16/05/2026
በላይነህ ክንዴ ግሩፕ 3ተኛ ዘር ሰልጣኞችን አስመረቀ።
ግንቦት 8/2018 ዓ.ም
በላይነህ ክንዴ ግሩፕ በገላ መኪና መገጣጠሚያ ለ3 ወራት በአውቶሞቲቨ ዘርፍ በ3ተኛ ዙር ያሰለጠናቸውን ወጣቶች በዛሬው እለት አስመርቋል።
በምረቃው ላይ የተገኙት የበላይነህ ክንዴ ኮርፖሬት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ደቅሲወስ በዛብህ እንደገለጽት ቢኬጂ በአውቶሞቲቨ ዘርፍ የሚታየውን የሰለጠነ የሰው ሀይል ችግር ለመቅረፍ በገላንና በደብረ ብርሃን መኪና መገጣጠሚያዎቹ ሰልጣኞችን በመቀበል በተግባራዊ ስልጠና በመስጠት ሀገራዊ ሚናውን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል።
የበላይነህ ክንዴ ሜታል ኢንጂነሪግ ስራ አስፈጻሚ አቶ በሱፍቃድ ሸዋዬ በበኩላቸው መኪና መገጣጠሚያው የተግባር ስልጠና ሰጥቶ ከማስመረቅ ባለፍ ከፍተኛ ውጤት የሚያስመዘግቡትን በመቅጠር የስራ እድል በመፍጠር ላይ ይገኛል ብለዋል።
የሸገር ከተማ አስ /ቴ/ሙ/ኤክስቴንሽን ዳይሬክተር አቶ ባልቻ ሄርጳ በበኩላቸው ቢኬጂ ከቴክኒክና ሙያ የተመረቁ ተማሪዎችነእ ተቀብሎ የተግባር ስልጠና በመስጠትና ለስራ ብቁ በማድረግ ለሌሎች ፋብሪካዎችም በአርኣያነት የሚጠቀስ ተግባር እያከናወነ ነው ብለዋል።
ቢኬጂ በደብረብርሃንና በገላን ባሉ መገጣጠሚያዎቹ በአራት ዙሮች ከ150 በላይ የሚደርሱ ወጣቶች በ ማስልጠና ለስራ ዝግጁ አድርጓል።
ቢኬጂ
የታታሪዋ ኢትዮጵያ ተምሳሌት