥት ያውቃል። ደብረዘይት እና ሞጆ ዱከም ከፌደራል ፖሊስ ጋር መታኮስ ከጀመረ ምን ቀረ? መንግሥት ተብዬው አፍንጫው ስር ያለው ሸኔን ንቆ በሰላም ሃገር እያረሰ፣ እየቀደሰ የተቀመጠውን ፋኖን ካላጠፋሁ ብሎ ያዙኝ ልቀቁኝ ይላል። ይሄ እንዳለ ሆኖ ትኩረት ግን ወደ ሲኖዶሱ እንዲሆን እመክራለሁ።

"…አሁን ነገሮች የባሰ እየከበዱ ነው የሚመጡት። የትግሬዋ ሕወሓት በሚቀጥለው ወር የግድ ወልቃይትና ራያን መረከብ አለብኝ ብላ ሄጵ ማለቷ እየተነገረ ነው። አርሚ ምንትስ፣ አርሚ ቅብጥርስ የሚባሉ የእሳት ራት ሟቾች ወደ ዐማራ ድንበር እያስጠጉ ነው። እናም በዚያ በኩል ጦርነት አይቀሬ ነው የሚሉ አሉ። ለዚህ ደግሞ የኦሮሙማው መንግሥት ትግሬዎቹን እንድንረዳችሁ ወልቃይት እና ራያን እንድናስረክባችሁ ከፈለጋችሁ እናንተም ፓትርያርኩን አሳምናችሁ የኦሮሙማ ጳጳሳት ሹመቱ እንዲጸድቅ አስደርጉልን። በእኛ በኩል አፍርሱ ያላችሁንን የዐማራ ልዩ ኃይልን አፍርሰንላችኋል፣ ፋኖን እየተዋጋነው ነው። እናንተ ወልቃይት እና ራያን እንደምትፈልጉት ሁሉ እኛም ጵጵስናውን የግድ እንፈልገዋለንና በሰጥቶ መቀበል መርህ እናንተም ይሄን ፈጽሙልን እንዳሏቸው ነው የተሰማው።

"…ነገሩ የተበላሸ

22/05/2023

👆👆 ከላይኛው የቀጠለ። …ይገመታሉ) በድምፅ ብልጫ ያወርዱና አዲስ የኦቦሌሶ ፓትርያርክ ይመርጣሉ። ከዚያ መፈንቅለ ዐማራ ያሉት፣ መፈንቅለ ኦርቶዶክስም በሰላም ይጠናቀቃል። ከዚያ ወሀቢ እና ፕሮቴስታንት በቀላሉ ቤተ ክርስቲያኒቱን ይረከቧታል። ይኸው ነው የሚሉ መተርጉማንም አሉ።

"…ኦሮሙማው ከወዲሁ የውትወታ ወይም የሎቢ ሥራም እየሠራ ነው ተብሏል። የምሥራቅ ሸዋው አቡነ ጎርጎሬዎስን "እኛ ለ30 ዓመት የያዙትን ሃገረ ስብከት አንፈልግም። ምንም ትግሬ ቢሆኑ ወዳጃችን ነዎት። እናም በሰጥቶ መቀበል መርህ መሠረት እርስዎም ለትግራይም ለሃገረ ስብከትዎም ሲሉ ከእኛ ጎን ይሰለፉ፣ ፓትርያርኩንም ያሳምኑ ነው ተባሉ የሚባለው።" ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የወለጋ ሰው ናቸው። እስከ አሁን እያሳዩ ያለው አቋም ከዘረኝነት እሳቤ ውጪ ነው። አማናዊቷን ክርስቶሳዊት ቤተ ክርስቲያን እስከአሁን በዘር ከረጢት አልቀየሩም። አሁን ግን የእሬቻ በዓልን ከተቃወሙ ወዲህ የጤና መጓደል እንደሚታይባቸው እየተነገረ ነው። ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በብዙ ነገር አፋቸው እንዲለጎም መደረጉም ተሰምቷል። የጅማ ፍቅር ሀገረ ስብከታቸው በከድር ወይም በይቴ ጭሷ እንዳይቀማ በአቢይ ጓደኛ በቄስ ታጋይ መጠርነፋቸው ነው የሚሰማው።

"…የብፁዕ አቡነ ናትናኤል አቋም ብዙ ኦሮሞዎችን ያሳመነ ሆኖ መገኘቱ ብልፅግና መሰረተ ዐማራው አቡነ ሳዊሮስ፣ አመንዝራው ኤውሳጣቴዎስ፣ ወላዱ ዜናማርቆስ ላይ ተዘፍዝፎ የሕዝብ ድጋፍ መሠረቱን ከሚያጣ ለጊዜው በኦርቶዶክሳዊ አቋማቸው፣ በሕዝባዊ ቅቡልነታቸው፣ በዜመኛው በድምጣዊው ማኅሌታይ በወዳጄ በብፁዕ አቡነ ናትናኤል ላይ ቀልቡን ማሳረፉን የመረጠ ይመስላል ነው የሚባለው። ለዚህም ነው አቢይ አሕመድ ያንቆለጳጰሳቸው፣ ሽመልስ አብዲሳም "ይቅርታ ብፁዕ አባታችን እርስዎን እስከዛሬ አልረዳንዎትም፣ አልተረዳንዎትምም" አላቸው የተባለው።

"…የሚሾመው ኦሮሚኛ የሚናገር ሳይሆን በደም ጥራቱ 7 ወደላይ ኦሮሞ፣ 7 ወደ ጎን ኦሮሞ የሆነ ካልሆነ አንቀበልም። ከተቻለ ስሙም ብፁዕ አቡነ በዳሳ፣ መገርሳ፣ ፈይሳ፣ ሌሊሳ ካልሆነ አንቀበልም። ጴጥሮስ፣ ጳውሎስ የሚባል የአይሁድ ስም አንፈልግም ማለታቸው እነ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስን ፍሬን ሳያስይዝ አልቀረም። አቡነ ሳዊሮስ የሰሜን ሸዋ የመንዝ የደራ ዐማራ ናቸው። ኤውስጣቴዎስ በአሜሪካ ዩኒቨርሲቲ የተመዘገበ የዝሙት ቅሌት ሰርተፊኬቱ ደንቃራ ነው የሆነባቸው። አቡነ ዜና ማርቆስ ሚስታቸው በቅርቡ መሞቷ መነገሩ አንገታቸውን አስደፍቷቸው እንጂ ደንበኛው ሸኔ መሆን የሚያምራቸው ነበሩ። አቡነ ዜና ማርቆስ ጳጳስ ከመሆናቸው በፊት አይዋ አሰፋ ተብለው የሚጠሩ ኦሮሚኛ ተናጋሪ የደራ ዐማራ ናቸው።

"…አቡነ ሩፋኤል መሰረታቸው ጎንደር ነው። የሰባራ በባቡር የአራዳ ልጅ ናቸው። ከጥቁር ራስነት ወደ ምንኩስና የገቡትም በቅርብ ነው። ጵጵስና የተሾሙትም በጋምቤላ አስተዳዳሪ ማስፈራሪያ ደብዳቤ በሟቹ አባይ ፀሐዬ ዛቻ ነው። በጋምቤላ እንዲሾሙ የተፈለገውም በዚያ የነበሩ የትግራይ ባለሀብቶች፣ ኢንቨስተሮች በሊቀጳጳሱ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ስለተፈለገ ነበር። ወያኔ በጋምቤላ የሚሾም ጋምቤላዊ ኦርቶዶክስ መሆን አለበት በማለቷ፣ ጳጳሱ እነዚያን እያስጠመቁ የትግሬ ኢንቨስተር ጠባቂ እንዲያደርጉ ነው ያስመረጧቸው። ያኔ እኔ ዘመዴ ወዳጄ ሆነው እንዳይመረጡ በብርቱ ታግዬ "ጳጳስ ይሳደባል" ተብዬ መወቀሴም ይታወሳል። አሁን ያ ሰው ነው ሲኖዶሱን እያወከ ያለው።

"…አባ ሩፋኤል የአብነት ትምህርት የላቸውም። የክብር ጳጳስ በሉት። ስላልተማሩ ደፋር ናቸው። ያኔ ወያኔ እንደተጠቀመችባቸው ስለሚያውቁ ኦህዴዶችም አሁን ለእኛ አገልግለን ብለው ይዘዋ

12/05/2023

መንግስት በፖለቲካ አመለካከታቸውና በመንግስት አሰራሮች ላይ በሚያቀርቡት የፖለቲካ ትቺት ምክንያት፤ ወንድማችንን ዘሪሁን ገሰሰን ጨምሮ፥ በተለያዩ አካባቢዎች ያሰራቸውን የፖለቲካ እስረኞች በአስቸኳይ ከእስር እንዲፈታ እጠይቃለሁ።

ፓርቲ የመሰረትነው መንግስትን መቼና እንዴት መተቼት እንዳለብን ከራሱ ከመንግስት አቅጣጫ እየተቀመጠልን ለመንቀሳቀስ አይደለምና፥ በተለይም የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ በትንሹ የራሱን አባላት ደኅንነት የማስጠበቅ ግዴታውን በወጉ እንዲወጣም በአንክሮ እጠይቃለሁ።

አይጥና ድመት  አንድ ቀን  ታረቅና ከዛሬ ጀምሮ አብረን በሰላም በፍቅር በደስታ አብሮ መኖር ብቻ ነዉ ተባባሉ እና አንድ ቀን ድመት ልማዷ ሊለቃት አልቻለም እና ድመት አይጦችን ልትበላ  ሜዉ...
12/05/2023

አይጥና ድመት አንድ ቀን ታረቅና ከዛሬ ጀምሮ አብረን በሰላም በፍቅር በደስታ አብሮ መኖር ብቻ ነዉ ተባባሉ እና አንድ ቀን ድመት ልማዷ ሊለቃት አልቻለም እና ድመት አይጦችን ልትበላ ሜዉ ስትል አይጥ ምን ብትል መሰላችሁ እኛ አዉቀናል ጉርጓድ ምሰናል!!!

በምእራብ ኦሮሚያ በተለያዩ ሀገረስብከቶች የሚገኙ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ምእመናን የቤተክርስቲያኗ ሲኖዶስ በተቀመጠው ጉባኤ ከወራት በፊት የተሾሙትን 26 ኤጲስቆጶሳት ሹመት ማፅደቅ...
12/05/2023

በምእራብ ኦሮሚያ በተለያዩ ሀገረስብከቶች የሚገኙ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ምእመናን የቤተክርስቲያኗ ሲኖዶስ በተቀመጠው ጉባኤ ከወራት በፊት የተሾሙትን 26 ኤጲስቆጶሳት ሹመት ማፅደቅ እንዳለበት ገለፁ።

ኦ ኤም ኤን ያነጋገራቸው በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ፣ በምስራቅ ወለጋ፣ በምእራብ ወለጋ ሀገረስብከቶች የሚገኙ ምእመናን፣ ነባሩ ሲኖዶስ ለዘመናት ስከተል በነበረው የተበላሸ አሰራረ ቤተክርስቲያኗ ለጉዳት ተጋልጣ መቆየቷን ገልፀዋል።

ምእመናን በብዛት ከቤተክርስቲያኗ ሸሽተዋል፣ አብያተክርስቲያናት በብዙ ቦታ ተዘግተዋል ያሉት ምእመናኑ፣ ይህ የሆነው ደግሞ ነባሩ ሲኖዶስ በቤተክርስቲያኗ ውስጥ የነበረውን ብልሹ አሰራር ማስተካከል ባለመቻሉ እንደሆነ ተናግረዋል።

ይህን ችግር ለመፍታት በሶስቱ ብፁዓን አባቶች ተነሳሽነት ቋንቋን የሚችሉና የህዝቡን እሴት የሚያውቁ ኤጲስቆጶሳትን በመሾም የተጀመረው እንቅስቃሴ እጅግ ወሳኝ ምእራፍ ጅማሮ መሆኑን ገልፀዋል።

ሲኖዶሱ አሁን በተቀመጠው ጉባኤ የኤጲስቆጶሳቱን ሹመት በማፅደቅ ቤተክርስቲያኗን የገጠመው ችግር ለመፍታት የመፍትሄ አካል መሆን እንዳለበት ምእመናኑ ጠይቀዋል።

ህዝቡ በፈለገ ቋንቋ የማምለክና ቋንቋውን በሚችሉና እሴቱን በሚያውቁ አባቶች የመመራት መብቱ መከበር እንዳለበት ገልፀው፣ ይህን ለመፃረር መሞከር አግባብነት የለውም ብለዋል።

ኤርሚያስ መኩሪያ በመከላከያ ሰራዊት እና በደህንነት አባላት ታፈነ።በዛሬው ዕለት ግንቦት 4 ቀን 2015 ዓ.ም ከቤቱ በመውጣት ወደ መርካቶ እየተጓዘ በነበረበት ወቅት የመከላከያ ኮማንዶዎችና ...
12/05/2023

ኤርሚያስ መኩሪያ በመከላከያ ሰራዊት እና በደህንነት አባላት ታፈነ።

በዛሬው ዕለት ግንቦት 4 ቀን 2015 ዓ.ም ከቤቱ በመውጣት ወደ መርካቶ እየተጓዘ በነበረበት ወቅት የመከላከያ ኮማንዶዎችና የደህንነት አባላት አፈና እንደፈፀሙበት የአይን እማኞች ገልጸዋል።

ኤርሚያስ መኮንን በዛሬው ዕለት ወደ መርካቶ ሲጓዝ የነበረው ከወለጋ ተፈናቅለው በደብረብርሃን መጠለያ ካምፕ ለሚገኙ አማራዎ ምግብ እና ልብሶችን ለመግዛት እየተጓዘበት በነበረበት ወቅት መሆኑን ታውቋል።

ኤርሚያስ ሲያሽከረክረው የነበረውን መኪናውን ከደህንነት አባላት አንዱ እየነዳ የወሰደው ሲሆን እየሆነ ያለውን ለባለቤቴ ላሳውቅ ሲል ጥያቄ ቢያቀርብላቸውም ሊፈቅዱለት እንዳልቻሉ እና ነገ ትደውላለህ የሚል ምላሽ እንደሰጡት ቦታው ከነበሩ እማኞች ለማወቅ ተችሏል።

ኤርሚያስ መኩሪያ እስካሁን የት እንዳለ ለማወቅ አልተቻለም።

ቴወድሮስ
12/05/2023

ቴወድሮስ

ጋዜጠኞቹ ዳዊት በጋሻው እና ቴዎድሮስ አስፋው ነገ ግንቦት 4 ቀን 2015 ዓ.ም ከረፋዱ 4:00 ላይ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት ይቀርባሉ።

11/05/2023

የወገን ጥሪ፤ ከወገን ለወገን

ለሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት በሙሉ

ከአማራ ሕዝባዊ የሕልውና ትግል ጊዜያዊ አስተባባሪ ኮሚቴ የቀረበ ጥሪ

***

የሀገር መከላከያ ሠራዊት የኢትዮጵያ ብሄረሰቦች ውህድ ማንነት ነው፡፡ ጠባቂነቱም ለመላ ኢትዮጵያዊያን ነው፡፡ መከላከያ ሠራዊት ኢትዮጵያዊ መልክ ያለው ትልቅ ሀገራዊ ተቋም ነው፡፡ ተልዕኮውና ዓላማውም የኢትዮጵያን የግዛት አንድነት ማስከበር፤ ዳር ድንበሯ ታፍሮና ተከብሮ እንዲኖር ማድረግ እንጅ የፖለቲካ ቡድኖች መጠቀሚያ መሆን አይደለም፡፡

ነገር ግን የሀገር መከላከያ ሠራዊት የጥቂት የፖለቲካ ቁማርተኞች ጠባብ ዘረኛ ፍላጎት ማስፈጸሚያ ለማድረግ የሚደረጉ ጥረቶች #አሁንም #ቀጥለዋል፡፡ የዚህ ድምር ውጤት ለኢትዮጵያና ሕዝቦቿ እጅግ አደገኛ ነው፡፡

በተለይም በሕዝብ ትግል ትህነግ/ወያኔን መንቀል ከተቻለ በኋላ የተረኝነቱና የመዋቅራዊ ወረራው እውነታ ሳይዘነጋ፣ በሀገር መከላከያ ሠራዊት ውስጥ ለኢትዮጵያና ለሕዝቧ ሰላም፣ ለሉዓላዊነቷ፣ ለአንድነቷና ለዕድገቷ እስከ ሞት ድረስ የታመኑላት ውድና ጀግና ወታደራዊ አመራሮችና የሠራዊቱ አባላት እንዳሉት ሁሉ፤ ኢትዮጵያን የካዷት፣ ለጠባብ ዘረኛ ፍላጎታቸውና ለፖለቲካ ዓላማቸው ምስኪኑን የሠራዊት አባል ያስጨፈጨፉ እንዳሉ በሰሜኑ ጦርነት ታይቷል፡፡

ከኢትዮጵያ የውስጥ ጠላቶች ጋር ወግነው በገንዘብ ተገዝተው ሊያፈርሷት የተጉና በልጆቿ ንፁህ ደም ምድሯን ያጨቀዩ “የእናት ጡት ነካሽ” የሆኑባት የሠራዊቱ ወታደራዊ አመራሮች አሉ፡፡ ለዚህም የሰሜኑ ጦርነት ታሪካዊ ምስክር ነው።

እነዚህ ጥቂት ወታደራዊ አመራሮች የዐቢይ አሕመድ የግል ተላላኪ ሆነው የአማራን ሕዝብ ከሠራዊቱ ጋር ለማጋጨት ጥረት በማድረግ ላይ እንዳሉ በግልጽ በመታየት ላይ ነው፡፡

በአሁኑ ሰዓት "የአማራ ልዩ ኃይል ለተሻለ ግዳጅ እንደገና ማደራጀት" በሚል ሽፋን የአማራ ሕዝብ ራሱንና አገሩን ከጥቃት ለመከላከል በሕጋዊ መንገድ የታጠቀው አለፍ ሲልም በህልውና ጦርነቱ ወቅት 'ማርከህ ታጠቅ' የሚለውን የክልሉ መንግሥት መመሪያ ተከትሎ የማይተካ ሕይወቱን አሲዞ ከጠላት ማርኮ የታጠቀውን ትጥቅ ለማስፈታትና ጠባቂ ከለላ አልባ ለማስቀረት የተጀመረው መንግሥታዊ ሴራ ከማንም የተሰወረ አይደለም።

ዛሬ የአማራ ሕዝብ ኢትዮጵያን በወደደና ባከበረ በጠላትነት ተፈረጆ፣ በየደረሰበት እንደ መፃተኛ ተሳዶ፣ እንደ ባይተዋር ተቅበዝብዞ፣ ያለ በደሉ እንደ መስዋዕት በግ በየደረሰበት እየታረደ የሚገኝበት ወቅት ነው።

ስለሆነም ሕዝባችን የሱዳን ተስፋፊ ኃይል፣ የወያኔ የጦር ወረራ ተጨባጭ ስጋቶች እና የውስጥና የውጭ አደጋ ተጋላጭነት ያለበት በመሆኑ ተጨማሪ የሚታጠቀው እንጅ የሚፈታው ትጥቅ ሊኖር አይገባም።

ይልቁንም ከነባሩ ባህላችንና የሕዝባችን ሥነ-ልቦና አንፃር የአማራ ሕዝብ ትጥቅ ሀገርን ከጥበቃት ለመጠበቅ፤ ለወገን መከታ የሚውል እንጂ እንደወያኔና የዓላማው ወራሾች ኢትዮጵያዊ ወገን ላይ ጥቃት ለመክፈት አይደለም። በመሆኑም ይህን እውነታ የሠራዊቱ አባላት እንድትረዱን እንሻለን።

ስለሆነም የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባል የሆናችሁ በየደረጃው የምትገኙ የኢትዮጵያ ልጆች የሚከተለው የትግል ጥሪ ቀርቦላችኋል፦

የአማራ ህዝብ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ወሳኝ ደጀን፤ ቀኝ እጅ ነው። ይህንንም በሰሜኑ ጦርነት ከሠራዊቱ ጋር አብሮ በመውደቅም ሆነ አስተማማኝ ደጀን ሆኖ የሚያስፈልገውን በማቅረብ በተግባር አሳይቷል።

የሕዝባችን የህልውና ትግል አማራን #ለማጥፋት ከሚሰሩ የፖለቲካ ቁማርተኛ ከሆኑት ገዥዎች ጋር እንጂ፣ ከጭቁኑ ሰፊው የኢትዮጵያ ሕዝብ አብራክ ከወጣው ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጋር

Address

Addis Abeba
London

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when መገናኛ መረዳጃ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share