05/05/2021
ቁርኣን እና ለይለቱል ቀድር
---
አፈንዲ ሙተቂ
----
አዎን! አላህ በለይለቱል ቀድር የሰጠን ትልቁ ስጦታ ቁርኣን ነው። ከመጽሐፎች ሁሉ በላጭ የሆነው ቅዱስ ቁርኣን የወረደው ለይለቱል ቀድር በተባለችው ታላቅ ሌሊት ነው። ይህንንም በቁርኣኑ ውስጥ በግልጽ ነግሮናል።
---
እስቲ በዚህች ታላቅ ሌሊት የወረደውን ቁርኣንን በአጭሩ እንቃኘው።
# ቅዱስ ቁርኣን 114 ምእራፎች (ሱራ) እና 6236 አንቀጾች (አያህ) ያሉት የአላህ ቃል ነው። በየወሩ ለማንበብ በሚያመች መልኩም በሰላሳ ጁዝእ (ክፍሎች) ተከፋፍሏል።
# ረጅሙ የቁርኣን ሱራ "አል በቀራህ" ሲሆን እርሱም 286 አንቀጾች አሉት።
# አጭር የሆኑት የቁርኣን ሱራዎች "አል ዐስር"፣ "አል ከውሠር" እና "አል ነስር" ሲሆኑ እያንዳንዳቸው ሶስት አንቀጾች አሏቸው።
# ረጅሙ የቁርኣን አንቀጽ በሱረቱል በቀራህ የሚገኘው 282ኛ አንቀጽ ነው። አጫጭሮቹ የቁርኣን አያዎች "ጣ ሃ"፣ "ሃ ሚም" እና "ያ ሲን" ናቸው።
# መጀመሪያ የወረደው የቁርኣን ሱራ "አል ዐለቅ" ሲሆን መጨረሻ ላይ የወረደው ሱራ "አል ነስር" ነው።
# በአንቀጽ ደረጃ ደግሞ መጀመሪያ የወረዱት የሱረቱል ዐለቅ አምስት አንቀጾች ሲሆኑ መጨረሻ ላይ የወረደው የሱረቱል ማኢዳ ሶስተኛ አንቀጽ (አያህ) ነው።
# የቁርኣን ሱራዎች በመጽሐፉ ውስጥ የተቀመጡት በወረዱበት ቅደም ተከተል ሳይሆን ለውሀል ማሕፉዝ (ጥብቁ ሰሌዳ) በሚባለው ታላቁ ሰሌዳ ላይ በተጻፉበት መልክ ነው።
# የቁርኣን አወራረድ ሁለት መልሶ አለው። መጀመሪያ ላይ ከለውሐል ማሕፉዝ (የተጠበቀው ሰሌዳ) ላይ ተወስዶ "ለይቱል ቀድር" በምትባለው ታላቋ የረመዳን ሌሊት፣ በቅርቢቷ ሰማይ በሚገኘው ቤይቱል ማእሙር በሚባለው ቤት ወደ መልአኩ ጂብሪል ወርዷል።
# ቁርኣኑ ወደ ጂብሪል የወረደው በተሟላ ሁኔታ እና በለውሐል ማሕፉዝ ላይ ያለውን የሱራዎችና የአያዎች ቅደም ተከተል በጠበቀ መልኩ ነው።
# የነቢዩ ሙሐመድ መልእክተኛነት ከተበሰረ በኋላ ደግሞ ጂብሪል ቁርኣኑን በምእራፎችና በአንቀጾች እየከፋፈለ በ23 ዓመታት ውስጥ በነቢዩ ሙሐመድ (ሰዐወ) ላይ አውርዷል።
# ነቢዩ ሙሐመድም (ሰዐወ) ወሕዩን ከጂብሪል መቀበል የጀመሩት በወርሃ ረመዳን "ለይቱል ቀድር" በምትባለው ትልቋ ሌሊት ነው። "ረመዳን" የወራቶች ንጉሥ የሚባለው በዚሁ ምክንያት ነው።
----
አላህ ለይቱል ቀድርን ከሚወፍቃቸው ያድርገን።
---
(ሼር ብታደርጉት አጅሩ ለእናንተም ለእኔም ነው። ጀዛኩሙላህ)