Ethiopian Management Institute/EMI/ የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • Ethiopian Management Institute/EMI/ የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት

Ethiopian Management Institute/EMI/ የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት Ethiopian Competency and Management Institute (ECMI) is a goverenment
enterprise that has been operating in Ethiopia as a service provider since 1958.

It is the leading management development service provider in the country.

በድህረ ምርጫ ወቅት የሲቪል ሰርቫንቱ ሚና ላይ ያተኮረ ውይይት በኢንስቲትዩቱ ተካሄደ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብቃትና ሥራ አመራር...
19/06/2026

በድህረ ምርጫ ወቅት የሲቪል ሰርቫንቱ ሚና ላይ ያተኮረ ውይይት በኢንስቲትዩቱ ተካሄደ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብቃትና ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት አመራሮችና ሠራተኞች በድህረ ምርጫ ወቅት የሲቪል ሰርቫንቱ ሚና ላይ ያተኮረ የግማሽ ቀን ውይይት በኢንስቲትዩቱ ዋና መ/ቤትና በቢሾፍቱ ማሰልጠኛ ማዕከል አካሄዱ።

የመድረኩን ዓላማ አስመልክቶ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ደሳለኝ ጣሰው በቅድሚያ ከምርጫ ጊዜው በፊት እና በምርጫው ሂደት ወቅት አስቻይ ሁኔታዎች እንዲፈጠር መደረጉ፤ ከ50 ሚሊዮን በላይ ዜጎችም ፍፁም ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ያስተዳድረኛል ያሉትን መምረጥ መቻላቸው ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ አድርገዋል ብለዋል።

እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ገለፃ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት በሀገራችን እየተገነባ መሆኑና ዜጎች ሁልጊዜ ለሀገሪቱ ሠላምና ፀጥታ ቅድሚያ የሚሰጡ መሆኑን የተማርንበትና ለሌሎች ሀገራት መልካም ገፅታችንን ያሳየንበት ነው ብለዋል።

የዛሬው መድረክም በቀጣዩ አዲስ ዓመት በመስከረም
ወር በምርጫ ቦርድ አሸናፊው ከተነገር በኋላ መንግስት የሚመስርተው ፓርቲ እስከሚታወቅና ርክክብ እስኪደረግ ድረስ በድህረ ምርጫ ወቅት እንደ ሲቪል ሰርቪስ ተቋም የሚጠበቁብን ተግባራት ላይ መወያያት እንደሆነ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር በመክፈቻ ንግግራቸው አመላክተዋል።

የኢንስስቲትዩቱ የሰው ሀብትና ስትራቴጂክ ሥራ አመራር ጽ/ቤት ሥራ አስፈፃሚ አቶ አብዱልሃሊቅ ረሺድ በድህረ ምረጫ ወቅት ሲቪል ሰርቫንቱ ሊተገበሩ ስለሚገባቸው ዋና ዋና ተግባራትን በተመለከተ መነሻ ሐሳብ አቅርበው፤ የኢንስቲትዩቱ ሠራተኞችም መነሻ ሐሳቡን መሠረት በማድረግ ውይይት ከተካሄደ በኋላ የዕለቱ መድረክ ተጠናቋል።

የኢትዮጵያ ብቃትና ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት በአዲስ መልክ ከተቋቋመ ቦርድ አባላት ጋር ትውውቅ አደረገ!የኢንስቲትዩቱ በርድ 9 አበላት ያሉት አዲስ ቦርድ በይፋ ተመስርቶ ወደ ስራ በዛሬው ዕለ...
25/05/2026

የኢትዮጵያ ብቃትና ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት በአዲስ መልክ ከተቋቋመ ቦርድ አባላት ጋር ትውውቅ አደረገ!
የኢንስቲትዩቱ በርድ 9 አበላት ያሉት አዲስ ቦርድ በይፋ ተመስርቶ ወደ ስራ በዛሬው ዕለት ግንቦት 15 ቀን የመጀመሪያውን የትውውቅ ስብሰባውን በሂልተን ሆቴል አድርጋል፡፡
ክቡር አቶ ደሳለኝ ጣሰው የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተርና የቦርዱ አባልና ጸሀፊ በመክፈቻ ንግግራቸው ኢንስቲትዩት የዛሬዉ አዲሱ ማንነት በአዋጅ ቁጥር 1353/2017 እና በሚንስትሮች ምክር ቤት በደንብ ቁጥር 584/2018 የተሰጠውን ተግባርና ኃላፊነት መሰረት በማድረግ በምናበስረው ሽግግር እና ባለፉት አስር ወራት የተከናወኑ መደበኛና የሪፎርም ስራዎች ውይይት በተዘጋጀው በዚህ የትውወቅ መድረክ ለመሳተፍ እንኳን በሰላም መጣችሁ በማለት አዲስ ለተቋቋመው ቦርድ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
በንግግራቸውም የኢንስቲትዩቱን ታሪካ ዳራ ለአገር ያደረገው አስተዋጽሆ ከፍተኛ መሆኑን በመግልጽ በሃገራዊ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ዉስጥ ከነበረዉ ተልኮ በተጨማሪ አዲስ ተልዕኮ በተሰጠው መሰረት ተቋማችን ሃገር አቀፍ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርምን በበላይነትና በከፍተኛ ሃላፊነት ለሚያስተባብረዉ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ተጠሪ ሆኖ በመንግሰት በኩልም በጀት እየተመደበለት የመንግስት ሰራተኞችንና አመራሮችን ብቃት የመመዘንና የማረጋገጫ ምስክር ወረቀት የመስጠት፣ የብቃት ምዘና መሳሪያዎችን ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ ማስተዳደርና ስራ ላይ እንዲውል ማድረግ፣ ለሁሉም የፌደራል መንግስት ተቋማት ብቃት ያለው የሰው ኃይል በማዕከል ደረጃ ቅጥር መፈጸም፣ ብቃታቸው ተረጋግጦ ዝቅተኛውን የማለፊያ ነጥብ ያላመጡትን ሰራተኞችና አመራሮች በአጫጭር ሞጁላርና በተጨማሪ ስልጠና መገንባት፣ የመንግስት ተቋማትን የመፈጸም አቅም ለማሳደግ የማማከር አገልግሎት መስጠት እንዲሁም እንደ አዲስ በተሰጠው ተግባርና ኃላፊነት ዙሪያ ጥናትና ምርምር እያደረገ ለመንግስት ለፖሊሲ ዝግጅት ግብዓትነት እንዲውል የማድረግ የሚሉት ዋና ዋና ተግባርና ኃላፊነቶች ተሰጠውት ስያሜውም የኢትዮጵያ ብቃትና ስራ አመራር ኢንስቲትዩት እየተባለ እንዲጠራ ተደርጓል፡፡
በመሆኑም ኢንስቲትዩቱ በመንግስት በኩል የተሰጡትን ተግባርና ኃላፊነቶች መሰረት በማድረግ በመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ማስተግበሪያ ፖሊሲ ሰነድ የተቀመጡትን ቁልፍ አምዶች በራሱ ላይ ተግብሮ በሌሎች የመንግሰት ተቋማት ሳይቆራረጥ የማስተግበር ኃላፊነት ስላለበት ከመስከረም 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሰባቱ አምዶች እና በሁለቱ አስተዳደራዊ ማሻሻያ ሪፎርም ስራዎች የተቀመጡትን ዋና ዋና ተግባራት እሁድን እንደ ሰኞ በመቁጠር እያከናወነ ይገኛል በማለት የመክፈቻ ንግግራቸውን አድረገዋል፡፡
በመቀጠልም የቦርዱ ሰብሳቢ ክቡር ዶ/ር ጌታቸው ጀንበር የኢትዮጵ ብቃትና ስራ አመራር ቦርድ ኮሚቴ ስብሳቢ ኢንስቲትዩቱ የተሰጠውን ትልቅ አገራዊ ኃላፊነት መወጣት አንዲችል ቦርዱ ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለብን አውቀን ስራችን በከፍተኛ ትጋት ማከናወን ይኖርብናል በማለት ትውውቅ እንዲደረግ አድረገዋል፡፡
የኢንስቲትዩቱ የመደበኛ ስራዎች አፈጻጸም፣የተከናወኑ ሪፎርም ስራዎች እና የተቋም አደረጃጀት ጥናት ለቦርዱ እንዲቀርብ የተደረገ ሲሆነ የቦርዱም ሰብሳቢ ለውውይት አቅረበወት ውይይት የተደረገበት ሲሆን በቀጣይ ስብሰባዎች ኢንስቲትዩቱ የሚያቀርባቸውን የውስጥ አሰራር ልዩ ልዩ መመሪያዎች ለማጽደቅ እና የአደረጃጀት መመሪያው ላይ ተወያይቶ ሃሳብ ለማቅረብ ቀጠሮ በመያዝ የትውውቅ ስብሰባው ተጠናቋል፡፡

ለመላው ክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው/ለፋሲካ በዓል አደረሳችሁ።የትንሳኤ በዓል ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ያለውን ፍቅር እስከ ቀራንዮ ድረስ የገለፀበትና ዳግም ሞት...
11/04/2026

ለመላው ክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው/ለፋሲካ በዓል አደረሳችሁ።

የትንሳኤ በዓል ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ያለውን ፍቅር እስከ ቀራንዮ ድረስ የገለፀበትና ዳግም ሞትን ሽሮ መቃብር ፈንቅሎ የተነሳበት ታላቅ በዓል ነው።

በዚህ በዓል ፍቅር የተገለፀበት እንደመሆኑ ሁላችንም በአንድነትና በመተሳሰብ በመረዳዳት የምናከብረው በዓል ነው።

ይህ ታላቅ በዓል የሠላም የፍቅር የመተሳሰብና የመደጋገፍ እንዲሆንልንም እመኛለው።

አቶ ደሳለኝ ጣሰው
የኢትዮጵያ ብቃትና ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
ዋና ዳይሬክተር

ኢንስቲትዮቱ ሠራተኞችና አመራሮች በሀገራዊ ወቅታዊ ሁኔታና ሪፎርም ላይ ውይይት አደረጉ።            ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የትንሳኤን በዓል ምክንያትም የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም ተከናወ...
08/04/2026

ኢንስቲትዮቱ ሠራተኞችና አመራሮች በሀገራዊ ወቅታዊ ሁኔታና ሪፎርም ላይ ውይይት አደረጉ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የትንሳኤን በዓል ምክንያትም የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም ተከናወነ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ ብቃትና ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት አመራሮችና ሠራተኞች በሀገራዊ ወቅታዊ ሁኔታና ሪፎርም ላይ መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በኢንስቲትዩቱ ዋና መ/ቤት ተካሄደ።

ሀገራችን ኢትዮጵያ በሀገር አቀፍ ደረጃ የምታካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ አሁን እየተካሄደ ባለበት ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ መንገድ ከዳር ለማድረስ መንግስት እየሰራ እንደሆነ የገለፁት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ደሳለኝ ጣሰው የኢንስቲትዩቱ ማህበረሰብም በፍቃደኝነት ላይ በተመሰረተ ምዝገባ በማከናወን የሚምረጠውን ፓርቲ መንግስት ማድረግ መብት አለው ብለዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የተጀመሩ የብልፅግና ሥራዎችንና የዴሞክራሲያዊ ሥርዓቱን ለማኮላሸት ከጠላት ጋር የሚሰሩ የሀገራችን ዕድገት የማይዋጥላቸው በተለያየ መንገድ ያልተገቡ መረጃዎችን የሚያሰራጩ መኖራቸው ቢታወቅም እውነታውን እንዲያውቁና እንዲገነዘቡ ማድረግ ተገቢ ነው ሲሉ በዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ገለፃ ኢንስቲትዩቱ በሪፎርም ሥራዎች የተጀመሩ ሥራዎችን በማጠናከርም ኢንስቲትዩቱ የተሰጠውን ተጨማሪ ተልዕኮ ለመወጣት መሥራት እንደሚጠበቅ ተገልፆል።

በውይይቱ የተሳተፉ ሠራተኞችም ኢንስቲትዩታችን ከተሰጠው ተልዕኮ አንፃር ያለበትን ኃላፊነት በአግባቡ በመረዳት በሀገራዊ ጉዳዮችም ሆነ ሪፎርምን በተመለከተ ለሌሎች አርአያ በመሆን ኃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ከውይይቱ መድረክ በኃላም በኢንስቲትዩቱ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ ሠራተኞች የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም በማከናወን ፕሮግራሙ ተከናውኗል።

እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሠላም አደረሳችሁ!፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨በዓሉ እንደተለመደው አብሮነታችን የሚገለጥበት፣ ደግነታችን የሚታይበትና እጆቻችን ለበረ...
20/03/2026

እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሠላም አደረሳችሁ!
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በዓሉ እንደተለመደው አብሮነታችን የሚገለጥበት፣ ደግነታችን የሚታይበትና እጆቻችን ለበረከት የሚዘረጉበት የፍቅርና የሠላም በዓል እንዲሆን በእኔና በኢንስቲትዩታችን ስም እመኛለሁ።

ኢድ ሙባረክ

አቶ ደሳለኝ ጣሰው
የኢትዮጵያ ብቃትና ሥራ አመራር ኢንስቲትዩቱ
ዋና ዳይሬክተር

እንኳን ለ130ኛ የአድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ! አደረሰን!፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ጀግኖች አባቶቻችን በአንድነትና በህብረት ሀገር ማዳን እንዴት እንደሚቻል ያስተማሩበት ለ...
02/03/2026

እንኳን ለ130ኛ የአድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ! አደረሰን!
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ጀግኖች አባቶቻችን በአንድነትና በህብረት ሀገር ማዳን እንዴት እንደሚቻል ያስተማሩበት ለሀገራችን ብሎም ለአፍሪካ ይህ ቀን ታላቅ የኩራት ቀን ነው።

ሁላችንም በተሰማራንበት መስክ የአባቶቻችንን ድል በመድገም ኃላፊነታችንን እንድንወጣ ከአደራ ጭምር እያሳሰብኩ፤ በሌላ ድል ሀገራችንን ስሟን እናስጠራ።

መልካም የድል በዓል
አቶ ደሳለኝ ጣሰው
የኢትዮጵያ ብቃትና ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት

በሀገሪቱ የተጀመረው የመንግስት አስተዳደር አገልግሎት ማሻሸያ ለኢንስቲትዩቱ መልካም ዕድል መሆኑ ተጠቆመ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ኢንስቲትዩቱ በአዋጅ ቁጥር 1353/20...
03/02/2026

በሀገሪቱ የተጀመረው የመንግስት አስተዳደር አገልግሎት ማሻሸያ ለኢንስቲትዩቱ መልካም ዕድል መሆኑ ተጠቆመ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ኢንስቲትዩቱ በአዋጅ ቁጥር 1353/2017 እንደ አዲስ ከተዋቀረ በኃላ የተሰጠውን የብቃትና ምዘናና ማረጋገጫ፣ የመንግስት ሠራተኞች ቅጥር፣ የብቃት ሥልጠና አሰጣጥ እና ማማከር ጥናትና ምርምር አገልግሎት ከማከናወን አንፃር በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወነ ያለው የመንግስት አስተዳደር አገልግሎት ማሻሸያ ለኢንስቲትዩቱ መልካም ዕድል መሆኑ ተገለፀ።

በአዳማ ከተማ ለኢንስቲትዩቱ አመራሮችና ሠራተኞች እየተሰጠ ባለው በኢንስቲትዩቱ መሪ ስትራቴጂ ሥልጠና እየሰጡ ያሉት ከፍተኛ አማካሪ አቶ ጀማል አህመድ ሀገራዊ ሪፎርም ለኢንስቲትዩቱ በሁሉም አገልግሎቶች ሀገራዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ከማስቻሉም በላይ ተቋሙን ተወዳዳሪና ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችል ሀብት እንዲያፈራ ዕድል የሚፈጥር ነው ብለዋል።
እንደ ከፍተኛ አማካሪው ገለፃ ይህን መልካም ዕድል ለመጠቀም ሪፎርሙን መገንዘብና መተግበር፣ በሪፎርሙ ልክ የወጡ ተግባራትን በብቃት መፈፀምና ዘመናዊ ቴክኖሎጂ መጠቀም ይኖርበታል ብለዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከሥልጠናው ጋር በተያያዘ አንዳንድ አመራርና ሠራተኞች አስተያየት የሰጡን ሲሆን የኢንስቲትዩቱ የፋሲሊቲና ጠቅላላ አገልግሎት ሥራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ ስዩም ነጋሽ ስልጠናው
በመንግስት የተሰጠው ተጨማሪ ተልዕኮ እጅግ የላቀ ትጋት የሚጠይቅ በመሆኑ ከዚህ ቀደም የባከኑ ጊዜያትን ጭምር ለማካካስ ሌት ተቀን ለመስራት ቁጭት እንዲፈጠርብን አድርጓል ብለዋል።

በቀጣይም ከዚህ ስልጠና በኋላ በግለሰብ ደረጃ በሪፎርም ሥርዓቱ ላይ የጋራ አረዳድ እና ግንዛቤ መፍጠር፣ የግል የመፈፀም አቅምን በማሳደግ
ላለበት የስራ መደብ ብቁ ሆኖ መገኘት እና የሚጠይቀው ስብዕናን እና የአገልጋይነት ስሜትን መላበስ ከሁላችንም የሚጠበቅ ነው ያሉት አቶ ስዩም በየደረጃው ያለ አመራር የብቃት ሥርዓቱ የሚጠይቀው የመፈፀምና የማስፈጸም ቁመና ላይ መገኘት፣ የማስፈጸሚያ ሀብት የማፈላለግ እና ማዘጋጀት፣ የሪፎርም ሥራዎችን የዕለት ተዕለት ቁልፍ ሥራ
አድርጎ መምራት ከአመራሩ የሚጠበቅ ነው ብለዋል።

በሌላ መልኩ አስተያየት የሰጡን የኢንስቲትዩቱ ከፍተኛ አማካሪ አቶ አወት ብርሃነ ከመንግስት አስተዳደር አገልግሎት ማሻሸያ ጋር እየተሰጠ ባለው ሥልጠና በመንግስት በኩል የተወሰደው ቁርጠኝነትና እየተሰራ ያለውን ሥራ እንድንገነዘብ ያደረገን ሲሆን ኢንስቲትዩታችንም ራሱን ሪፎርም ከማድረግ አኳያ መዘግየቱና በአሠራርና በአመራር ደረጃም ሰፊ ክፍተት እንዳለብን ያመላከተና ቁጭትን የፈጠረ ነው ብለዋል።

ከፍተኛ አማካሪ አቶ አወት አሁን የተጀመረው ኢንስቲትዩቱን ሪፎርም የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልፀው በተለይም የስትራቴጂክ ዕቅዱ ዝግጅት ላይ ብቃት ያላቸው ኤክሰፐርቶች፣ ተባባሪ ባለሙያዎችን በማሳተፍ በጥልቅ በመወያየትና በመመርመር እንዲሰራ ቢደረግ፣ የቴክኖሎጂ ኢኖቬሽኑን በፕሮጀክት ቢሰራ፣ ስትራቴጂክ አጋርነት በዋና ዳይሬክተሩ የሚመራ ትልቅ አደረጃጀት ፈጥሮ መስራት ቢቻል ለቀጣይ ውጤታማነት አጋዥ ይሆናል ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ኢንስቲትዩቱ ከመንግስት የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት የጀመረውን ራሱን ሪፎርም የማድረግ ሥራ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለፀ። ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ከመንግስት ...
31/01/2026

ኢንስቲትዩቱ ከመንግስት የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት የጀመረውን ራሱን ሪፎርም የማድረግ ሥራ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለፀ።

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ከመንግስት አገልግሎት አስተዳደር ፖሊሲና ሪፎርም ጋር በተያያዘ ለፕሮፌሽናልና ለአመራሮች በአዳማ ከተማ እየተሰጠ ባለው የግንዛቤ ማስበጫ ኢንስቲትዩቱ ከብቃትና ምዘና እንዲሁም ከቅጥር ጋር በተያያዘ የተጣለበትን ሀገራዊ ኃላፊነት ለመወጣት የጀመረውን ራሱን ሪፎርም የማድረግ ሥራ አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ተባለ።

ከመንግስት ሠራተኞች ብቃት አተገባበርና ይዘት ጋር በተያያዘ ሥልጠና እየሰጡ ያሉት የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የሥራ ኃላፊ ዶ/ር ብርሃኑ አስፋው በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተተገበረ ለሚገኘው የመንግስት አገልግሎት አስተዳደር ፖሊሲና ሪፎርም ኢንስቲትዩቱ እንደ አዲስ የተሰጠው ከብቃት ጋር የተያያዙ ሥራዎችን ለመሥራት ጊዜ የለኝም በሚል ስሜት ከዚህ ቀደም በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ኃላ የቀረበትን ታሳቢ በማድረግ የተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎችን በብቃት መስራትና ማጠናቀቅ ይጠብቅበታል ብለዋል።

እንደ ዶ/ር ብርሃኑ ገለፃ ኢንስቲትዩቱ ሪፎርም ካደረገ በኃላ በአዋጅ 1353/2017 እንዲሁም በሚኒስትሮች ምክር ቤት ባደረገው 51ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ባፀደቀው ደንብ መሠረት የብቃት ምዘና ስልጠናና የመንግስት ሠራተኞች ቅጥር ላይ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ይጠበቃል ሲሉ ተናግረዋል።

Address

Addis Ababa
51

Opening Hours

Monday 08:00 - 17:00
Tuesday 08:00 - 17:00
Wednesday 08:00 - 17:00
Thursday 08:00 - 17:00
Friday 08:00 - 17:00

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Management Institute/EMI/ የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethiopian Management Institute/EMI/ የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት:

Share