Top Consulting Center /TCC/

Top Consulting Center /TCC/ Training Center

25/07/2022

ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው ታሪክ ከፍተኛውን ሜዳሊያ በማግኘት አጠናቀቀች‼

ላለፉት 10 ቀናት በአሜሪካ ኦሪገን ሲካሄድ የሰነበተውን 18ኛውን የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በታሪኳ ከፍተኛውን ሜዳሊያ በማግኘት አጠናቃለች፡፡

በወንዶች እና ሴቶች ማራቶን እንዲሁም በ10ሺ እኛ 5 ሺ ሜትር ሴቶች 4 ወርቅ በማምጣት በሻምፒዮናው ከፍተኛ የሚባል ውጤት ተመዝግቧል፡፡

በ3ሺ ሜትር መሰናክል በሴት እና ወንድ እንዲሁም በወንዶች ማራቶን እና በ1500 ሜትር ሴቶች የብር ሜዳሊያ ተገኝቷል፡፡

ሁለቱ የነሐስ ሜዳያ የመጣው ደግሞ በሴቶች 3ሺ መሰናክል እና በ5ሺ ሜትር ነው፡፡

ኢትዮጵያ በድምሩ 10 ሜዳሊያዎችን በማግኘት ከአፍሪካ ቀዳሚ፣ ከዓለም ደግሞ ከአሜሪካ በመቀጠል 2ኛ ደረጃ ላይ በመቀመጥ በሻምፒዮናው ታሪክ ከፍተኛው ሜዳሊያ በማግኘት አጠናቃለች፡፡

ጎረቤት ኬንያ ደግሞ በ2 ወርቅ ፣5 የብር እና 3 የነሀስ በድምሩ 10 ሜዳሊያ በማግኘት በኢትዮጵያ በሁለት ወርቅ ተበልጣ ከአፍሪካ 2ኛደረጃን ይዛ አጠናቃለች፡፡

24/07/2022

በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና አትሌቶቻችን ተጨማሪ ሜዳሊያ ለማስገኘት ዛሬ ሌሊት ይፋለማሉ
*************************

በ18ኛው የኦሪገን የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ አትሌቶች ለሀገራቸው ተጨማሪ ሜዳሊያዎችን ለማስገኘት ዛሬ ሌሊት በሚደረጉ ሁለት የፍፃሜ ውድድሮች ላይ ይፋለማሉ።

ተጠባቂው የወንዶች 5 ሺህ ሜትር የፍፃሜ ውድድር ከሌሊቱ 10:05 ሰዓት ጀምሮ ይካሄዳል።

በዚህ ውድድር አትሌት ሰለሞን ባረጋ፣ አትሌት ሙክታር ኢድሪስ እና አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ እና እስካሁን የተገኘውን የሜዳሊያ ቁጥር ከፍ ለማድረግ የሚፋለሙ ይሆናል።

በቶኪዮ ኦሎምፒክ የ10 ሺህ ሜትር ውድድር ለሀገሩ ብቸኛውን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኘው አትሌት ሰለሞን ባረጋ በውድድሩ ይጠበቃል።

በሌላ በኩል የሴቶች 800 ሜትር የፍጻሜ ውድድር ሌሊት 10:35 ሲደረግ፣ በርቀቱ ኢትዮጵያን ወክላ ለፍፃሜው ያለፈችው ብቸኛዋ አትሌት ድርቤ ወልተጂ እንደ ሌሎቹ የሀገሯ ልጆች ደማቅ ታሪክ ለመጻፍ ትፋለማለች።

10ኛ ቀኑን በያዘው የኦሪገን አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ እስካሁን 4 የወርቅ፣ 4 የብር እና 2 የነሐስ ሜዳሊያ በድምሩ 10 ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ በሜዳሊያ ሰንጠረዡ ከአሜሪካ ቀጥላ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።

ኢትዮጵያ በ18ኛው የኦሪገን የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ስታደርገው የነበረው ተሳትፎ ዛሬ ሌሊት በሚደረጉ ሁለቱ ውድድሮች ይገባደዳል።

24/07/2022
24/07/2022

እንኳን ደስ አለን!!

የዓለም የሴቶች 5000 ሜትር ፍጻሜ ውድድርን አትሌት #ጉዳፍ ፀጋዬ አሸነፈች።

በአሜሪካ ኦሬገን በተካሄደው 18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የሴቶች 5,000 ሜትር የፍጻሜ ውድድርን አትሌት #ጉዳፍ ፀጋዬ አንደኛ በመውጣት ወርቅ፣ #ዳዊት ስዩም ሶስተኛ በመውጣት ነሀስ በማገኘት ታሪክ ሰርተዋል ፡፡ አትሌት #ለተሰንበት ግደይ 5ኛ በመሆን አጠናቃለች።

ኢትዮጵያ ዛሬም በልጆቿ ኮርታለች!
እንኳን ደስ አለን!

21/07/2022

ወርቅውሃ ጌታቸውና
መቅደስ አበበ
በ3000 ሜትር መሰናክል ብርና ነሃስ በማምጣት
የሀገራችንን ባንዲራ ከፍ አድርገውልናልና ምስጋና ይገባቸዋል!!

20/07/2022

#ድል ቀንቶናል !!!🇪🇹🇪🇹🇪🇹

#በ3000 ሜትር መሰናክል ሴቶች ኢትዮጵያ በተሳተፈችበት ርቀት ሁለት አትሌቶች ለፍፃሜ አልፈዋል።

#ረቡዕ ለሊት 11:45 ለሚደረገው የሴቶች 3,000ሜ መሠናክል ፍጻሜ ያለፉት አትሌቶች፦
👉 ወርቅውሃ ጌታቸው 9:11.25 ሁለተኛ በመውጣ ከአንደኛ ምድብ
👉 መቅደስ አበበ 9:14.83 ሁለተኛ በመውጣት ከሁለተኛ ምድብ

ድል ለአትሌቶቻችን💪🇪🇹💪🇪🇹💪🇪🇹
#ኢቢኤስ

19/07/2022

በወንዶቹ ማራቶን እልህ አስጨራሽ ትንቅንቅ ሪከርድን የሰበረው ታምራት ቶላ🌷 እንኳን ደስ አላችሁ🌷🙏

19/07/2022

በሴቶች 1500 ሜትር ፍፃሜ ጉዳፍ ፀጋዬ የብር ሜዳልያ
አትሌት ለሜቻ ግርማ በ3000 መሰናክል የብር ሜዳልያ

18/07/2022

አትሌት ጎይተቶም ገብረስላሴ 3ኛውን የወርቅ ሜዳልያ ለኢትዮጵያ አስገኘች

በኦሪገን እየተካሄደ በሚገኘው 18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ተጨማሪ የወርቅ ሜዳልያ አገኘች።

ከሰአት በኋላ በተካሄደው የሴቶች የማራቶን ውድድር አትሌት ጎይተቶም ገብረስላሴ ውድድሩን በአሸናፊነት አጠናቃለች።

ኢትዮጵያም 3ኛውን የወርቅ ሜዳልያ በውድድሩ አግኝታለች።

25/04/2022

We are providing training on:Different Bank payment system on international procurements IncotermsConsulting on International and National bids Custom procedures etc.

24/04/2022

we are providing:
1. International procurement
2. National procurement
3. International trade
4. World Bank procurement procedure
5. Kaizen
6. Leadership etc trainings by more trained and exprienced professionals in the field.

Address

Addis Ababa

Telephone

+251925964013

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Top Consulting Center /TCC/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Top Consulting Center /TCC/:

Share