30/12/2025
ከ8 ተከታታይ ጨዋታ በኃላ አስቶን ቪላ በአርሰናል 4 ለ 1 ተሸነፈ
በ19ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የበዓል ሰሞን ጨዋታ መድፈኞቹ 4 ለ 1 በማሸነፍ ከተከታያቸው ማንችስተር ሲቲ ያላቸውን የነጥብ ልዩነት ወደ 5 አስፍተዋል፡፡
በኤምሬትስ በተደረገው ጨዋታ አስቶን ቪላ ከ11 ተከታታይ አሸናፊነት በኋላ ጉዞው በአርሰናል ተገቷል፡፡
ከጉዳት የተመለሰው ጋብርኤል ማጋሌሽ፣ ማርቲን ዙቢሜንድ እና ሌአንድሮ ትሮሳርድ እንዲሁም ተቀይሮ የገባው ጋብርኤል ጄሱስ በመጀመርያ የኳስ ንኪኪው ግቦቹን አስቆጥረዋል፡፡
ኦሊ ዋትኪንስ የአስቶን ቪላን አንድ ግብ በባከነ ሰዓት አስቆጥሯል፡፡
ለ11 ወራት በጉዳት ከሜዳ የራቀው ጋብርኤል ጄሱስ ተቀይሮ ከገባ በኋላ ግቧን ለማስቆጠር የወሰደበት ጊዜ 55 ሰከንድ ብቻ ነው፡፡ ከሦስት ጨዋታ በፊት በቪላ ፓርክ 2 ለ 1 የተሸነፉት መድፈኞቹ የዋንጫ ግስጋሴያቸውን ያሳመሩበትን ምሽት አሳልፈዋል፡፡
አሰልጣኝ ኡናይ ኢምሪ በፕሪሚየር ሊጉ ከ8 ተከታታይ ድል በኋላ በቀድሞ ክለባቸው ለመሸነፍ ተገደዋል፡፡
#