Grand African Organizational and Leadership Award Organization

Grand African Organizational and Leadership Award Organization award for an outstanding achievement that has saved the world and it's people!

25/05/2026

በታክስ አስተዳደር አዋጅ ማሻሻያ ረቂቅ ላይ ከባለድርሻ አካላት አስተያየት ለማሰባሰብ እና ውይይት ለማድረግ የተደረገ ጥሪ የታክስ አስተዳደር ሥርዓቱን ይበልጥ ቀልጣፋ፣ ፍትሃዊ እና ከወቅቱ የ...
15/05/2026

በታክስ አስተዳደር አዋጅ ማሻሻያ ረቂቅ ላይ ከባለድርሻ አካላት አስተያየት ለማሰባሰብ እና ውይይት ለማድረግ የተደረገ ጥሪ

የታክስ አስተዳደር ሥርዓቱን ይበልጥ ቀልጣፋ፣ ፍትሃዊ እና ከወቅቱ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ጋር የተጣጣመ ለማድረግ ይቻል ዘንድ፤ ነባሩን የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 ለማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል። በዚህም መሠረት የገንዘብ ሚኒስቴር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ አዘጋጅቷል።

የሕጉ ረቂቅ ጸድቆ ወደ ሥራ ከመግባቱ በፊት፣ በሕጉ ቀጥተኛ ተገዢ የሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎችንና ባለሙያዎችን ማሳተፍ፣ ግብዓት
መሰብሰብና ግልጽ ውይይት ማድረግ አፈላጊ በመሆኑ፣ የታክስ አስተዳደር አዋጅ ማሻሻያ የሚመለከታችሁ ግብር ከፋዮች፣ የንግዱ ማኅበረሰብ አባላት፣ የሕግና የኢኮኖሚ ባለሙያዎች እንዲሁም ፍላጎት ያላችሁ የኅብረተሰብ ክፍሎች በሙሉ ግንቦት 11 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ ስድስት ኪሎ በሚገኘው የገንዘብ ሚኒስቴር ዋና መሥሪያ ቤት ቅጥር ግቢ፤በአካል በመገኘት አስተያየታችሁን እንድትሰጡ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

በተጨማሪም፣ በረቂቅ አዋጁ ላይ የጽሑፍ አስተያየት መስጠት ለምትፈልጉ አካላት፣ የአዋጁን ዝርዝር የድንጋጌዎች ረቂቅ (በአማርኛ ቅጂ) በገንዘብ ሚኒስቴር ድኅረ-ገጽ ላይ መመልከት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን፤ ያዘጋጃችሁትን ዝርዝር አስተያየት እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በኢሜይል አድራሻ [email protected] እንድትልኩልን በአክብሮት እንጋብዛለን።

Website link :-https://www.mofed.gov.et/media/filer_public/ea/58/ea58858b-a3c1-4640-88c6-dadac6fe088a/yataakese_asetadaadare_awaaje_maashaashaayaa_amaarenyaa_05152026_second_draft_clean.pdf

  ግራንድ አፍሪካን የተቋማትና የአመራር ሽልማት ድርጅት፣ የማህበራዊ ሚዲያ ማኔጅመንት እና የዌብሳይት ግንባታ አገልግሎቶችን የሚሰጡ ብቁ ድርጅት ወይም ባለሙያዎችን ማሰራት ይፈልጋል።• የማህ...
15/05/2026


ግራንድ አፍሪካን የተቋማትና የአመራር ሽልማት ድርጅት፣ የማህበራዊ ሚዲያ ማኔጅመንት እና የዌብሳይት ግንባታ አገልግሎቶችን የሚሰጡ ብቁ ድርጅት ወይም ባለሙያዎችን ማሰራት ይፈልጋል።
• የማህበራዊ ሚዲያ ማኔጅመንት፡
o የድርጅታችንን የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች (Facebook, Instagram, LinkedIn, YouTube, TikTok) ማስተዳደር እና ይዘቶችን ማፍለቅ።
o የጥራት እና ወቅታዊ ይዘቶችን በማዘጋጀት የተጠቃሚዎችን ተሳትፎ ማሳደግ /Boosting/።
o የማህበራዊ ሚዲያ ማስታወቂያዎችን በማዘጋጀት እና በማስተዳደር የድርጅቱን ስም እና አገልግሎቶች ለሰፊው ህዝብ ማስተዋወቅ።
o የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን በተመለከተ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ግንዛቤዎችን በማቅረብ ድርጅቱ በዲጂታል ዓለም የበላይነቱን እንዲያገኝ ማስቻል።
• የዌብሳይት ግንባታ፡
o የድርጅታችንን የዌብሳይት ግንባታ እና ጥገና ማከናወን።
o የጥራት እና የተጠቃሚ-ተስማሚ ዌብሳይት በመገንባት የድርጅቱን አገልግሎቶች እና ሽልማቶችን ለሰፊው ህዝብ ማስተዋወቅ።
o የዌብሳይት አጠቃቀምን በተመለከተ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ግንዛቤዎችን በማቅረብ ድርጅቱ በዲጂታል ዓለም የበላይነቱን እንዲያገኝ ማስቻል።
• ሌሎች መስፈርቶች፡
o ለግለሰቦች በዘርፉ ቢያንስ የሁለት ዓመት የስራ ልምድ ያለው። በተጨባጭ የሰሯቸውን የስራ ልምዶች ማቅረብ የሚችሉ፡፡
o ለስራው አፈጻጸም ፕሮፖዛል ሰርተው የሚያቀርቡ፡፡
o ለድርጅቶች ህጋዊ ፈቃድ ያላቸው፡፡ ቢሮና አድራሻ ያላቸው፡፡
o ለስራው ውል መዋዋል የሚችሉ፡፡
o የሰሯቸውን ስራዎች ናሙና የሚያቀርቡ፡፡
o ለስራው አፈጻጸም ፕሮፖዛል ሰርተው የሚያቀርቡ፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በስራ ሰዓት በ0911-24 83 68 ደውለው ይጠይቁ፡፡









14/05/2026

10/05/2026

ግራንድ አፍሪካን የተቋማትና የአመራር ሽልማት ድርጅት፣ የማህበራዊ ሚዲያ ማኔጅመንት እና የዌብሳይት ግንባታ አገልግሎቶችን የሚሰጡ ብቁ ድርጅት ወይም ባለሙያዎችን ማሰራት ይፈልጋል።• የማህበራ...
08/05/2026

ግራንድ አፍሪካን የተቋማትና የአመራር ሽልማት ድርጅት፣ የማህበራዊ ሚዲያ ማኔጅመንት እና የዌብሳይት ግንባታ አገልግሎቶችን የሚሰጡ ብቁ ድርጅት ወይም ባለሙያዎችን ማሰራት ይፈልጋል።
• የማህበራዊ ሚዲያ ማኔጅመንት፡
o የድርጅታችንን የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች (Facebook, Instagram, LinkedIn, YouTube, TikTok) ማስተዳደር እና ይዘቶችን ማፍለቅ።
o የጥራት እና ወቅታዊ ይዘቶችን በማዘጋጀት የተጠቃሚዎችን ተሳትፎ ማሳደግ /Boosting/።
o የማህበራዊ ሚዲያ ማስታወቂያዎችን በማዘጋጀት እና በማስተዳደር የድርጅቱን ስም እና አገልግሎቶች ለሰፊው ህዝብ ማስተዋወቅ።
o የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን በተመለከተ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ግንዛቤዎችን በማቅረብ ድርጅቱ በዲጂታል ዓለም የበላይነቱን እንዲያገኝ ማስቻል።
• የዌብሳይት ግንባታ፡
o የድርጅታችንን የዌብሳይት ግንባታ እና ጥገና ማከናወን።
o የጥራት እና የተጠቃሚ-ተስማሚ ዌብሳይት በመገንባት የድርጅቱን አገልግሎቶች እና ሽልማቶችን ለሰፊው ህዝብ ማስተዋወቅ።
o የዌብሳይት አጠቃቀምን በተመለከተ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ግንዛቤዎችን በማቅረብ ድርጅቱ በዲጂታል ዓለም የበላይነቱን እንዲያገኝ ማስቻል።
• ሌሎች መስፈርቶች፡
o ለግለሰቦች በዘርፉ ቢያንስ የሁለት ዓመት የስራ ልምድ ያለው። በተጨባጭ የሰሯቸውን የስራ ልምዶች ማቅረብ የሚችሉ፡፡
o ለስራው አፈጻጸም ፕሮፖዛል ሰርተው የሚያቀርቡ፡፡
o ለድርጅቶች ህጋዊ ፈቃድ ያላቸው፡፡ ቢሮና አድራሻ ያላቸው፡፡
o ለስራው ውል መዋዋል የሚችሉ፡፡
o የሰሯቸውን ስራዎች ናሙና የሚያቀርቡ፡፡
o ለስራው አፈጻጸም ፕሮፖዛል ሰርተው የሚያቀርቡ፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በስራ ሰዓት በ0911-24 83 68 ደውለው ይጠይቁ፡፡









ማስታወቂያየአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ከተማ አስተዳደሩ በልዩ ትኩረት እየተገበረ ለሚገኝው መጠነ ሰፊ የቤት ልማት ፕሮግራም በግንባታው ዘርፍ ላይ የተሰማሩ እና መስፈርቱን የሚ...
07/05/2026

ማስታወቂያ

የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ከተማ አስተዳደሩ በልዩ ትኩረት እየተገበረ ለሚገኝው መጠነ ሰፊ የቤት ልማት ፕሮግራም በግንባታው ዘርፍ ላይ የተሰማሩ እና መስፈርቱን የሚያሟሉ ስራ ተቋራጮችን አወዳድሮ ለማሰራት ይጋብዛል ፡፡

በዚህም መነሻ

1. ለስራ ተቋራጮች ምዝገባ መሟላት
ያለባቸው መረጃዎች፡-

ሀ) የታደሰ የንግድ ፍቃድ ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፍኬት ፣ የታደሰ የብቃት ማረጋገጫ ምዝገባ ሰርተፍኬት እና የአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ ስለመመዝገቡ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፤

 በምዝገባው ወቅት የሰነዶቹን ዋና እና አንድ የማይመለስ ቅጂ በአካል የሚቀርብ ሆኖ የስራ ተቋራጩ የበላይ ኃላፊ ባለቤት ወይም ህጋዊ ውክልና ያለው ተወካይ ፊርማ እና የድርጅቱ ህጋዊ ማህተም በማድረግ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡

2. ደረጃ 1 እና 2 (ህንፃ (BC) እና ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ(GC)) እንዲሁም ደረጃ- 3 (ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ (GC)) የብቃት ማረጋገጫ ያላቸው በግንባታው ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ስራ ተቋራጮች ተሳታፊ መሆን ይችላሉ

3. ከዓርብ ሚያዝያ 30 ቀን 2018 ዓ/ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ ቅዳሜን ጨምሮ ለ5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት ( እስከ ዕሮብ ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ/ም ከሰዓት እስከ 11፡30)) በአካል በመቅረብ በኮርፖሬሽኑ 11ኛ ወለል በሚገኝ አዳራሽ ላይ ምዝገባ በማድረግ መረጃዎቹ መሟላታቸው በመዝጋቢው ሲረጋገጥ ለዚሁ የተዘጋጀ የቴክኒካል ሰነድ መግዛት ይቻላል፤

4. ተገቢውን ሰነድ በማቅረብ የምዝገባ ሂደቱን በሚገባ ያሟላ ስራ ተቋራጮችን በተመለከተ ምዝገባው በተጠናቀቀ በ 24 ሰዓት ውስጥ ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ/ም በተቋሙ ማህበራዊ ድህረ ገጽ እና በኮርፖሬሽኑ የማስታወቂያ ቦርድ 11ኛ ወለል የሚለጠፍ ይሆናል፡፡

5. ስራ ተቋራጮች የቅድመ ምዝገባ ውጤት ከታወቀበት ቀን ቅዳሜን ጨምሮ በአስር (10) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ አንድ ኦርጅናል እና ሁለት ቅጂ የቴክኒካል ፕሮፖዛላችሁን ለዚሁ በተዘጋጀ ሳጥን እስከ ቀን ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ/ም ከሰዓት 10፡00 ድረስ ብቻ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡

6. ስራ ተቋራጮች ለምዝገባ እና ለቴክኒካል ሰነድ ግዢ
የማይመለስ ብር

ለደረጃ 1 ...........ብር 7500
ለደረጃ 2 .......... ብር 6500
ለደረጃ 3 ...........ብር 5500 መክፈል ይጠበቅባቸዋል፡፡

አድራሻ

 ቂርቆስ ክ/ተማ ወረዳ 01
ባምቢስ አከባቢ ግሪክ ት/ቤት ፊት ለፊት በሚገኘው
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት አስተዳደር ህንፃ ላይ ፦

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጭ፦
https://linktr.ee/aahdc

የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

ሚያዝያ 29 ቀን 2018 ዓ/ም

ሊያመልጥዎ የማይገባ ታላቅ የገለጻና ውይይት መድረክ!             *****************የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ወቅታዊና ሀገራዊ ፋይዳ ባላቸው ጉዳዮች ላይ ሳይንሳዊ ውይይቶችን...
06/05/2026

ሊያመልጥዎ የማይገባ ታላቅ የገለጻና ውይይት መድረክ!
*****************
የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ወቅታዊና ሀገራዊ ፋይዳ ባላቸው ጉዳዮች ላይ ሳይንሳዊ ውይይቶችን የማካሄድ ተልዕኮውን መሠረት በማድረግ “የገጠር ትራንስፎርሜሽን በኢትዮጵያ: ከግብርና ወደ መዋቅራዊ ሽግግር ትልም’’ በሚል ርዕስ የገለጻና ውይይት መርሐግብ አዘጋጅቷል።

በዕለቱም የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ማንደፍሮ ንጉሤ ሰፊ ገለጻ የሚያደርጉ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ፕሬዝዳንት በፕሮፌሰር በላይ ካሳ አወያይነት ውይይቱ ይመራል።

ስለሆነም የዘርፉ ባለሙያዎች፣ ጋዜጠኞችና ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች በሙሉ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት በአካል በመገኘት በውይይቱ ላይ እንድትሳተፉ በአክብሮት ተጋብዘዋል።
መርሐ-ግብሩ፦
🗓ቀን፦ ነገ ሐሙስ ሚያዝያ 29 ቀን 2016 ዓ.ም
⏰ሰዓት፦ ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ
📍ቦታ፦ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ 5 ኪሎ ካምፓስ (AAiT) አዳራሽ
በአካል መገኘት ለማትችሉ በዙም (Zoom) ወይም በፖስተሩ ላይ ያለውን QR code በመጠቀም መከታተል ትችላላችሁ፦
የZoom አድራሻ፦
🔗Link: https://us06web.zoom.us/j/87449049928?
pwd=o6WgdwZJsmMK88hbsRVDGf8aIOs6ZH.1
💡Meeting ID: 874 4904 9928
🗝Passcode: 378609

Address

Djibouti Street
Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Grand African Organizational and Leadership Award Organization posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share