AAAE የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት/Addis Ababa Abattoirs Enterprise

AAAE   የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት/Addis Ababa Abattoirs Enterprise short code 8868

13/05/2026
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክትኢትዮጵያ እና የተባበሩት መንግሥታት፤ የጋራ ታሪክ፣ የአሁን እና ተሻጋሪ ትብብር ፣ በሰላም አብሮ ለመኖር!‎‎ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት...
13/05/2026

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

ኢትዮጵያ እና የተባበሩት መንግሥታት፤ የጋራ ታሪክ፣ የአሁን እና ተሻጋሪ ትብብር ፣ በሰላም አብሮ ለመኖር!

‎ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የስምንት አስርት ዓመታት ጉዞን ምክንያት በማድረግ፣ "በሰላም አብሮ ለመኖር" በሚል መሪ ቃል ልዩ የመታሰቢያ ቴምብር ስብስብ አውጥታለች።
‎እነዚህ አራት ቴምብሮች እ.ኤ.አ. በ1945 በሳን ፍራንሲስኮ የተባበሩት መንግሥታት ቻርተርን ከመፈረም ጀምሮ፣ በኮንጎ የሰላም አስከባሪ ኃይሎችን እስከማሰማራት እና በአፍሪካ ምድር ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደውን የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት ስብሰባ እስከ ማስተናገድ ያለውን የጋራ ታሪካችንን የሚተርኩ ናቸው። በዓለም የፖስታ ህብረት በኩል ለ192 ሀገራት የተሰራጩት እነዚህ ቴምብሮች፣ ለአንድ ወቅት ብቻ ሳይሆን ለትውልድ ሁሉ የሚተርፍ የታሪክ ዐሻራ ማሳያ ናቸው።

‎በዚሁ አጋጣሚ፣ ለተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ ክቡር አንቶኒዮ ጉቴሬዝ እና ለቡድናቸው፣ በዘመናዊው ታሪክ ውስጥ እጅግ ፈታኝ በሆነ ወቅት ላይ ሰላምን፣ ልማትን እና ሰብዓዊ መብቶችን ለማስከበር እያሳዩት ላለው ጽኑ አመራር ጥልቅ አድናቆታችንን እንገልጻለን።
‎የተባበሩት መንግሥታት የጸናው ሀገራት ከመከፋፈል ይልቅ ውይይትን ስለመረጡ ነው።
‎ኢትዮጵያም ይህንኑ የሁልጊዜ ምርጫዋን ታጸናለች!

ባለስልጣኑ በንግድ ስራዎች ድርጅት ላይ እያስጠና ያለው የመዋቅር ጥናት ለአመራሮችና ለባለድርሻ አካላት ቀረበሚያዚያ 30/2018 :-በአዲስ አበባ በየአዲስ አበባ ከተማ የመንግስት ልማት ድርጅ...
08/05/2026

ባለስልጣኑ በንግድ ስራዎች ድርጅት ላይ እያስጠና ያለው የመዋቅር ጥናት ለአመራሮችና ለባለድርሻ አካላት ቀረበ

ሚያዚያ 30/2018 :-በአዲስ አበባ በየአዲስ አበባ ከተማ የመንግስት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን በንግድ ስራዎች ድርጅት በ10 ዓመት ፍኖተ ካርታ መሰረት እየተጠናያ ያለው የመዋቅር ጥናት ለባለስልጣኑ አመራሮችና ለባለድርሻ አካላት በዛሬው ዕለት ቀርቧል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተንኩዌይ ጆክ እንደገለጹት፣አዲሱ መዋቅር የስራ አፈፃፀምን ውጤታማ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

ዋና ስራ አስፈፃሚው አክለውም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጥናት ቡድን በጥናቱ ሂደት ተጨባጭ መረጃዎችን ማቅረቡን ጠቅሰው፣ ቴክኒካል ሃሳቦችን በማካተት የተጠናቀቀው ጥናት በቀጣይ እንዲቀርብ አሳስበዋል።

የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የስርዓት ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ድዳ ድሪባ በበኩላቸው የጥናት ቡድኑ በዚህ ደረጃ ጥናቱን ማቅረቡ አበረታች መሆኑን ገልጸው፣ በቀጣይ ሁሉም የጥናቱ ስራዎች በተሰጠው ግብዓት መሰረት ተካተው መቅረብ አለባቸው ብለዋል።

በዕለቱ የጥናት ቡድኑ አባላት የመዋቅሩን ጥናት በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን፣ ከተሳታፊዎች የተለያዩ አስተያየቶች፣ ጥያቄዎች እና ጥናቱን የሚያሻሽሉ ምክረ ሃሳቦች ቀርበዋል። ለቀረቡት ጥያቄዎችም በቂ ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቷል።

ውጤታማ ስራ ለማከናወን ሰራተኞችን በአቅምና በችሎታ መመደብ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸሚያዚያ 22/2018:- ውጤታማና ትርፋማ ስራ ለማከናወን ሰራተኞችን በችሎታቸውና በሙያቸው የሚመጥኑ የስራ ቦታዎ...
30/04/2026

ውጤታማ ስራ ለማከናወን ሰራተኞችን በአቅምና በችሎታ መመደብ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ

ሚያዚያ 22/2018:- ውጤታማና ትርፋማ ስራ ለማከናወን ሰራተኞችን በችሎታቸውና በሙያቸው የሚመጥኑ የስራ ቦታዎች ላይ መመደብ እጅግ አስፈላጊ መሆኑ ተገልጿል።

ይህ የተገለጸው በአዲስ አበባ ከተማ የመንግስት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን ለተጠሪ የልማት ድርጅቶች በሪፎርም አተገባበር፣ በስራ መመሪያዎች እና በሰራተኞች የድልድልና ምደባ አፈፃፀም ላይ በተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ወቅት ነው።

የአዲስ አበባ ከተማ የመንግስት ልማት ድርጅቾች አስተዳደር ባለስልጣን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተንኩዌይ ጆክ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደገለጹት፣ተቋማት አደረጃጀታቸውን በመከተል ሰራተኞችን በሚመጥናቸው የስራ ቦታዎች ሲመድቡ የተቋሙ አፈፃፀም እንደሚጨምር ገልጸዋል።

እየተካሄደ ያለው የሪፎርም ስራ ሰራተኞች ስራቸውን በአግባቡ እንዲያከናውኑና የአገልግሎት አሰጣጡ ለተገልጋዮች እንዲሻሻል እንደሚያግዝ አቶ ተንኩዌይ አክለው ጠቅሰዋል።

በተመሳሳይ የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የስርዓት ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ድዳ ድሪባ በበኩላቸው፣ሪፎርሙ ስራንና ሰራተኛን በአግባቡ ለማገናኘት እና የተቋማትን ውጤታማነት ለማሻሻል ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

ቀልጣፋ አገልግሎትንና ደንበኛን የሚያረካ አፈፃፀምን ለማረጋገጥ ሪፎርሙ አስፈላጊ መሆኑን ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚው አክለው ተናግረዋል ።

በስልጠና መርሃ-ግብሩ ከተጠሪ ልማት ድርጅቶች በሪፎርሙ ስራ ላይ በተለያዩ የኮሚቴ ተግባራት ላይ የሚሳተፉ ባለሙያዎች የተገኙ ሲሆን በተሰጠው ስልጠና የተለያዩ ሃሳብና አስተያየቶች ተነስተው ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን ለተነሱት ጥያቄዎችም ምላሽ ተሠጥቶባቸዋል፡፡

የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት አመራርና ሰራተኞች የ9ወር የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ አካሄዱሚያዚያ 21፤ቀን 2018 ዓ.ምድርጅቱ ባለፉት 9 ወራት ያከናወናቸዉን በርከት ያሉ ተግባራት አፈጻጸማቸ...
29/04/2026

የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት አመራርና ሰራተኞች የ9ወር የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ አካሄዱ
ሚያዚያ 21፤ቀን 2018 ዓ.ም
ድርጅቱ ባለፉት 9 ወራት ያከናወናቸዉን በርከት ያሉ ተግባራት አፈጻጸማቸዉ ምን እንደሚመስልና ይህንንም ተከትሎ የመጡ ለዉጦች በስፋት የተዳሰሰበት ሪፖርት ቀርቦ ዉይይት ተካሂዶበታል፡፡
የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ እንዳብራሩት በተለይ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ የነበሩትን የዕርድ ማስፋፊያ ስራና የዉሃ እጥረት ችግሮች በአጭር ግዜ ሰራተኛዉና አመራሩ በጋራ በመስራት ዕልባት እንዲያገኝ በመቻሉ በዚህ ረገድ የነበረዉን የደንበኞች ቅሬታ መፍታት ያስቻለ እርምጃ መወሰዱን ጠቅሰዉ ይህም ቀጣይነት ባለዉ መልኩ እንደሚሰራበት አሳስበዋል፡፡ በተጨማሪም በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ ስራ አስፈጻሚዉ አቅጣጫ እስቀምጠዋል፡፡
በዉይይቱ በሰራተኞች በኩል የተለያዩ ሀሳቦች እና አስተያቶች የቀረቡ ሲሆን በዋናነትም እስካሁን በተሰሩ ስራዎች ብዙ መሻሻሎች መኖራቸዉን ገልጸዉ ዘላቂና ቀጣይነት እንዲኖራቸዉ ግን የጋራ ስራዉ ተጠናክሮ መቀጠል ይገባዋል ሲሉ አስተያየታቸዉን ሰጥተዋል፡፡

ለተጨማሪ መረጃ 👇

ነፃ የስልክ መስመር፡- 8868

ፌስቡክ:-https://www facebook.com/AAAEKERA

ቲውተር፡-https://twitter.com/AAAEkera

ቴሌግራም፡- https://t.me/AAAEKERA

የከተማ አስተዳደራችንን የ9 ወራት የሥራ አፈጻጸም ገምግመን ቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ አጠናቀናል።በግምገማችንም ከአምስ አመት አንፃር የደረስንበት እያነፃፀርን ፣የተገኙ ውጤቶች እና  ተስ...
27/04/2026

የከተማ አስተዳደራችንን የ9 ወራት የሥራ አፈጻጸም ገምግመን ቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ አጠናቀናል።

በግምገማችንም ከአምስ አመት አንፃር የደረስንበት እያነፃፀርን ፣የተገኙ ውጤቶች እና ተስፋ ሰጪ አፈጻጸሞች እንዲሁም በቀጣይ መስተካከል ያለባቸው ተግባራት ለይተናል።
የ9 ወር አፈፃፀምን ጨምሮ ባለፋት አምስት አመታት ከተከናወኑ በርካታ ተግባራት ዋና ዋናዎቹን ለአብነት ያክል:-

• ስር የሰደዱ ኋላ ቀር አስተሳሰቦችን ችግሮችን ተጋፍጠን የጋራ እሴት ግንባታ ላይ በትጋት ሰርተናል።በዚህም አዲስ አበባን ከሰፈር ፖለቲካ አውጥተን፣ የዲፕሎማቲክ ማዕከልነቷ ይበልጥ ጎልብቶና አድጎ ከተማችን ከእኔነት ወደ የሁላችን ከተማነት ከፍ አድርገናታል።በዚህም ለኢትዮዽያዊን ብቻ ሳይሆን አፍሪካዊያን ሁሉ ዋና ከተማችን ብለዉ የሚኮሩባት ከተማ አድርገናታል።
• አዲስ አበባን “ እንደ ስሟ ውብ አዲስ አበባ “እናደርጋታለን ብለን በቃላችን መሰረት:-
• የከተማችንን ጎስቋላ ገጽታ ለመቀየር 74 በመቶ የሚሆነውን የጭቃ ቤት ወደ ውብ ምቹ ከተማ ለማድረግ በሰራነው ሥራ በ44 በመቶ በመቀነስ ችለናል።

• ተማሪዎቻችን የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም እና ዩኒፎርም የማቅረብ የትልድ ግንባታን አከናውነናል።
• የአዲስ አበባ ህጻናት ቦርቀዉ የሚጫወቱበት ከ5ሺህ በላይ የልጆች መጫወቻ ፣እንክብካቤ የሚያገኙበት
ከ1000 በላይ ዴይ ኬር ገንብተን በርካታ ወላጆችን እፎይ አስብለናል።

• በከተማችን 30 የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከላትን በመገንባት ጧሪ የሌላቸው አረጋውያን፣ አቅመ ደካሞች እና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ወገኖቻችንን ተጠቃሚ አድርገናል።
• በ “የለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል” በሺዎች የሚቆጠሩ ሴቶች ከአስከፊ ህይወት እንዲወጡና በተጨባጭ የሥራ ባለቤት እንዲሆኑ ተደርጓል።
• የአረጋዊያን መጦሪ ፣ መስማትና ማየት ለተሳናቸዉ ት/ቤት ተገንብተው ልማታችን ማንንም ወደ ኋላ የተወ እንመዳይሆን በጥቃቄ ሰርተናል።

• የተበከሉ ወንዞች ፀድዉ፣ለጎርፍ ተጋላጭ በሆኑ እና በቆሸሹ የወንዝ ዳርቻ አካባቢዎች ይኖሩ ለነበሩ ነዋሪዎች የተሻለ መኖሪያ ቤቶች ተገንብተው ተሰጥቷል።

ጨለማ የነበሩ ጐዳናዎች በርተዋል ። በዚህም ለወንጀል ለዝርፊያ ለአስገድዶ መድፈር አጋላጭ የነበሩ አካባቢዎች ተቀይረዋል።
• በየሜዳዉ ከመፀዳዳት ለህዝባችን ምቾትን የሚጨምሩና ክብርን የሚጠብቁ እንዲሁም ጤናው እንዲጠበቅ የሚያስችሉ ንጹህ፣ ደረጃቸውን የጠበቁ መጸዳጃዎችን በስፋት ገንብተናል።

• የመገድ ሽፋንን 12.% ወደ20 % አሳድገናል።በርካታ የመኪና ማቆሚያዎች፣ ደረጃቸውን የጠበቁ መጸዳጃዎች፣ ሰፋፊ የፍሳሽ ማስወገጃ መስመሮች እና ማጣሪያ ማእከላት ተገንብተዋል።

• የከተማችንን የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ከ70% በላይ ማሳደግ ችለናል።
የቤት አቅርቦት 480ሺ አድርሰናል ።

• ወጣቶች በአካል እና በአዕምሮ የዳበሩ እንዲሆኑ የስፖርት ማዘውተሪያ እና ደረጃቸውን የጠበቁ የስፖርት መወዳደሪያ ማዕከላት በየአካባቢዉ ገንብተናል።
• አዳዲስ ሆስፒታሎች ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት ሲደረጉ፣ ነባሮቹም ታደሰው ደረጃውን ለጠበቀ አገልግሎት ዝግጁ ተደርገዋል።
• የከተማዋን የመንገድ እና የአረንጓዴ ስፍራ ሽፋን 2.8% ወደ24% አሳድገናል።
• ከአፍሪካ አስር ንጹህ ከተሞች አዲስ አበባ አንዷ ንጹህ ከተማ መሆን ችላለች።

•በዚህም የቱሪዝም ማዕከል በመሆን በ2018 ዘጠኝ ወራት ከ200 በላይ ዓለም አቀፍ ኮንፍራንሶችን አስተናግደናል።
አሁን ያገኘናቸውን ስኬቶች እና አፈጻጸም በቀጣይ የበለጠ በማጠናከር ከተማችንን የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ መግባባት ላይ ደርሰናል።

• በህዝብ ተሳትፎ እና በመንግት በጀት ከ60ሺህ በላይ ፕሮጀክቶችን አጠናቀን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል።

• ከፍተኛ ተግዳሮት የሆነብንን ስር የሰደደ ቀርፋፋ የአገልግሎት አሰጣጥን እና የጉበኝነት ልምምድ ለመለወጥ የመንግስት አገልግሎቶችን በ6 የመሶም የአንድ ማዕከል አገልግሎት እና በአንድ ዲጅታል ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎት መስጠት የቻልን ሲሆን፣ ቀሪ 5 ማልከላት በቅርቡ ወደ ስራ ይገባሉ።

• ልላኛዉ ተግዳሮት የሆነብንን የኑሮ ውድነት ጫናን ለመቀነስ የገበያ ማዕከላትን እና የእሁድ ገበያዎችን በተለያዩ የከተማው አካባቢዎች አስፋፍተናል።
በመሆኑም በልማት፥በሰላም፥ በማህበራዊ ስራዎች አብሮን ሳይለየን የሰራውን መላው የከተማችን ነዋሪ በጣም እናመሰግናለን።

ከሁሉ በላይ ያሳካልን ፈጣሪ አምላክ ምስጋና ይገባዋል!!!

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ስር የሰደዱ ኋላ ቀር አስተሳሰቦችን እና ችግሮችን ተጋፍጠን የጋራ እሴት ግንባታ ላይ በትጋት ሰርተናል።በዚህም አዲስ አበባን ከሰፈር ፖለቲካ አውጥተን፣ የዲፕሎማቲክ ማዕከልነቷ ይበልጥ ጎልብቶ...
27/04/2026

ስር የሰደዱ ኋላ ቀር አስተሳሰቦችን እና ችግሮችን ተጋፍጠን የጋራ እሴት ግንባታ ላይ በትጋት ሰርተናል።

በዚህም አዲስ አበባን ከሰፈር ፖለቲካ አውጥተን፣ የዲፕሎማቲክ ማዕከልነቷ ይበልጥ ጎልብቶና አድጎ ከተማችን ከእኔነት ወደ የሁላችን ከተማነት ከፍ አድርገናታል።

በዚህም ለኢትዮዽያዊን ብቻ ሳይሆን አፍሪካዊያን ሁሉ ዋና ከተማችን ብለዉ የሚኮሩባት ከተማ አድርገናታል። - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Address

From Mxico To Kera, አዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AAAE የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት/Addis Ababa Abattoirs Enterprise posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share