Tame TK

Tame TK Media and news page

ከ8 ተከታታይ ጨዋታ በኃላ አስቶን ቪላ በአርሰናል 4 ለ 1 ተሸነፈበ19ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የበዓል ሰሞን ጨዋታ መድፈኞቹ 4 ለ 1 በማሸነፍ ከተከታያቸው ማንችስተር ሲቲ ያላቸ...
30/12/2025

ከ8 ተከታታይ ጨዋታ በኃላ አስቶን ቪላ በአርሰናል 4 ለ 1 ተሸነፈ
በ19ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የበዓል ሰሞን ጨዋታ መድፈኞቹ 4 ለ 1 በማሸነፍ ከተከታያቸው ማንችስተር ሲቲ ያላቸውን የነጥብ ልዩነት ወደ 5 አስፍተዋል፡፡

በኤምሬትስ በተደረገው ጨዋታ አስቶን ቪላ ከ11 ተከታታይ አሸናፊነት በኋላ ጉዞው በአርሰናል ተገቷል፡፡

ከጉዳት የተመለሰው ጋብርኤል ማጋሌሽ፣ ማርቲን ዙቢሜንድ እና ሌአንድሮ ትሮሳርድ እንዲሁም ተቀይሮ የገባው ጋብርኤል ጄሱስ በመጀመርያ የኳስ ንኪኪው ግቦቹን አስቆጥረዋል፡፡

ኦሊ ዋትኪንስ የአስቶን ቪላን አንድ ግብ በባከነ ሰዓት አስቆጥሯል፡፡

ለ11 ወራት በጉዳት ከሜዳ የራቀው ጋብርኤል ጄሱስ ተቀይሮ ከገባ በኋላ ግቧን ለማስቆጠር የወሰደበት ጊዜ 55 ሰከንድ ብቻ ነው፡፡ ከሦስት ጨዋታ በፊት በቪላ ፓርክ 2 ለ 1 የተሸነፉት መድፈኞቹ የዋንጫ ግስጋሴያቸውን ያሳመሩበትን ምሽት አሳልፈዋል፡፡

አሰልጣኝ ኡናይ ኢምሪ በፕሪሚየር ሊጉ ከ8 ተከታታይ ድል በኋላ በቀድሞ ክለባቸው ለመሸነፍ ተገደዋል፡፡
#

ጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ የተፈጥሯዊ ሀብት ጥበቃንና ኢኮ-ቱሪዝምን በማበረታታት ትልቅ ሚና እየተጫወተ ነውጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፖርኩ የተፈጥሯዊ ንብረትና በተለያዩ የዱር እንስሳት ሀብት የ...
29/12/2025

ጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ የተፈጥሯዊ ሀብት ጥበቃንና ኢኮ-ቱሪዝምን በማበረታታት ትልቅ ሚና እየተጫወተ ነው

ጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፖርኩ የተፈጥሯዊ ንብረትና በተለያዩ የዱር እንስሳት ሀብት የተሞላ መሆኑ ይታወቃል። ፓርኩ የአገሪቱን የሕይወት ብዝሃነት ለመጠበቅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ ሲሆን፣ የኢኮ-ቱሪዝም ልማትን በማበረታት ለአካባቢው ማህበረሰብ የኢኮኖሚ ዕድገት ዕድሎችን እየፈጠረ ነው።

በፓርኩ ውስጥ ዝሆን፣ አንበሳ፣ ጎሽ፣ አጋዘንና የተለያዩ የዱር አውሬዎች እንዲሁም የአዕዋፋት ዝርያዎች በሰፊ መጠን ይገኛሉ።
ይህ ሁኔታ ፓርኩን ለተፈጥሮ ጥናትና ለቱሪስቶች ልዩ መዳረሻ አድርጎታል። የፓርኩ አስተዳደር ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመተባበር የጥበቃ ስራዎችን እያጠናከረ ሲሆን፣ ይህ የተሳትፎ አቀራረብ የፓርኩን ጥበቃ ለማጠናከር እና ለአካባቢው ልማት አዎንታዊ ተፅዕኖ አለው።

በአጠቃላይ፣ ጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፖርክ የተፈጥሮ ጥበቃን ከልማት ጋር በማጣመር የሚታወቅ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ የኢኮ-ቱሪዝም እድገት ውስጥ ተስፋ ሰጪ ምሳሌ መሆኑን እያረጋገጠ ይገኛል።
Konta #

❗️ እውነተኛ ለውጥ የሚመጣው ከውስጥ ብቻ ነው.... እራስን  ሳይቀይሩ አለምን ለመቀየር ማሰብ የዘበት ነው። ✍️ የተሻለ ማንነትን ለመፍጠር፣ አዳዲስ ነገሮችን ለመሞከር፣ ልማዶች ወይም የአ...
25/12/2025

❗️ እውነተኛ ለውጥ የሚመጣው ከውስጥ ብቻ ነው.... እራስን ሳይቀይሩ አለምን ለመቀየር ማሰብ የዘበት ነው።

✍️ የተሻለ ማንነትን ለመፍጠር፣ አዳዲስ ነገሮችን ለመሞከር፣ ልማዶች ወይም የአኗኗር ዘይቤአችንን ለመቀየር በራስ ተነሳሽነት ስንወስን ነገሮች ሁሉ በተሻለ ሁኔታ ይሰራሉ።

✊ ምንም እንኳን በመጀመሪያዎቹ ጥቂት ጊዜያት ከባድ ስሜት ቢሰማንም እንኳ በሂደት ግን ለውጦችን የመፍጠር ኃይል እንዳለን በጊዜ ሂደት እንገነዘባለን።

💪 የሚያስፈልገንን ውስጣዊ ጥንካሬ ለማዳበር ምን ጊዜም ቢሆን ሂደቱን ከውስጥ መጀመር አለብን። ይህንን ውስጣዊ ጥንካሬአችንን አእያወቅን እና እያጓለበትን ስንመጣ መልካም ነገሮችን የመፍጠር፣ የሰመረ ህይወትን የምራት እና ለሌሎች ምሳሌ መሆን እንጀምራለን።

👍 ከእኛ የሚጠበቀው ማመን እና ጊዜ ወስዶ እራስን መቀየር ነው!

የስኬት መርሆዎች
መንደር #

በባህልና ስፖርት ሥራ ዘርፎች የሚታዩ አበረታች ውጤቶች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው።  የባህልና ስፖርት ሚ/ር ልዑካን ቡድን=============================የፌዴራል ባህልና ስፖ...
24/12/2025

በባህልና ስፖርት ሥራ ዘርፎች የሚታዩ አበረታች ውጤቶች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው። የባህልና ስፖርት ሚ/ር ልዑካን ቡድን
=============================
የፌዴራል ባህልና ስፖርት ሚኒስትር ልዑካን ቡድን በዞኑ በባህል፣ ቋንቋና ስፖርት ዘርፎች እየተሠሩ ያሉ ሥራዎችን ምልከታ አድርገዋል።

ልዑካን ቡድኑ በባህል ሥራ ዘርፎች የሙዚየም አደረጃጀት፣ ባህል እሴቶችና ትውፊታዊ ሀብቶች አጠባበቅና አጠቃቀም፣ ሀገር በቀል እውቀቶችን ማልማትና ማሳደግ፣ የቤተ መጽሐፍት ማዕከል ጥበቃና እንክብካቤ እንዲሁም አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የተሠሩ ሥራዎችን ምልከታ አድርገዋል።

በጉብኝቱ የፌደራል ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የፖሊሲና ስትራቴጂ ጥናትና ምርምር ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር አውላቸው ሹምነካ በዞኑ የባህል እሴቶችና ትውፊታዊ ሀብቶች አጠባበቅ፣ አጠቃቀም እንዲሁም በስፖርቱ ዘርፍ ታዳጊ ወጣት ስፖርተኞችን በማፍራት ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሠሩ ያሉ ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አመላክተዋል።
#ኮንታ ዞን ባህል ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ #

ከሪበላ ሐይቅ - በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ኮንታ ዞን የሚገኘው ማራኪ ተፈጥሮ
23/12/2025

ከሪበላ ሐይቅ - በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ኮንታ ዞን የሚገኘው ማራኪ ተፈጥሮ

የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ የቴሌቪዥን ስርጭት ፈቃድ አገኘየደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመገናኛ ብዙሃን ተቋም የሆነው የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ፣ የህዝብ ብሮድካስት የቴሌ...
18/12/2025

የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ የቴሌቪዥን ስርጭት ፈቃድ አገኘ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመገናኛ ብዙሃን ተቋም የሆነው የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ፣ የህዝብ ብሮድካስት የቴሌቪዥን ስርጭት አገልግሎት ለመስጠት ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ይፋዊ ፈቃድ ዛሬ አግኝቷል።

ይህ ፈቃድ የሚዲያ ተቋሙ የክልሉን ማህበረሰብ በተሟላ መረጃ ለማገልገል የጀመረውን ጉዞ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ታሪካዊ እርምጃ መሆኑ ተገልጿል።

በዛሬው ዕለት በባለስልጣኑ ጽ/ቤት በተካሄደው የፈቃድ ርክክብ ስነ-ስርዓት ላይ የሚዲያ ኔትወርኩ ስራ አስኪያጅ አቶ መንግስቱ መኩሪያ እና ምክትላቸው ዶ/ር ካሳሁን ወዳጆ ፈቃዱን ከባለስልጣኑ ሃላፊዎች እጅ በይፋ ተረክበዋል።

የቴሌቪዥን ስርጭቱ መጀመር፣ ሚዲያ ኔትወርኩ "በመረጃ የበለጸገ ህብረተሰብ ተፈጥሮ ማየት" በሚል ራዕይ የጀመረውን ጥረት የሚያጠናክር ትልቅ ምዕራፍ ነው። ይህ ፈቃድ ተቋሙ በክልሉ ውስጥ ያለውን የመረጃ ተደራሽነት በማስፋት የህዝቡን የመረጃ ፍላጎት ለማርካት የሚያስችለውን ቁልፍ እንደተረከበ ያሳያል።

የቴሌቪዥን ስርጭቱ መጀመር በክልሉ የሚገኙ በርካታ ዜጎችን በቀላሉ ለመድረስና የሚዲያ ተደራሽነትን ለማስፋት ወሳኝ ነው። ኔትወርኩ በዚህ ፈቃድ አማካኝነት የክልሉን ብሎም የሀገሪቱን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮች እንዲሁም የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሂደቶችን ለህዝብ በማድረስ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከሚዲያዉ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።

ጅማ ከተማ 21ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል እንድታዘጋጅ ተመረጠች***********ጅማ ከተማ 21ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል እንድታዘጋጅ በይፋ ተመርጣለች፡፡በዚ...
08/12/2025

ጅማ ከተማ 21ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል እንድታዘጋጅ ተመረጠች
***********

ጅማ ከተማ 21ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል እንድታዘጋጅ በይፋ ተመርጣለች፡፡

በዚህም 21ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ የሚከበር ይሆናል፡፡

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የዝግጅቱን ሰንደቅ ዓላማ ለኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ አስረክበዋል፡፡
#

ለህዳር 29 ቀን በዓል አከባበር  የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የባህል ቡድን በሆሳዕና ከተማ ይገኛሉ።በመጪው ሰኞ ለ20ኛ ጊዜ  በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አስተናጋጅነት ለሚካሄደው...
06/12/2025

ለህዳር 29 ቀን በዓል አከባበር የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የባህል ቡድን በሆሳዕና ከተማ ይገኛሉ።

በመጪው ሰኞ ለ20ኛ ጊዜ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የኢትዮጵያ ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ወደ ሆሳዕና ለገቡ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የባህል ልዑካን ቡድኖች በተለያዩ ቦታዎች ላይ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

በፌደሬሸን ምክር ቤት አሰተባባሪነት እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አሰተናጋጅነት ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት በሚል መሪ ሀሳብ የሚከበረዉ የ20ኛዉ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን በዓል ላይ ለመሳተፍ ወደ ሆሳይና ያቀኑ የክልሉ ተሳታፊዎች ሆሳዕና ገቡ ሲሆን በህዝቦች መካከል ጠንካራ የወንድማማችነት እሴት እንዲጎለብት የሚያግዙ ባህል በማንፀባረቅ ላይ ይገኛል።

"ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል ህዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ  በሚከበረዉ 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ...
06/12/2025

"ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል ህዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በሚከበረዉ 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል አከባበር ላይ ለመሳተፍ በጉዞ ላይ ለሚገኙ እንግዶች በተለያዩ አካባቢዎች የተደረገ አቀባበል - በፎቶ

#ፎቶ ኮባቱስ #

06/12/2025

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Kibru Wana, TemeYe Markos Abe, Endale Feleke, Aman Je

🙏ወዳጄ ባይጠቅምህም አይጎዳህም፤እስቲ አንቢበዉ🙏1.  ለሰው ምክር መስጠት ያለብህ ከጠየቀህ ወይም ከፈለገ ብቻ ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ሰዎች አብዝቶ የሚመክራቸውን ሰው አይወዱም፡፡ ያነሱ መስሎ...
26/11/2025

🙏ወዳጄ ባይጠቅምህም አይጎዳህም፤እስቲ አንቢበዉ🙏

1. ለሰው ምክር መስጠት ያለብህ ከጠየቀህ ወይም ከፈለገ ብቻ ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ሰዎች አብዝቶ የሚመክራቸውን ሰው አይወዱም፡፡ ያነሱ መስሎ ሊሰማቸውም ይችላል፡፡

2. ማንንም ሰው “ለምን እስካሁን አላገባህም/ሽም?" አይነት የግል ጥያቄዎችን አትጠይቅ። ወይም "ለምን ልጅ አልወለድክም/ሽም " አትበል፡፡ ይህ የነርሱ እንጂ ያንተ ጉዳይ አይደለም፡፡ እንዲህ አይነት ጥያቄ ሰዎችን ያሳቅቃል፡፡

3. አንድን ሰው (እንደሰማህ እያወቅክ) በተከታታይ ከሁለት ጊዜ በላይ አትጥራው፡፡ መልስ ካልሰጠህ ምናልባት የሆነ እየሰራው ያለው ነገር ሊኖር እንደሚችል ወይም በራሱ ምክንያት መልስ ሊሰጥህ እንዳልፈለገ ይግባህ፡፡

4. በር ከፍተህ ስትገባ ከኋላህ ወንድም ሆነ ሴት፣ ትልቅም ሆነ ትንሽ ሰው ቢኖር በሩ በላያቸው እንዳይዘጋ ያዝላቸው፡፡ ለሰዎች ትህትና ማሳየት አንተን ያስከብርህ ይሆናል እንጂ ትንሽ አያደርግህም፡፡

5. ሁሌም እኔ ብቻ ልክ ነኝ አትበል፡፡ ላንተ 6 ቁጥር የሚመስለው ለሌላው ሰው 9 ቁጥር ሊሆን ይችላል፡፡ ትክክልነት ካለህበት አንጻር የሚታይ አንጻራዊነት ነው፡፡ ካንተ የተለየ አስተያየት ማግኘት ይጠቅምሃል እንጂ አይጎዳህም፡፡

6. ሰው ሲናገር እስኪጨርስ ጠብቅ እንጂ አታቋርጥ፡፡ አንድ ሰው ለማለት የሚፈልገውን ሳይጨርስ አስተያየት መስጠት ወደስህተት ሊመራህ ይችላል፡፡

7. በሰዎች ላይ በቀልድ አታሹፍ፡፡ በተለይ ሹፈቱን ካልወደዱት ወዲያውኑ አቁም፡፡ እንዲህ ያለውን ነገር አለመድገም ለሰዎች ስሜት ምን ያህል እንደምትጠነቀቅ ማሳያ ነው፡፡

8. ሁሌም ሰዎች በጥያቄህ መሰረት ከረዱህ በኋላ “አመሰግናለሁ” ማለት ይልመድብህ፡፡

9. ሰዎች በስልካቸው ላይ ፎቶ እንድታይ ሲሰጡህ ያሳዩህን ብቻ አይተህ መልስ፡፡ ሳይፈቀድልህ ወደቀጣዩ ፎቶ አትሂድ፡፡ በድንገት የግል እና ማንም እንዲያየው የማይፈልጉትን ፎቶ አይተህ ቅር ልታሰኛቸው ትችላለህ፡፡

10. በመስሪያ ቤትህ ስራ አስፈጻሚም ይሁን ጽዳት ሰራተኛ ሁሉንም ሰው በአክብሮት ጥራ፡፡ ብዙዎች “ለሁሉ ትሁት ነው” የሚሉትን ሰው አብልጠው እንደሚወዱና እንደሚያቀርቡ እወቅ፡፡


11. አንተን በቀጥታ የሚመለከትህ ካልሆነ በቀር በሌላ ሰው ጉዳይ በተለይ በባለትዳርና በፍቅረኞች ጉዳይ ጣልቃ አትግባ፡፡

12. ማንኛውንም መልካም መልዕክት ከተቀበልህ በኋላ “ለመልእክቱ አመሰግናለሁ” በል፡፡

👉አስታዉስ ወዳጄ፣ ማወቅ መልካም ነዉ። ያወቁትን ማሳወቅ፣ፍፁም በጎነት ነዉ። እኛ በምድር ላይ በነፃ የምናደርጋቸዉ መልካም ነገሮች በሰማይ የዘላለም ደመወዝ ሆነዉ ይከፍሉልናል።🙏🙏🙏🌹🌹??🌹🙏🙏🙏
መንደር #

አርሰናል ባየር ሙኒክን አሸነፈ****************በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ 5ኛ ዙር ጨዋታ አርሰናል ባየር ሙኒክን 3 ለ 1 አሸንፏል፡፡በኤምሬትስ በተደረገው ጨዋታ ጁሪየን ቲምበር፣ ኖኒ...
26/11/2025

አርሰናል ባየር ሙኒክን አሸነፈ
****************

በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ 5ኛ ዙር ጨዋታ አርሰናል ባየር ሙኒክን 3 ለ 1 አሸንፏል፡፡

በኤምሬትስ በተደረገው ጨዋታ ጁሪየን ቲምበር፣ ኖኒ ማዱኬ እና ጋብርኤል ማርቲኔሊ የመድፈኞቹን ግቦች አስቆጥረዋል፡፡

ሌናርት ካርል የባየር ሙኒክን አንድ ግብ አስገኝቷል፡፡

የጀርመኑ ክለብ በውድድር ዓመቱ በሁሉም ውድድሮች ለመጀመርያ ጊዜ የተሸነፈበት ሆኗል፡፡

አርሰናል አምስቱንም የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለ ብቸኛው ክለብ ሆኖ በ15 ነጥብ እየመራም ይገኛል፡፡

በሳምንቱ መጨረሻ በሰሜን ለንደን ደርቢ ቶተንሀምን 4 ለ 1 ያሸነፈው አርሰናል በአውሮፓ ትልቁ ውድድር ጠንካራውን ቡድን ባየር ሙኒከን በማሸነፍ ግስጋሴውን አሳምሯል፡፡

መድፈኞቹ በ13ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በለንደን ደርቢ ከቼልሲ የሚገናኙም ይሆናል፡፡
#

Address

Addis Ababa

Telephone

+251967095778

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tame TK posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Tame TK:

Share