06/08/2026
ህዩዋ...ባላ ህዩዋ…. እንኳን አደረሳችሁ፡፡
ጳጉሜ 1 በታላቅ ድምቀት የሚከበረው "ህንግጫ" የልምላሜው መልክ፤ የኮንታ ብሔረሰብ አዲስ ዓመት፤
የኮንታ ብሔረሰብ በርካታ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ባህላዊ፣ ታሪካዊ እና ተፈጥሯዊ ቅርሶችና ዕሴቶች ባለቤት መሆኑ እሙን ነው፤ ከእነዚህ ውብ ዕሴቶች አንዱ የሆነው የብሔረሰቡ የዘመን መለወጫ/ህንግጫ/ በዓል አንዱ ነው።
የኮንታ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ /ህንግጫ/ በዓል በብሔረሰቡ ዘንድ በየዓመቱ በታላቅ ጉጉት ተጠብቆ የሚከበር ልዩ በዓል ሲሆን ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲሻገር ባህላዊ ይዘቱን ጠብቆ ነው፡፡ እሴቱ ሳይጎድልና ውበቱ ሳይደበዝዝ እዚህ የደረሰ የብሔረሰቡ የማንነት መገለጫም ነው፡፡
ህንግጫ በኮንታ ብሔረሰብ አጠራር ያማረ፣ ያጌጠ፣ የለመለመ ማለት ሲሆን አደይ አበቦች ፈክተው የሚታዩበት፣ የክረምቱ ወራት አልፎ የጠራ ሰማይ የሚታይበት፣ አርሶ አደሮች የክረምት አዝመራቸውን አገባደው ከአረምና ኩትኳቶ ስራ አርፈው ለመልካም ፍሬ ተስፋ የሚሰንቁበት ወቅት በመሆኑ በብሄረሰቡ ዘንድ በልዩ ትኩረትና በተስፋ የሚከበር ልዩ በዓል ነው።
የህንግጫ በዓል ሲከበር ከአሮጌው ዓመት ወደ አዲሱ ዓመት መሸጋገሪያ እንደመሆኑ በዕለቱ ሁሉም ጠግበው፣ ጎዶሎው ሞልቶ፣ ያለው ለሌለው አካፍሎ የሚበላበት፣ ድሃ ከሀብታም እኩል የሚያከብሩት፣ መጥፎ ነገር ሁሉ ቀርቶ መልካም መልካሙ እንዲሸጋገር ፈጣሪውን የሚለምንበት የጥጋብና ሙሉ የመሆን አስተምህሮ የሚገለፅበት የተስፋ በዓል ነው።
እንደ ባህሉ ትውፊት ህንግጫ ከጳጉሜ የመጨረሻዋ ቀን እስከ መስከረም 30 ድረስ ደምቆ ይከበራል። ከቤት እስከ ደጃፍ አካባቢ ይፀዳል፤ ከአሮጌው ዓመት የሚሻገር እድፍና ጉድፍ እንዳይኖር ይጠረጋል፤ ምድር ትዋባለች፡፡
ህንግጫ ከ12 ዓይነት በላይ የሆነው የኮንታ ባህላዊ ምግብ ተዘጋጅቶ የሚቀርብበት የባህል አውድም ነው፡፡ የዘመን መለወጫ በዓል ማብሰሪያ እሳት የሚወጣው ጳጉሜ የመጨረሻዋ ቀን ነው፡፡
በህንግጫ ወቅት ‹‹ሙጬ ›› ማለት ከጳጉሜ 1 እስከ ጳጉሜ 5/6 ድረስ ያሉ ቀናትን የሚያመላክት ሲሆን በእነዚህ ቀናት ዉስጥ እህል በተለይም ጤፍ ቢዘራ የማይበቅልና ቢበቅልም እንኳን ከግንዱ ተቆርጦ የሚወድቅና እንዲሁም ሳያድግ ቀጭጮ ስለሚቀር ወቅቱ ‹‹ ሙጬ ›› ተብሏል፡፡
በመሆኑም ‹‹ ሕንግጫ ›› የሚለዉ የብሔሩ የዘመን መለወጫ በዓል እንደሆነ የዕድሜ ባለፀጋዎችና የተለያዩ የታሪክ መጽሐፍቶች ይመሰክራሉ፡፡
የኮንታ ህዝብ የዘመን መለወጫ በዓል ማክበር የጀመረዉ በኦሞ፣ በጎጀብ እና በዝግና ተፋሰስ መኖር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በዓሉን ሲያከብሩ እንደ ነበረ ይነገራል፡፡
ሆኖም በዓሉ መቼና እንዴት ተጀምሮ እያደገ እንደመጣ ትክክለኛውን ጊዜ የሚጠቁም የጽሑፍ መረጃ ባይኖርም ለበዓሉ ታሪካዊ አመጣጥ የራሱ አመልካች መረጃዎች እንዳሉ ቀደምት አባቶች በአፈ-ታሪክ ያረጋግጣሉ፡፡
ይህም በኮንታ መንግሥት ተመስርቶ ግዛቱን ተቆጣጥሮ መኖር ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ማለትም የመጀመሪያው የአራ የዘር ግንድ ቀዳሚ ንጉስ “ከካቲ ኤማዶ” ዘመነ መንግስት በ12ኛዉ መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ ይበልጥ በተጠናከረ ሁኔታ በቤተሰብ ደረጃም ሆነ ከጎረቤት ጋር በጋራ በመሆን በዓሉን እያከበሩ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ መሆኑ በታሪክ ይነገራል፡፡
‹‹ህንግጫ›› ማለት እንደ ብሔሩ አባቶችና የታሪክ ምሁራን አገላለጽ የሁለት ቃላት የ‹‹ሂን›› እና የ‹‹ጊጫ›› ዉህድ ሲሆን ‹‹ሂን›› ማለት ወደዚያ አስፋ/ፊ ሲሆን ‹‹ጊጫ›› ማለት አሳምር፣ ጥረግ፣ አጽዳ፣ ፋቅ (Giid’ara) የሚል ትርጉም ይሰጣል፡፡
በመሆኑም ከዕለቱ በዓል ጋር የሚያ