Hailemichael Tadesse Authorized Accountant

Hailemichael Tadesse Authorized Accountant We worked on Any Accounting services and prepare Financial statement Reports, VAT, Income Tax, Month

25/02/2026

ለክቡራን ግብር ከፋዮች
ለ2017 ግብር ዘመን ጠቅላላ ከከፈላችሁት ንግድ ሥራ ትርፍ ግብር ላይ (ዊዝሆልዲንግ ታክስ ያቀናነሳችሁትና በቅድመ- ኦዲት [Pre- Audit] የተደረገዉን ማስተካከያ ግብር ጨምሮ) 25%ቱን በማስላት፤ ከሀምሌ/2017 ዓም እስከ መስከረም/2018 ዓ.ም ዊዝሆልድ የተደረጋችሁትን ቅድመ- ግብር በመቀነስ ለ2018 ግብር ዘመን ቅድሚያ ግብር ክፍያ እስከ የካቲት 25/2018 ዓ.ም ባለዉ ጊዜ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጠመንጃ ያዥ ቅርንጫፍ በቅ/ጽ/ቤታችን ስም AACGRA LARGE TAX PAYERS BRANCH OFFICE ወደተከፈተ ባንክ ሒሳብ ቁጥር 1000277732088 ገቢ አድርገዉ Bank Deposit Slip እንዲያቀርቡ እንዲሁም ከሀምሌ/2017 ዓም እስከ መስከረም/2018 ዓም ድረስ ዊዝሆልድ የተደረጋችሁትን ቅድመ- ግብር በEXCEL- SHEET በሠንጠረዥ ሞልታችሁ እንድታቀርቡ እንዲሁም የዊዝሆልዲንግ ደረሰኝ ኮፒ በተጨማሪም ፕሪ ኦዲት የተሰራበትን ወረቀት ኮፒ በማድረግ እንድታቀርቡ እናሳስባለን፡፡
የአዲስ አበባ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት (AALTO)

28/01/2026

በ2018 ግብር ዘመን በየሶስት ወሩ የሚከፈል ቅድመ ግብር መቼ መቼ ይከፈላል ?
በፌዴራል የገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1395/2017 አንቀጽ 89 ከተያዘው የግብር ዓመት በፊት በነበረው የግብር ዓመት የተከፈለውን ግብር 25 በመቶ እንደሚከፍል ተደንግጓል፡፡ በዚህ መሰረት የ2018 ግብር ዓመት ዓመታዊ የትርፍ ግብር በየሩብ ዓመቱ (በየሶስት ወሩ) በማሳወቅ የሚከፍሉበት የጊዜ ሰሌዳ እንደሚከተለው ይሆናል፡፡
የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የመክፈያ ጊዜ ከየካቲት 1 እስከ የካቲት 30
• ከሐምሌ 1 እስከ መስከረም 30 የተቀነሰ 3% ቅድመ ግብር (Withholding ) በዚህ ወር ከሚከፈለው ክፍያ ላይ ተቀናሽ ይደረጋል፡፡
የሁለተኛ ሩብ ዓመት የመክፈያ ጊዜ ከግንቦት 1 እስከ ግንቦት 30
• ከጥቅምት 1 እስከ ታህሳስ 30 የተቀነሰ 3% ቅድመ ግብር (Withholding ) በዚህ ወር ከሚከፈለው ክፍያ ላይ ተቀናሽ ይደረጋል ፡፡
የሶስተኛ ሩብ ዓመት የመክፈያ ጊዜ ከነሐሴ 1 እስከ ነሐሴ 30
• ከጥር 1 እስከ መጋቢት 30 የተቀነሰ 3% ቅድመ ግብር (Withholding )
በዚህ ወር ከሚከፈለው ክፍያ ላይ ተቀናሽ ይደረጋል ፡፡
በ2019 ከሐምሌ 1 እስከ ጥቅምት 30 አጠቃላይ የ2018 ግብር ዓመት የትርፍ ግብር ቀድመው የከፈሉትን በመቀነስ ቀሪውን ይከፍላሉ፣ በትርፍ የተከፈለም ካለ ተመላሽ ይጠይቃሉ፡፡

12/09/2025

በ2017 የግብር ማሳወቂያ ወቅት የሒሳብ መዝገብ ሲቀርብ መሟላት ያለባቸው ዋና ዋና መረጃዎች (ሰነዶች)

ለሁሉም ዘርፎች ላይ ተፈጻሚ የሚደረግ

# ለኢ-ታክስ ካልተመዘገቡ መረጃ የተሞላበት ዓመታዊ የግብር የማሳወቂያ ቅጽ፤
# ሁሉም በ2017 የሒሳብ ዓመት የጸኑ የንግድ ፈቃዶች ቅጂ፤ የተ.እ.ታ፣ የኤክሳይስ ታክስ፣ የዊዝሆልዲንግ ታክስ የምዝገባ የምስክር ወረቀቶች፣
# የሀብትና ዕዳ፣ የትርፍ ኪሳራ፣ የጥሬ ገንዘብ ፍሰት እና የሐብት ለውጥ የሒሳብ መግለጫዎች፣
# የዘመኑ የየቀኑ ግብይት የተመዘገበበት ዝርዝር የሒሳብ መዛግብት (የሒሳብ ቋቶች-ledgers) እንዳስፈላጊነቱ ስስ ኮፒ ወይም ባክ አፕ

# የዘመኑ የባንክ ሒሳብ መግለጫዎች፣ የባንክ ማስታረቂያዎች፤
# የገበያ ዋጋ ንጽጽር የሚመለከታቸው ዘርፎች ከሆነ የ12 ወራት ወይም የዘመኑን ዝርዝር የሽያጭ መረጃ ኦርጂናል (ሃርድ ኮፒ እና ስስ ኮፒ)፣
# የዓመቱ መጨረሻ የንግድ ዕቃ፣ የጥሬ ዕቃ፤ የምርት መጠን፤ በእጅ ላይ ያለ የጥሬ ገንዘብ፤ የቋሚ የንግድ ሀብት የቆጠራ ሪፖርት (physical count sheet)፣
# የንግድ ዕቃዎች፣ ጥሬ ዕቃዎች ተመን መግለጫ (Inventory valuation sheets ወይም Stock valuation sheets) ፣
# የዘመኑ ሁሉንም አቅራቢዎች ስም ዝርዝር (ከነ ግ/ከ/መ/ቁጥራቸው) (all suppliers list with TIN)
# የአገልግሎት/ምርት ስርጭት በተመለከተ የተደረጉ ውሎች፣ እንዳስፈላጊነቱ የግዢ ዝርዝር፤
# የቤት ኪራይ ውሎች (የተከራዩት/ያከራዩት)፣
# የተፈቀደለት የሒሳብ አዋቂ/ የውጭ ኦዲተር የሙያ ምስክር ወረቀት ወይም የሙያ ፈቃድ፣ የንግድ ስራ ፈቃድ፣ የግ/ከ/መ/ቁጥር ቅጂ፣
# ሒሳቡ የተዘጋጀው በተቀጣሪ የሒሳብ ባለሙያ ከሆነ የቅጥር ውል፣ የትምህርት መረጃ፣ የሦስት ወራት "payroll" ተያይዞ መቅረብ ይኖርበታል፤

አምራች ዘርፍ፤

የተሰማራበት የማምረት መስኮች (fields) ፤ የምርት ዓይነቶች የሚገልጽ ሰነድ፣
# ምርቶች የኤክሳይዝ ታክስ የሚመለከታቸው/የማይመለከታቸው ለይቶ ማቅረብ፣
# የግብር እፎይታ ፈቃድ (ካለው)፣
# ዓመታዊ የማምረት አቅም (annual production capacity) ፣
# የዘመኑ የምርት መጠን መግለጫ (Production statement ወይም statement of cost of goods manufactured) እና የምርት መጠን፣
# ከማምረት አቅም ውስጥ ምንም ምርት ማምረት ያልጀመሩ ማሽነሪዎች (excess capacity) ፣
ቋሚ የማምረቻ ወጪ መጠን (በብር)(annual Fixed production costs)፣፣
# የግብዓት ምርት ጥምርታ (a pre-determined input-output ratio ወይም I-O rate) ፣
# የግብአት አጠቃቀም ሪፖርት (raw material uses)፣
# ስታንዳርድ የማምረቻ ወጪ (a pre-determined standard production cost) እና ትክክለኛ የማምረት ወጪ (actual production cost) ፣
# የምርቱ ዋና ዋና አከፋፋዮች እና ውል ወይም ዋና ዋና የምርት ተቀባዮች ዝርዝር (TIN)

አስመጪ/ላኪ

# እንደ አስፈላጊነት የዘመኑ የውጭ ሀገር ግዥ/ሽያጭ የጉሙሩክ ዴክላራሲዮን ወይም
# አስመጪ የግዥ ዋጋ ግንባታ መግለጫዎች
# አስመጪ የግዥ መረጃ ዝርዝር
# ላኪ የሽያጭ መረጃ ዝርዝር
# ሃገር ውስጥ የንግድ ፊቃድ /ሃገር ውስጥ ግዥ፣
# ስቶክ ካርድ/ስቶክ ሌጄርስ (ሲጠየቅ)፣
# ላኪዎች ከታክስ ደረሰኝ ወጭ የተፈፀሙ ግዥዎች የክፍያ ማረጋገጫ፣
# አስመጪ ከሆነ የዘመኑ የሽያጭ ፖሊስ (የዱቤ/ የጥሬ ገንዘብ/ Discount….)፣
# አስመጪ ከሆነ የዘመኑ የምርቱ ተቀባዮች (ደንበኞች) ስም ዝርዝር (TIN) ፣

አከፋፋዮች/ጅምላ ንግድ

# ከአቅራቢዎች ጋር ያለ የምርት ስርጭት ውሎች (ካለ)፣
# የምርት ተቀባዮች (ደንበኞች) ስም ዝርዝር መረጃ (TIN) ፣
# የዘመኑ የግዥ መረጃ ዝርዝር መረጃ (ከአቅራቢዎች የቀረበ)፣

ሥራ ተቋራጭ ዘርፍ

# የስራ ተቋራጩ የደረጃና የብቃት ማረጋገጫ ሰነድ፤
# ዋና እና ንዑስ የስራ ተቋራጭ ውል ስምምነቶች፣
# እንደአስፈላጊነቱ በየፕሮጀክቶቹ የክፍያ ምስክር ወረቀቶች ቅጅ፣
# በዘመኑ በእንቅስቃሴ ላይ ያሉ እና የሌሉ ፕሮጀክቶችን ዝርዝር መረጃ፣
# በየፕሮጀክቶቹ ገቢ እና ወጪ ተለይቶ የተያዘ መዝገብ (የሒሳብ መግለጫ)፣
# የተሻሻሉ ወይም የተለወጡ የስራ ተቋራጭ ውል ስምምነቶች፣
# በዘመኑ ስራ ላይ የሌሉ ወይም በከፊል ስራ ላይ የነበሩ ማሽነሪዎች፤
# የተከራያቸው የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች፤የንዑስ ስራ ተቋራጮች ውሎች (ክፍያቸው-የተፈፀመበት አኳሃን)፣

የኮንስትራክሽን ማሽነሪ ኪራይ

# የኪራይ ውል ስምምነቶች (የዘመኑና የዞረ ውል)፣
# የማሽነሪዎቹ ብዛትና ዓይነት እና የባለቤትነት ማረጋገጫ (ሊብሬ)፣
# የማሽነሪዎች በቀን የመስራት አቅም፣
# ተከራይቶ ማከራየት ከሆነ የኪራይ ውል ስምምነት፣
# ባለቤት የሆነባቸው ማሽነሪያች የተገዛበት ዋናው ሰነድ፤
# የኮንስትራክሸን መሣሪያዎች የስራ ላይ ቆይታ ጊዜ መመዝገቢያ ሰነድ (Time Sheet)
# የብልሽት ማስረጃ (ለረጅም ጊዜ የቆመ ከሆነ)

ልኳንዳ ቤቶች

# የልኳንዳ ቤቱ ደረጃ፣
# የዕርድ (የዘመኑ) መረጃ (ዝርዝር) በከብት ዓይነት እና ብዛት፣
# የግዥ መረጃ (ዝርዝር) የክፍያ ማረጋገጫ፣
# በዘመኑ አዲስ የሒሳብ መዝገብ መያዝ የጀመሩ በተመለከተ፡
# ደረሰኝ የህትመት ፍቃድና የታተሙ ደረሰኞች፣
# የዘመኑ የግዥ መረጃ ማጠቃለያ፣
# የዘመኑ የሽያጭ መረጃ ማጠቃለያ፣
# መዝገብ መያዝ ሲጀምሩ በእጅ ላይ ያለ ያልተሸጡ ዕቃዎች ዝርዝር (የቆጠራ ማስረጃ)፣
# "Charts of Accounts)" ፣ለተመዘገቡት ሒሳቦች ሰነድ ሲጠየቁ ማቅረብ የሚችሉ መሆኑን ማረጋገጥ፤
# በታክስ ህግ ተቀባይነት ባለው የሒሳብ አያያዝ መርህ/ ዘዴ የተዘጋጀ የሒሳብ መዝገብ መያዛቸው እና ሒሳቡን ያዘጋጀው ተቀባይነት ባለው ባለሙያ መሆኑን ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል፡፡

21/07/2025
21/07/2025

Addis Ababa Revenu Bereau

የተጨማሪ እሴት ታክስ የማሳወቂያ ጊዜን ይመለከታል
የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢዎች የሆናችሁ ግለሰብ ወይም ድርጅቶች
1ኛ.ስማችሁ ከ A-G የሚጀምር ግብር ከፋዮች ወር በገባ በመጀመሪያው ሳምንት

2ኛ. ስማችሁ ከ H-N የሆናችሁ ወር በገባ በሁለተኛው ሳምንት

3ኛ. ስማችሁ ከ O-T የሆናችሁ ወር በገባ በሶስተኛው ሳምንት እንዲሁም

4ኛ. ስማችሁ ከ U-Z የሆናችሁ የቫት ተመዝጋቢዎች ወር በገባ በመጨረሻው ወይም በአራተኛው ሳምንት ብቻ ወርሃዊ ቫታችሁን እንድታሳውቁ::
አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ

09/07/2025

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የ2017 ዓ/ም የግብር ዘመን ግብር አወሳሰንና አሰባሰብ አሰራር ይፋ አድርጓል።

አዲሱ መመሪያ የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመክፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታ ተፈጻሚ የማይደረግባቸው ግብር ከፋዮችን በሚመለከት።

እንዲሁም የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ያልተወጡ ግብር ከፋዮችን በተመለከተ መደረግ ስላለበት ዝርዝር ሃሳብ የያዘ ደብዳቤ በቢሮው የታክስ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ወርቅነሽ ሰቦቃ ተፈርሞ ለሁሉም ለግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ተልኳል።

ደብዳቤው "የተወሰኑ ግብር ከፋዬች በህጉ የተጣለባቸውን ግዴታ ለመወጣት የተሰማሩበትን የስራ ዘርፍ ባለው የተለየ ባህሪ ምክንያት መቸገራቸውን በተለያየ ጊዜ በመጥቀስ አቤቱታ ያቀረቡ" መሆኑን ገልጿል።

ይሁን እንጂ የግብር ሕጉ ለየትኛውም የንግድ ዘርፍ በተለየ መልኩ የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ቀሪ አለማድረጉንም አሳውቋል።

ይህንኑ ግዴታ አለመወጣትም አስተዳደራዊ ቅጣት የሚያስከትል መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ የተለየ ባህሪ ያላቸው የተወሰኑ የሥራ ዘርፎች የግብር ህጉን ድንጋጌዎች በአስከበረ አግባብ የገቢ አሰበሰቡን እና የአገልግሎት አሰጣቱን ፍታሀዊነት ማዕከል ያደረገ የአሰራር ሥርዓት ለ2017 የግብር ማሳወቂያ ጊዜ ሂሳብ መዝገብ የማቅረብ ግዴታን ተፈጻሚነት በቅጣት ብቻ በማለፍ ማዘግየት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበታል ብሏል።

ስለሆነም የደረጃ "ሀ" እና የደረጃ "ለ" ግብር ከፋዬች የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ከዚህ በታች የተዘረዘሩ ግብር ከፋዬች በማይወጡበት ጊዜ ለደረጃ «ሐ» ግብር ከፋዬች የወጣውን ገቢ ግብር ደንብ ቁጥር 410/2009 የትርፍ ሕዳግ እና በግምት ግብር አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 138/2010 በቁርጥ የወጪ ሰንጠረዥ መጠቀም ዘርፉ ግዴታውን በገቢ ግብር ሕጉ መሰረት እንዳይወጣ ከተማውም ማግኘት የሚገባውን ገቢ እንዳይሰበስብ ምክንያት ስለሚሆን ይህንኑ ክፍተት ለመዝጋት በገቢ ግብር አዋጁ ቁጥር 979/2008 አንቀጽ 80 መሰረት ግብር በግምት በሚሰላበት ጊዜ፦

ከግብር ከፋዮች ግንዛቤ የተለየ ድጋፍ የሚፈልጉ እና ሥራቸውም ከመንግስት ጋር በተገባ ውል ብቻ የሚያከናውኑ በማህበር የተደራጁ :-

- የትምህርት ቤቶችና የምገባ ማዕከላት መጋቢ እናቶች

- በከተማ ጽዳትና ውበት ደረቅ ቆሻሻ እና ገጸ-ምድር ማስዋብ ላይ የተሰማሩ

- ከንግድ ቢሮ ትስስር የተፈጠረላቸው የሸገር ዳቦን የሚሸጡ ማህበራት

ከመንግስት ተቋማት ጋር ያላቸውን ውልና በበጀት ዓመቱ ከአሰራቸው የመንግስት ተቋም ዓመቱን ሙሉ የተከፈላቸውን ክፍያ የሚገልጽ መረጃ ሲያመጡ መረጃን መሰረት አድርጎ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ገቢው ተወስኖ እንዲሰበሰብ።

በተጨማሪም የሸገር ዳቦን የሚሸጡ በተጓዳኝ የሚከናውኑ የንግድ ስራዎች መኖራቸው በመስክ ምልከታ ተረጋግጦ በየዘርፉ የቀን ገቢ ግምት እንዲገመትላቸው ተደርጎ ግብሩ ተወስኖ እንዲሰበሰብ።

የንግድ ሥራ ፍቃድ ሳይኖራቸው በሞያ ፍቃድ ብቻ አገልግሎት የሚሰጡ ጠበቆች ፣የኢንሹራንስ ወኪሎች ፣ኢንሹራንስ ጉዳት ገማች ግለሰቦች በሚመለከት:-

➡️ ከግብር አመቱ አጠቃላይ እንደ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።

➡️ የንግድ ሥራ ያልሆነ ገቢ ያላቸው የመኖሪያ ቤት አከራዮች ከግብር አመቱ አጠቃላይ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።

➡️ በግል ኮድ 02 እና በንግድ ኮድ 03 ተሸከርካሪ የኪራይ አገልግሎት የሚሰጡ አጠቃላይ የኪራይ ገቢ ላይ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት በመረጃ የሚወሰን በመሆኑ ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።

➡️ በህግ ደረሰኝ የመጠቀም ግዴታ ተፈጻሚ የማይደረግባቸው የከተማ ውስጥ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭዎች /በቴክኖሎጂ ስምሪት የሚሰጣቸውን የሜትር ታከሲዎች ጨምሮ/ የገቢ ግብር ደንብ ቁጥር 410/2009 ሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ መወሰኑን ይገልጻል።

(ተጨማሪውን ከተያያዘው ደብዳቤ ይመልከቱ)

09/07/2025
08/05/2025

" የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ በህግ የሚገደዱ ግብር ከፋዮች ከመጪው ሀምሌ የግብር ማሳወቂያ ወር ጀምሮ የተሟላ የሂሳብ መዝገብ በመያዝ ካልመጡ በስተቀር አይስተናገዱም "- የገቢዎች ቢሮ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ከመጪው ዓመታዊ የግብር ማሳወቂያ ወር ጀምሮ የደረጃ "ሀ" እና "ለ" ግብር ከፋይ ሆነው በህግ የሚገደዱ ግብር ከፋዮች ያለ ሂሳብ መዝገብ የማይስተናገዱ መሆኑን አሳውቋል።

አይስተናገዱም የተባሉት በደረጃ "ሀ" እና "ለ" የግብር ከፋይነት የተመዝገቡ እና በህጉ መሰረት የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ የሚገደዱትን ብቻ ነው።

የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደተናገሩት በህጉ መሰረት የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ የሚገደዱ ነጋዴዎች ከሚቀጥለው በጀት አመት በኋላ ግብር ለመክፈል ያላቸውን አጠቃላይ ወጪ እና ገቢያቸውን በዝርዝር የሚያሳይ መዝገብ መያዝ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።

አቶ ሰውነት አየለ በዝርዝር ምን አሉ ?

" የሂሳብ መዝገብ ማለት ያላቸውን አጠቃላይ ሽያጭ እና ወጪ በዝርዝር የሚያሳይ ሰነድ/መዝገብ ነው።

ህጋዊ የሆነ ግብይት የሚፈጸም ከሆነ እና በደረሰኝ ላይ የተመሰረተ ግብይት ካለ ከዚህ መዝገብ ጋር ተያይዞ ነው የሚቀርበው።

ይህ ህግ ከወጣ ረጅም ጊዜ ነው ነገር ግን አፈጻጸም ላይ የተለያዩ ክፍተቶች በመኖራቸው በቁርጥ ግብር የሚስተናገዱ ነበሩ።

ለእነዚህ ግብር ከፋዮች በተለያየ መንገድ መረጃዎችን እያደረስን ነው ያለነው ከሚቀጥለው በጀት አመት በኋላ ከዚህ ሂሳብ መዝገብ ውጪ እንደማናስተናግዳቸው እንዲያውቁ እያደረግን ነው።

ግብይቶቻቸውን በደረሰኝ ላይ ተመስርተው ፈጽመው በሂሳብ ባለሙያ አልያም የድርጅታቸው ተቀጣሪ በሆነ የሂሳብ ባለሙያ የተዘጋጀ የሂሳብ መዝገብ ማቅረብ አለባቸው።

ግብር ከፋዮች ከግምት የጸዳ የግብር አሰባሰብ ስርዓት የራሳቸውን ሚና እንዲጫወቱ ለማስቻል ይህንን የማሳወቅ ስራ እየሰራን ነው።

በደረጃ "ሀ" እና "ለ" ከ120 ሺ በላይ ግብር ከፋዮች አሉ ከእነዚህ ውስጥ ገቢ እና ወጪያቸውን በአግባቡ እየመዘገቡ ፣ደረሰኝ እየቆረጡ አመታዊ ግብራቸውን የሚያሳውቁ አሉ ነገር ግን ከዚህ ውጪ ሲስተናገዱ የቆዩ ግብር ከፋዮቾም ነበሩ።

ይህ አሰራር ተለምዶ ከአመት አመት ዝም ብሎ በቁርጥ ግብር ለመስተናገድ የመፈለግ አዝማሚያ ይታያል ህጉ ግን ይህንን አሰራር የማይፈቅድ በመሆኑ ከመጪው ሐምሌ ወር ጀምሮ ሲመጡ በተሟላ መንገድ ሂሳብ መዝገባቸውን ይዘው ካልመጡ በስተቀር አይስተናገዱም።

መያዝ አለባቸው እያልን ያለነው በደረጃ "ሀ" እና "ለ" የግብር ከፋይ ተመዝግበው በህጉ መሰረት የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ የሚገደዱትን ብቻ ነው።

ሁሉንም ማለት አይደለም በተሰማሩበት የንግድ ዘርፋቸው ምክንያት እዚህ ውስጥ የማይካተቱ ይኖራሉ የሚመለከተው የተሰማሩበት የስራ ዘርፍ የሂሳብ መዝገብ መያዝ እያስገደዳቸው በተለያየ ምክንያት የማይዙትን እና በቁርጥ ግብር ሲስተናገዱ የነበሩ የንግዱን ማህበረሰብ ነው።

 /ማሻሻያ/_ቁጥር_188/2017ሕዳር 04/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)ለእያንዳንዱ የንግድ ሥራ ዘርፍ እና የንግድ አድራሻ የተለያየ ደረሰኝ እንዲታተም ማድረግ አስፈላጊ ስለሆነ እና በ...
13/11/2024

/ማሻሻያ/_ቁጥር_188/2017

ሕዳር 04/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

ለእያንዳንዱ የንግድ ሥራ ዘርፍ እና የንግድ አድራሻ የተለያየ ደረሰኝ እንዲታተም ማድረግ አስፈላጊ ስለሆነ እና በእያንዳንዱ ደረሰኝ ላይ ልዩ QR ኮድ (unique QR code) ማካተት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ገቢዎች ሚኒስቴር በፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 አንቀጽ 19(4) በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ይህን የማሻሻያ መመሪያ አውጥቷል፡፡

Address

Addis Ababa
1000

Opening Hours

Monday 08:30 - 18:00
Tuesday 08:30 - 18:00
Wednesday 08:30 - 18:00
Thursday 08:30 - 18:00
Friday 08:30 - 18:00
Saturday 09:00 - 17:00

Telephone

+251913143025

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hailemichael Tadesse Authorized Accountant posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hailemichael Tadesse Authorized Accountant:

Share