14/02/2025
የኦዲት መርሆዎች
ማንኛውም የኦዲት ተቋም የኦዲት ሥራውን በሚያከናውንበት ጊዜ የሚከተሉትን መሠረታዊ መርሆዎች መከተል ይገባዋል፡፡
-ማንኛውም ኦዲት ሲካሄድ የሂሳብና የኦዲት ደረጃዎችን መሠረት ማድረግ አለበት፤
-በኦዲቱ ሂደት ከፍተኛ የሙያና መልካም የግል ሥነ-ምግባር ሊጠበቅ በሥራም ሂደት ሊገለጽ ይገባል፤
-ሁሉም ኦዲቶች ነጻ በሆነ መንገድ ሊካሄዱና ሪፖርት ሊደረጉ ይገባል፤
-በኦዲት ወቅት የታዩ ትኩረት የሚሹ ማናቸውም ጉዳዮች በሪፖርቱ መካተት አለባቸው፤
-በኦዲቱ ሥራ የሚደረስባቸው መደምደሚያዎችና የሚቀርቡ የማሻሻያ ሃሳቦች ሁሉ በበቂ የኦዲት ማስረጃ ሊደገፉ ይገባል፤
-ኦዲተሮች በኦዲት የሥራ ሂደት ማንኛውንም መረጃ የማግኘት መብት አላቸው፡፡ ምንም ዓይነት ክልከላ ሊደረግባቸው አይገባም፡፡
-የኦዲቱን ዓላማ፣ ወሰን እንደዚሁም በኦዲቱ ሂደት የሚገኙ ግኝቶችን አስመልክቶ የመጨረሻ ሪፖርት ከመውጣቱ አስቀድሞ ከኦዲቱ ተደራጊው ጋር በቂ ውይይት መደረግ አለበት፡፡