23/04/2026
አዲሱ ሙሽራ በሚስቱ የቀድሞ ፍቅረኛ ተገደለ !
በጌዴኦ ዞን ገደብ ከተማ የአቢሲኒያ ባንክ ሰራተኛ የሆኑት አቶ ተመስገን ዳንኤል፣ ዛሬ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ገደማ ወደ ስራ በመጓዝ ላይ ሳሉ በአደባባይ በተተኮሰባቸው ጥይትና በደረሰባቸው የስለት ጥቃት ህይወታቸው አልፏል።
ግድያውን ፈጽመዋል የተባሉት ተጠርጣሪ ግለሰብ በአሁኑ ሰዓት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው ይገኛል።
የአይን እማኞች እና የሟች የቅርብ ቤተሰቦች እንደገለጹት፣ ጥቃቱ የተሰነዘረው አቶ ተመስገን ከሁለት ወራት በፊት ካገቧቸው ከወይዘሮ ምህረት ደስታ ጋር በተያያዘ በደረሰ የቂም በቀል ተነሳሽነት ነው።
ተጠርጣሪው አቶ አቡሽ ታደሰ ሁጤሳ የሟች ባለቤት የቀድሞ ፍቅረኛ እንደነበሩ የተጠቀሰ ሲሆን፣ "ሚስቴን አገባህብኝ" በሚል ሰበብ ግድያውን እንደፈጸሙት ተነግሯል።
ጥቃቱ በደረሰበት ወቅት አቶ ተመስገን "አድኑኝ፣ ሊገድለኝ ነው" በማለት የእርዳታ ጥሪ ቢያሰሙም፣ በአካባቢው ከነበሩ ሰዎች ፈጣን ምላሽ ባለማግኘታቸው ....
ተጠርጣሪው በሽጉጥ በመተኮስ እና በመቀጠልም በስለት መሳሪያ አስክሬኑን በመቆራረጥ አሰቃቂ ጥቃት ሊያደርሱባቸው ችለዋል።
ፖሊስ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር አውሎ ዝርዝር ምርመራ እያከናወነ ሲሆን፣ የአካባቢው ማህበረሰብ በድርጊቱ ከፍተኛ ድንጋጤና ሀዘን ተሰምቶታል።
ማህበረሰባችን ወዴት እየሄደ ነው ሰው ሲገደል እንዴት ቆም ያያል መገላገል እየቻለ እረ ወዴት እየሄድን ነው የግዮን ማለዳ ቤተሰቦች😭
ለቤተሰቦቹ ለወዳጅ ዘመዶቹ በግዮን ማለዳ ስም መፅናናትን እንመኛለን ። ነብሱን ይማርልን !
ግዮን ማለዳ
ፍትህ ለዚህ ወጣት 😭 😭 አመሟቱ በጣም አሰቃቂ ነው የማየት አቅሙ ያላችሁ ቴሌግራም ቻናላችን ላይ ተመልከቱት 👇
ቴሌግራም 👉 T.me/GhionMaleda