Belayneh Kindie Group

Belayneh Kindie Group This is the official Facebook home page of Belayneh Kindie Group. join us! Addis Ababa, Ethiopia

BK Business Group is one of Ethiopia's leading corporate groups, with interests include Import, export, transport, hotel, rental of construction materials, domestic business Investment and sales of a variety of products and services within and abroad. Website: https://bkgenterprises.com/
e-mail: [email protected]

This Is our only Official Social Media Platform as of now.

እንደምርጫዎአዳዲስ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ከቢኬጂቢኬጂየታታሪዋ ኢትዮጵያ ተምሳሌት
25/08/2026

እንደምርጫዎ
አዳዲስ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ከቢኬጂ

ቢኬጂ
የታታሪዋ ኢትዮጵያ ተምሳሌት

ግሪን አዲስ ትራንስፖርት በ2018 በጀት አመት ከፍተኛውጤት ላስመዘገቡ ሰራተኞቹ እወቅና ሰጠ ።ነሀሴ 17/2018 ዓ.ም   አንድ መቶ በኤሌክትሪክ ሀይል የሚንቀሳቀሱ የከተማ አውቶብሶችን በአ...
23/08/2026

ግሪን አዲስ ትራንስፖርት በ2018 በጀት አመት ከፍተኛውጤት ላስመዘገቡ ሰራተኞቹ እወቅና ሰጠ ።

ነሀሴ 17/2018 ዓ.ም
አንድ መቶ በኤሌክትሪክ ሀይል የሚንቀሳቀሱ የከተማ አውቶብሶችን በአዲስ አበባ በማስተዳደር ላይ የሚገኘው ግሩን አዲስ ትራንስፖርት በ2018 በጀት አመት የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ ሰራተኞቹን እወቅና ሰጥቷል።
በእውቅና ዝግጂቱ ላይ የተገኙት የግሪን አዲስ ትራንስፖርት ቦርድ ሰብሰባ አቶ በላይነህ ክንዴ ባስተላለፍት መልዕክት ግሪን አዲስ በአጭር ጊዜ ውስጥ በተገልጋዬቹ ዘንድ የፈጠረውን ተቀባይነት ለማስቀጠል ሁሉም ሰራተኛ ተሳፉሪዎችን ዝቅ ብሎ ማገልገልና የተቀላጠፈ አገልግሎት መስጠት ቅድሚያ መስጠት ተገቢ ነው ብለዋል ።
ሌላው በእውቅና መርሀግብሩ የተገኙት የአዲስ አበባ ትራስፖርት ም/ቢሮ ሀላፊና የግሪን አዲስ የቦርድ አባል አቶ ዳኛቸው ሽፈራው በበኩላቸው ግሪን አዲስ ትራንስፖርት በአዲስ አበባ ከተማ ለተጀመረው ዘመናዊ ትራንስፖርት ጉዞ በሞዴልነት አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ሲሆን ከተማ አስተዳደሩ ዘርፍን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል ።
የትናንትናው ቬሎሲት የዛሬው ግሪን አዲስ በ2018 በጀት አመት ከአርባ ሚሊዬን በላይ ተሳፋሪዎችን በማጓጓዝ ተገቢ አገልግሎት መስጠቱ በዝግጂቱ ላይ ተገልጻል።

ቢኬጂ
የታታሪዋ ኢትዮጵያ ተምሳሌት

ምቹ፣ ዘመናዊና አነስተኛ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ከቢኬጂለተጨማሪ መረጃ 09 04 77 55 7709 05 77 55 77 ይደውሉ      አልያም አራት ኪሎ አልማ ህንፃ   የሚገኘው የሽያጭ ...
18/08/2026

ምቹ፣ ዘመናዊና አነስተኛ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ከቢኬጂ

ለተጨማሪ መረጃ

09 04 77 55 77
09 05 77 55 77 ይደውሉ
አልያም አራት ኪሎ አልማ ህንፃ የሚገኘው የሽያጭ ክፍላችን ጎራ ይበሉ ።

ቢኬጂ
የታታሪዋ ኢትዮጵያ ተምሳሌት

ሎጎ ሀይቅ ሪዞርትየልጆች  ደስታ  መፍጠሪያ                   ጎራ ይበሉቢኬጂየታታሪዋ ኢትዮጵያ ተምሳሌት
16/08/2026

ሎጎ ሀይቅ ሪዞርት
የልጆች ደስታ መፍጠሪያ
ጎራ ይበሉ
ቢኬጂ
የታታሪዋ ኢትዮጵያ ተምሳሌት

የምስራችበኤሌክትሪክ ሀይል የሚንቀሳቀሱ የህዝብ ተሽከርካሪዎች  በሀገር ውስጥ በመገጣጠም ለደንበኞቹ  በማስረከብ ሰመ ጥር የሆነው ቢኬጂ  አሁን ላይ አነስተኛ  ተሸከርካሪዎችን በስፍት  ማቅረ...
16/08/2026

የምስራች
በኤሌክትሪክ ሀይል የሚንቀሳቀሱ የህዝብ ተሽከርካሪዎች በሀገር ውስጥ በመገጣጠም ለደንበኞቹ በማስረከብ ሰመ ጥር የሆነው ቢኬጂ አሁን ላይ አነስተኛ ተሸከርካሪዎችን በስፍት ማቅረብ ጀምሯል ።
እጂግ ዘመናዊ ፈጣንና ምቹ አነስተኛ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን ሲፈልጉ ወደ ቢኬጂ ጎራ ይበሉ ።

ለተጨማሪ መረጃ

09 04 77 55 77
09 05 77 55 77
09 07 77 55 77 ላይ ይደውሉ።

ቢኬጂ
የታታሪዋ ኢትዮጵያ ተምሳሌት

ለሀገራችን ተስማሚ የሆኑ እጂግ ዘመናዊ ሀገር አቋራጭ  አወቶብሶቸን ቢኬጂ ደብረ ብርሀን  በሚገኘው ፉብሪካው በስፋት እየገጣጠመ ነው።ቢኬጂየታታሪዋ ኢትዮጵያ ተምሳሌት
15/08/2026

ለሀገራችን ተስማሚ የሆኑ እጂግ ዘመናዊ ሀገር አቋራጭ አወቶብሶቸን ቢኬጂ ደብረ ብርሀን በሚገኘው ፉብሪካው በስፋት እየገጣጠመ ነው።

ቢኬጂ
የታታሪዋ ኢትዮጵያ ተምሳሌት

የሀገራችንን የህዝብ ትራንስፖርት ችግር ለመቅረፍ ቢኬጂ በትኩረት እየሰራ ነው።ቢኬጂየታታሪዋ ኢትዮጵያ ተምሳሌት
13/08/2026

የሀገራችንን የህዝብ ትራንስፖርት ችግር ለመቅረፍ ቢኬጂ በትኩረት እየሰራ ነው።

ቢኬጂ
የታታሪዋ ኢትዮጵያ ተምሳሌት

የቅዳሁድ ወግ - በሀይቅ በኩል    በተስፋዬ ይመር ( ወርጣዬ)     ከሎጎ ሀይቅ ሪዞርት ጉብኝት በኃላ የተፃፈ………………. ..,,,,"ሀይቅ" ስል ከደሴና ኮምቦልቻ ከተሞች ጋር አጣምሬ ነው...
09/08/2026

የቅዳሁድ ወግ - በሀይቅ በኩል
በተስፋዬ ይመር ( ወርጣዬ)
ከሎጎ ሀይቅ ሪዞርት ጉብኝት በኃላ የተፃፈ
………………. ..,,,,

"ሀይቅ" ስል ከደሴና ኮምቦልቻ ከተሞች ጋር አጣምሬ ነው፣ ከአምባሰል፣ ተሁለደሬና ወረባቦ ወረዳዎች እንዲሁም በቆላው በኩል ሀብሩ ወረዳ ነጥዬ አይቼ አይደለም - እስከአፋርና ወደብ የሚዘረጋ መገናኛ አድርጌ ነው የማያት፣ ቀጠናውን የምትወክል መሰባሰቢያ / Melting pot / አድርጌ ነው የማስባት። የምስራቅ አፍሪካ ዋና ከተማ እያልኩ አሽኮረምማታለሁ።
ኢኢለዚህ አንዱ ምክንያቴ ታሪክና ስልጣኔ ነው። ሁለተኛው ኃይማኖት፣ ሶስተኛው ባህላዊ መገለጫዎችና አራተኛው የተፈጥሮ ፀጋ ነው።
የአክሱም ስልጣኔ ያከተመው፣ የአክሱም የመጨረሻው ንጉስ ድልን ነዓድ በዚሁ አካባቢ ደማሞ በተባለ ተራራ ላይ ነው። 32x40 የሆነ የንጉሱ ቤተመንግስት፣ መቃብሮችና በወቅቱ ከቤተመንግስቱ ጎን አሰርቶት የነበረው ቤተክርስቲያምም ዛሬም እየተቀደሰበት ነው።
ቤተመንግስቱ የህንፃ ቅሪት ብቻ አይደለም የተወልን። ሞሰበወርቅ የተባለችው የንጉስ ድልነዓድ ልጅን የንጉሱ ባለሟል የነበረው መራ ተክለኃይማኖት ከንጉሱ ፊልም በሚወጣው መልኩ ለትዳር ይሁንታን አግኝቶ ወደላስታ የወሰዳት በኋላም እነዣንስዩምን ወልደው፣ ቅዱስ ላሊበላም Sileshi Girma ተወልዶ ዛጉዬም ስርወመንግስትም የፀናው መነሻው ከሀይቅ ነው። በዚህም የአክሱምና የዛጉዬ ስርዓቶች ሽግግር ያደረጉባት ደሴት ያደርጋታል።
ቤተክርስቲያኑና ቤተመንግስቱ ብቻ ሳይሆን በሀይቁና በአካባቢው እስከ ግሸን ደብረከርቤ የሚዘረጉ ታሪካዊና ሀይማኖታዊ አሻራዎች አሉ።
በዚሁ አካባቢ የእስልምና ሀይማኖት አሻራዎች ያሉባቸው ታላላቅ የእምነት ቦታዎችም በመኖራቸው አማኞች ለፀሎትና ጉብኝት ዛሬም ድረስ ይጎበኟቸዋል።
በቅርቡ የባቡር ፕሮጀክት ስራ ለማከናወን በነበረ ቁፋሮ የአንድ ትልቅ የእስልምና ኃይማኖ አባት መቃብር የነካ ዶዘር ምን እንደገጠመው ብዙዎች ያወሳሉ። በዘመናዊ አእምሮ የማንደፈራቸው በርካታ ተአምራትም አሉ።
በክርስትና ኃይማኖትም የመጀመርያው ኃይማኖታዊ ዩንቨርስቲ የሚባለው የሐይቅ እስጢፋኖስ አቡነ እየሱስ ሞዓ ገዳም ይገኛል። በዚህ ቦታ ከደብረ ዳሞ እስከ ደብረ ቢዘን( ኤርትራ) ከሳይንት እስከ አባጊዮርጊስ ዘጋስጫ የሚዘረጉ ታሪኮች አሉ። ቅዱሳንና ልዕለ ስብዕናዎች ፈርተውበታል።
በባህላዊ መገለጫነት ከሚጠቀሱት ውስጥ አጊያጌጥ( costume )፣ ፌስቲቫሎችና የጭፈራ አይነቶች ተጠቃሽ ናቸው። ለምሳሌ "የሚሌው አውሬ" የሚባለው የጭፈራ አይነት አጨዋወት ልዩ መገለጫ ያለው ሲሆን በጭፈራዎቹ ውስጥ ጀግንነትን፣ ውበትና አካባቢን የሚገልፁበት አሰነኛኘት አስደናቂ ነው።
የሀይቅ ልጅና የጣት ወርቅ አንድ ነው
ካመለጠ ወዲያ ፈላጊው ብዙ ነው።
ሌላው በዚህ አካባቢ ተለይቶ የሚታወቀው አሆላሎ ፌስቲቫል በውስጡ በርካታ ባህላዊ መገለጫዎችን የያዘ ነው። ፌስቲቫሉ ያለሀይማኖት ልዩነት የልጃገረዶችና ጎረምሶች ልዩ ክብረ በዓል ነው። የአደስ፣ አርቲ፣ ኩል፣ የተፈጥሮ ማጌጫዎችን የሚጠቀም በተለይ ጥር ወር ከጥምቀት ጋር እንዲሁም የአረፋ ሰሞንና የአስተርዮ ማርያም ባህላዊ ክዋኔ ነው። የዳኝነትና ልዩ ልዩ ስነስርዓቶች ያሉት ነው።
ሀይቅና አካባቢው በሁሉም አቅጣጫ ታሪካዊ፣ ባህላዊና ኃይማኖታዊ መገለጫዎች ብቻ ሳይሆን በተፈጥሮ ፀጋ የታደሉ ናቸው። ወይናደጋ የአየር ንብረት ስላላት ከሀይቅ ውሃው በተጨማሪ በ15 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የአርዲቦ ሀይቅና ጎልቦ ሀይቅ፣ የሚሌ ፍልውሃና የፈውስ ቦታዎች መገኛም ናት። በርካታ አይነት አዝዕርቶች የሚበቅሉባትም ነች።
እንዲህ ያሉ ታሪካዊ፣ ኃይማኖታዊና ተፈጥሯዊ ሀብቶች ላይ ልዩ ልዩ ፕሮጀክቶች ተጨምረውላታል። ከነዚህም ውስጥ
- የጭፍራ - ሀይቅ አስፋልት መንገድ
- የአዋሽ - ኮምቦልቻ- ወልድያ ባቡር መንገድ
- የሎጎ ሀይቅ ሪዞርት ይገኙበታል።
እነዚህ ፕሮጀክቶች በተለይ በቅርቡ አገልግሎት መስጠት የጀመረው የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ልዩ ገፅታን አላብሷታል።

ሎጎ ሀይቅ ሪዞርትን እንደዕድል
ሪዞርቱ ሀይቅ እስጢፋኖስ ጋር ትይዩ ሆኖ ሆኖም በሀይቁ በኩል 1 ኪሜ ያክል ርቆ የተሰራ ከባቡርና ከጭፍራው መንገድ እንዲሁም ወደኮምቦልቻ ለመሄድ ሌላ አማራጭ መንገድ በሚኖርበት አመች ቦታ ላይ 14 ሄክታር ቦታ ላይ ያረፈ ነው።
ሪዞርቱን ድንቅ የሚያሰኘው ቀድመው የነበሩ ዛፎችንና የመሬት አቀማመጦችን ባሉበት ሁኔታ ተጠቅሞ በመርከብ ቅርፅ የተሰራ መሆኑ ነው። ጥበበኛ እጆች የሰረት ነው Nigat Zd ሊመሰገን የሚገባው ጥበበኛ ሆኖ አግኝቼዋለሁ።
ቀደም ሲል ከሰለሞን ክብረት በፊት "ከበደ አሊ መናፈሻ" ( ፊሾ) ይባል የነበረው ቦታ ላይ ቀድሞ የነበረውን ሎጅ የሚያስታውስ ዲዛይን አለበት። ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ገፅታዎችን ጠብቆ ማልማት መቻላቸው በአጠቃላይ የፕሮጀክቱን መሪዎች በሙሉ የሚያስመሰግን ነው።
ሪዞርቱ የእርሻ፣ የመዝናኛ፣ የአገልግሎት ክፍሎች ያሉት ነው። ይህን ሪዞርት የቱሪዝም አገልግሎት መስጫ ብቻ አድርጎ ማዬት አይቻልም።

በሶስት ምክንያት
1. በታሪካዊና ተፈጥሯዊ ዳራው
2. በተሰራበት ጥራት፣ እይታና ሁኔታ
3. ተስፋው

ሪዞርቱ ራሱን የቻለ ከተማ የሚሆን ነው።

የሚጎድለው አንድ ትልቅ የፌስቲቫል/ ኹነት ማከናወኛ መሰረተ ልማት ነው። ይህ ቦታ ልዩ ልዩ የአደባባይ ዝግጅቶች ለማከናወን የሚያስችል ይሆናል። ተከታታይ ሰፋፊ ስብሰባ ማከናወኛ ማዕከልም መሆን ይችላል። ልዩ ልዩ ሁሉን አቀፍ ውድድሮችም ማከናወኛ ይሆናል። ቦታው ከተፈጥሮና ባህላዊ ፀጋው ጋር ተያይዞ ተመራጭ መዳረሻም የመሆን እድሉ ከፍተኛ ነው።
ቦታው በተለይ ለአሆላሎ ፌስቲቫል ማከናወኛ ሆኖ ቢሰናዳና በሪዞርቱ አስተዳዳሪነት የሀይቅ ውሃው እይታ ባለበት ቦታ ላይ ተጠርጎ ቢዘጋጅ ቢያንስ በዓመት ሁለት ጊዜ ፌስቲቫሎች ሊዘጋጁበት ይችላሉ። የወሎ ፈረሰኞች በተለይ ድሮ ቀጤ ሜዳ ላይ ይከናወን የነበረውን ፈረስ ግሊቢያ ማከናወኛም የመሆን እድል አለው።
ሌላው ሪዞርቱ የመግቢያ ክፍያ ያለው በመሆኑና ገና ስላልተዋወቀ ብዘ ሰው እየጎበኘው አይደለም። በርግጥ ብዙ ሰው ቢያጥለቀልቀው ሊበላሹ የሚችሉ ጉዳዮች ይኖራሉ።
ሆኖም የአካባቢው ሰው ልማቱን ትርጉም እንዲሰጠው የሚያችል ግብዣዎችና ዝግጅቶች በማሰናዳት ማነቃቂያም አድርጎ ማሰብ ይፈልጋል። ባለቤትነትም ተሰምቶት አብሮ እንዲሰራ ለማድረግ ልዩ ልዩ ስልቶችን መጠቀም ያስፈልጋል። ይህ እስከ ደሴ፣ ኮምቦልቻ፣ አፋር፣ ወልድያ ድረስ የሚያካት ቢሆን።
ልማትና ዕድገት ይምሩን!
ተስፋዬ ይመር ( ወርጣዬ)
ሀምሌ 20-24 ስለጎበኘኋት ሀይቅ
ነሀሴ 3/2018

ሂልተን ባህር ዳርን በፍጥነት አጠናቆ ስራ ለማስጀመር በትኩረት እየተሰራ ነው ።     ከቀናት በፊት በምክትል ጠ/ሚኒስትር  አቶ ተመስገን ጥሩነህና በክልሉ ፕሬዚደንት አቶ አረጋ ከበደ የተጎ...
09/08/2026

ሂልተን ባህር ዳርን በፍጥነት አጠናቆ ስራ ለማስጀመር በትኩረት እየተሰራ ነው ።
ከቀናት በፊት በምክትል ጠ/ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህና በክልሉ ፕሬዚደንት አቶ አረጋ ከበደ የተጎበኘው ሂልተን ባህር ዳር የግንባታ ሂደቱ በጥሩ ደረጃ ላይ መሆኑ ተመላክቷል።
ቢኬጂ በሆቴል ዘርፍ የቆየ ልምድ ያለው ሲሆን ከወራት በፊት ሎጎ ሐይቅ ሪዞርትን በጥራት ገንብቶ በማስረከብ በሀገር ደረጃ እውቀና የተሰጠው ሲሆን በአሁኑ ሰአት ደግሞ ሪዞርቱን በማስተዳደር ለአካባቢው የቱሪዝም እድገት ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው ።
ቢኬጂ በሆቴል ዘርፍ ለባህር ዳር ከተማ እውን የሚያደርገው ሂልተን ባህር ዳር በዘመናዊነቱ፣ በሚያቀርባቸው አገልሎቶች ብሎም በመኝታ አገልግሎት መስጫ ክፍሎቹ ብዛት በቀዳሚነት የሚቀመጥ ሲሆን የሆቴሉ መጠናቀቅ ለውቢቱ ባህር ዳርና ለአካባቢው የቱሪዝም መጎልበት ትልቅ ሚና ይኖረዋል።
ቢኬጂ ከባህር ዳር በተጨማሪ በአዳማ ከተማ በቢኬ ሆቴል ዘርፍ ስር የሚገኘውን አዳማ ራስ ሆቴል ደረጃውን አስድጎ ለአገልግሎት ለማብቃት በትኩረት አየሰራ ነው።

ቢኬጂ
የታታሪዋ ኢትዮጵያ ተምሳሌት

ለውቢቱ ባህር ዳር ሌላ መልክና ገጽታን የሚያጎናጽፈውና በቢኬጂ የሚገነባው ሂልተን ባህር ዳር ሆቴል   የግንባታ ሂደቱ እየተፋጠነ ነው ።     የሆቴሉ የግንባታ  ሂደት በኢፌድሪ ም/ጠ ሚኒስ...
08/08/2026

ለውቢቱ ባህር ዳር ሌላ መልክና ገጽታን የሚያጎናጽፈውና በቢኬጂ የሚገነባው ሂልተን ባህር ዳር ሆቴል የግንባታ ሂደቱ እየተፋጠነ ነው ።
የሆቴሉ የግንባታ ሂደት በኢፌድሪ ም/ጠ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በክልሉ ፕሬዚደንት አቶ አረጋ ከበደና በሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተጎብኝቷል።
ቢኬጂ
የታታሪዋ ኢትዮጵያ ተምሳሌት

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Belayneh Kindie Group posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share