ቤተ ተውኔት የተውኔት ጽሁፍ አማካሪዎች

ቤተ ተውኔት የተውኔት ጽሁፍ አማካሪዎች Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ቤተ ተውኔት የተውኔት ጽሁፍ አማካሪዎች, Consulting Agency, Fikru Kassa, Arada sub city, Addis Ababa.

11/04/2024

“ከሻይ ቤት ሀርሞኒካ እስከ ዳህላክ ባንድ”
በስብሐት ገብረ እግዚአብሔር
(1973 ዓ.ም)
አንዳንድ ዘፈን አለ … ድንገት ደርሶ ድፍን አዲስ አበባን የሚያጥለቀልቅ። በየቡና ቤቱ፣ በየ መጠጥ ቤቱ፣ በየሻይ ቤቱ በቴፕ ያሰሙታል። ካሴት ያላቸው ታክሲዎች ውስጥም ሲዘፈን ይሰማል። በመንገድ ጐረምሶች ዜማውን ያፏጩታል። ሴቶች ብቻቸውን ሆነው ልብስ እያጠቡ ወይም ወጥ እየሠሩ ለራሳቸው ይዘፍኑታል። ልጆች መንገድ ሲሄዱ ይዘፍኑታል … አልፎ አልፎ ባንድ እግራቸው ብቻ እየነጠሩ። ገና አፋቸውን የፈቱ ሕፃናትም ይኰላተፉበታል። የመንደር ሰካራሞችም ይንገዳገዱበታል። ባጭሩ፣ የከተማው ዘፈን እሱ ይሆናል።
ከጥቂት ወራት በፊት “ናኑ ናኑ ነይ፣ ናኑ ናኑ ነይ፣ ካንቻለኝ ጉዳይ!” እያለ ሲያስተጋባ ነበር የአዲስ አበባ ሕዝብ … ከሙሉቀን መለሰ ተቀብሎ ነበር የዘፈነው።
አንድ የሥራ ጓደኛዬ እድሜዋ ሶስት ዓመት ተኩል የሆነ ልጅ አለችው። አንድ ቀን፣

“አባዬ! ያቺ ኮ ስሟ ናኑ ነው” አለችው ወደ አንዲት ኰረዳ እያመለከተች።

“ኧረ?” ሲላት፣

“አዎን” አለች፤ “ብትፈልግ ትላንትና ‘ናኑ ናኑ ነይ፣ ካንቻለኝ ጉዳይ’ ስል ጊዜ መጣች!”

ጓደኛዬ ይህን ከነገረኝ በኋላ፣ “ያንን ሙሉቀንን ባወቅኩት እቺን አጫውተው ነበር” አለኝ።
ሙሉቀን መለሰ አጠር ያለ፣ ወፈር ያለ፣ በጣም ቀይ የሆነ የሃያ ስምንት ዓመት ጐረምሳ ነው። ለሁለት ሰዓት ይህል ሲያነጋግረን እንደገመትኩት ሙሉቀን ሀሳቡን በቀጥታ የሚናገር ሰው ነው። ማለቴ፣ “እንዲህ ያልኩ እንደሆነ እንደዚህ ተብሎ ሊተረጐምብኝ ይችላል” የሚል ሥጋት የለበትም።

“ሙሉቀን ብለው ስም ያወጡልህ ለምንድነው?” አልነው።

“እህቴ ነች ያወጣችልኝ። እናቴ ‘ሙሉሰው’ ነው የምትለኝ። ከኔ በፊት አስወርዷት ነበር። ደሞ ታላላቆቼ አራቱም ሲወለዱ ምጥ ይበዛባት ነበር። እኔ ስወለድ ግን ይህ ችግር አልነበረም። ለዚህ ነው ‘ሙሉሰው’ ያለችኝ። ‘ስማቸው’ ይለኛል አባቴ። የመሬት ሙግት ነበረበት። ጠላቶች ነበሩት። እነሱን ስማቸው ማለቱ ነው።”
ሙሉቀን መለሰ በጐጃም ክፍለ ሀገር አነደድ ወረዳ ውስጥ ዳማ ኪዳነ ምሕረት በምትባል መንደር በ1946 ዓ.ም ተወለደ። አሥር ዓመት ሲሆነው እናቱ ስለሞቱ፣ አዲስ አበባ ይኖሩ የነበሩ አጐቱ እንዲማር ብለው አመጡት። ኰልፌ ሰፈር ጳውሎስ ትምህርት ቤት ገባ። ግን ብዙ አልተማረም። ያጐቱ ሚስት ይጠሉት ስለነበረ ብስጭት በዛበት።
እንግዲህ ኰልፌ አንድ የጡረታ ቤት ነበረ። ባንድ ጐኑ የልጆች ማሳደጊያ ነበረው። የሚረዱ አሉ ሲባል ሰምቶ ሙሉቀን ሄዶ ጠየቀ። ተቀበሉት።
“የበላይ አስተዳዳሪዋ ይወዱኝ ነበር። ‘ኤልቪስ’ ነበር የሚሉኝ። በሁለት ወር እንደዚህ ልብስ ይዘውልኝ ይመጡ ነበር። ውጭ አገር ልኬ አስተምርሃለሁ ብለውኝም ነበር። ይንከባከቡኝ ነበር። እወዳቸው ነበር። ውለታቸው በጣም ትዝ ይለኛል።”
እዚያው የሙዚቃ ትምህርት ቤት ተከፈተ። አቶ ተፈራ አቡነ ወልድ ነበሩ አስተማሪው።
ሙሉቀን ስድስት ወር ያህል እንደተማረ እህቱ ስለታመመች ወደ አገር ቤት ሄደ። ያን ጊዜ ነው አዲስ አበባ ውስጥ አክስት እንዳሉት ያወቀው። እሳቸው ይዘውት መጡና ከሳቸው ጋር መኖር ጀመረ። ቤታቸው የካ ሚካኤል ነው። እንግዲህ ሙሉቀን ወደ ሙዚቃ ትምህርት ቤቱ አልተመለሰም።
አክስቱ የወታደር ሚስት ናቸው፣ ጠላም ይነግዳሉ። ኑሮአቸው ጐስቋላ ነው። ልጁ አልተመቸውም።
አንድ ቀን ወደ ምድር ጦር ሙዚቃ ክፍል ሄደ። ሊቀጠር። አልተቀበሉትም። ግን በእርዳታ መልክ ሻይ የማፍላት ሥራ ሰጡት።
“ምድጃዋ የኤሌክትሪክ ነበረች። ባንድ ቀን ውስጥ ሶስት ጊዜ ኮረንቲ ያዘኝ” አለ።
ስድስት ወር ያህል ከሰራ በኋላ ትቶት ወጣ። ጥቂት ወራት ተንከራተተ።
ከአቡነ ጴጥሮስ ሐውልት ወረድ ብሎ አንድ ሻይ ቤት ነበረ። የሻይ ቤቱ ባለቤት ሙሉቀንን ይወደዋል፤ ይረዳዋል። ሀርሞኒካ የሚጫወት ጓደኛ አለው ሙሉቀን። ሻይ ቤቱ ቁጭ ይሉና ጓደኛው ሀርሞኒካውን ይጫወታል። ሙሉቀን ይዘፍናል።
አንድ ቀን ሙሉቀንና ጓደኞቹ አብረው ሲጫወቱ ያመሹና ወደ ሶስት ሰዓት ላይ አንዱን ጓደኛቸውን ለመሸኘት ይነሳሉ። ደጃች ውቤ ሰፈር ሲደርሱ የውቤ በርሀ ልዩ ልዩ ቀለማት መብራቶች በርተው ሙሉቀንን በጣም ያስደንቁታል። አንዱ ቤትማ ከሌሎቹም የበለጠ አሸብርቋል። ጓደኛሞቹ ይኸ ቤት ምንድነው ብለው ሲጠያይቁ፣ ይኸማ ‘ፈጣን ኦኬስትራ’ የሚጫወትበት ‘ፓትሪስ ሉሙምባ ናይት ክለብ’ ነው ይሏቸዋል።

ፊት ለፊቱ ካለው ሱቅ ሄደው፣
“ባለቤቱ ማነው የዚህ ናይት ክለብ?” ብለው ጠየቁ።
“ወይዘሮ አሰገደች አላምረው ናቸው” አለ ባለሱቁ።
“ሥራ ይሰጡኝ ይሆን ወይ?” ብሎ ጠየቀ ሙሉቀን።
“ፃፍና ጠይቃቸው” አለው ባለሱቁ ወረቀትና እስክሪፕቶ እየሰጠው።
እዚያው ቆሞ ደብዳቤውን ፃፈ። ጓደኛሞቹ ከፍርሃት ጋር እየታገሉ ከዚያ ከአስደናቂ ቤት ገቡ። ሙሉቀን ደብዳቤውን ለኦኬስትራው መሪ ሰጠው።
አነበበውና ሳቀበት።
“ምንድነው እሱ?” አሉ ወይዘሮ አሰገደች ከወዲያ ቁጭ ብለው።
ሰውየው ነገራቸው። ደብዳቤውን ተቀብለው አነበቡ።
“ፈትነው። ካለፈ ጥሩ … አለዚያም ሌላ ሥራ እሰጠዋለሁ” አሉ። የልጅ መልኩና ጎስቋላ ሁኔታው ሀዘኔታቸውን ቀስቅሶ ሳይሆን አይቀርም።
ያን ጊዜ ሙሉቀን እንደ ጥላሁን ገሰሰና እንደ ዓለማየሁ እሸቴ እያደረገ ይዘፍን ነበር። ባዶ እግሩንና በቁምጣ ሱሪ መድረኩ ላይ ወጣና ‘ለውነት እሞታለሁ፣ አልሳሳም ለነብሴ’ን እና ‘እንክርዳድ’ን ዘፈነ።
የናይት ክለቡ ሴቶች (በጣም ብዙ ናቸው) ዘፈኑን ወደዱለትና ያን ጊዜውኑ አንድ አራት መቶ ብር የሚሆን አዋጡለት።

“በበነጋታው ካኪ ልብስ ተገዛልኝ፤ ሱፍ ልብስ ተለካሁ። ቢትልስ ጫማ አደረኩ … እግሬን ታጥቤ!” አለ።
እዚያው ክፍል ተሰጠው። ምግብም ከዚያው ነው። የዘፈን ሥራ ጀመረ።
ወደ ናይት ክለቡ የሚመጣው ሰው እየበዛ ሄደ። ወይዘሮ አሰገደች ሙሉቀንን ኮንትራት (ውል) አስፈረሙት። እሱ ማታ ማታ ሊዘፍን፣ እሳቸው በወር ዘጠና ብር ሊከፍሉት።
“ዘጠና ብር! ሚልየኔር የሆንኩ ነው የመሰለኝ!” አለን።
የቀድሞው አሜሪካን ቤተ መጻሕፍት አጠገብ ‘ዙላ ናይት ክለብ’ የሚባል ነበር። የዚህ የዙላ ባለቤቶች መጥተው አነጋገሩት ሙሉቀንን። በወር ሦስት መቶ ብር እንክፈልህ፣ ለኛ ዝፈን አሉት። እሺ ብሎ ሄደ።
ሴትየዋ ኮንትራት አፍርሷል ብለው አሳሰሩት። ሦስተኛ ፖሊስ ጣቢያ። አንዱ ፖሊስ እሳቸውን ለማስደሰት ብሎ ሙሉቀንን በጥፊ ሲለው ጊዜ ታዲያ በጣም ተቆጡት።
“እንድታስፈራሩልኝ ነው እንጂ እንድትጎዱት አይደለም” አሉ።
ከቤታቸው አልጋ መጣለትና ተረኛው መኰንን ክፍል ተነጥፎለት እዚያ አደረ። በነጋታው ተፈታ። ‘ዙላ ናይት ክለብ’ ገባ።
“ጋሽ ሰሎሞን ተሰማ የደረሰውን ‘የዘላለም እንቅልፍ’ እና አቡበከር አሸኬ የደረሰውን ‘ያላየነው የለም’ … ሁለቱን ዘፈን ይዤ በቴሌቪዥን ቀረብኩ።”
አዲስ አበባ ሙሉቀን መለሰን ሊያውቀው ጀመረ።
የፖሊስ ኦርኬስትራ አስተዋዋቂ ሻለቃ ወርቅነህ ዘለቀ
“አንድ አራት መቶ ብር እንክፈልህ፣ ና እኛጋ!” አሉት።
እሺ ብሎ ሄደ። የወር ደሞዙ ይመጣል ታድያ – አንድ መቶ ብር ብቻ!። እወጣለሁ ቢል ጊዜ፣ “ፈርመሃል!” ብለው አስፈራሩት። ልጅ ነዋ!
ሙሉቀን መለሰ ለፖሊስ ኦርኬስትራ በተቀጠረ በሦስት ቀኑ መቀሌ ከኦርኬስትራው ጋር የ “ወይዘሪት ትግራይ” የቁንጅና ውድድር ይደረግ ነበር። ሙሉቀን የጥላሁን ገሰሰን ዘፈኖች ዘፈነ። በጣም ወደደው ሕዝቡ። የኦርኬስትራው አባሎችም አለማየሁ እሸቴ ሄዶባቸው ስለነበረ ሙሉቀንን “ምትኩ” አሉት።

ተስፋዬ አበበ የደረሳቸውን ሦስት ዘፈኖች (“እምቧይ ሎሚ መስሎ” “እናቴ ስትወልደኝ መች አማከረችኝ” እና “ልጅነት” የተባሉትን) ሙሉቀን በሕዝብ ፊት ይዘፍን ጀመር። በነዚህ ዘፈኖች ታዋቂነትን አተረፈ። ጋዜጣ ላይም “ኮከብ ድምጻዊ ተጫዋች” ብለው ጻፉለት።
ከፖሊስ ኦርኬስትራ ጋር ሦስት ዓመት አገልግሎ ወጣ … የማታ ክበቦች እንደገና መጫወት ጀመረ።
ዛሬ በግዮን ሆቴል በ‘ዳህላክ ባንድ’ እየታጀበ ይዘፍናል።
አንድ አስር የሚሆን የሙሉቀን መለሰ ሸክላ ወጥቷል። ከአብዮቱ ወዲህ ዘፈኖቹ በካሴት ተሰራጭተዋል።
ከዘፈኖችህ በጣም የምትወደው የትኞቹን ነው? ብለን ጠየቅነው።
“እኩል ነው የማያቸው። ግን … በጣም የሚያረኩኝ … በዜማውና በዘፈኑ … ‘ሰውነቷ’ እና ‘ሆዴ ነው ጠላትሽ’ … እ …… በሙዚቃ ጥራትና ባሠራር ደግሞ፣ ሙላቱ አስታጥቄ ያቀነባበራቸውና ከዳህላክ ባንድ ጋር የዘፈንኳቸው ‘ቼ በለው’ እና ‘ውቢት’።”
ከድምፃውያን ተጫዋቾች ማንን ታደንቃለህ? አልነው።
“ዓለማየሁ እሸቴን። ደረጃው በጣም ከፍተኛ ነው። ካሉን ዘፋኞች ሁሉ የበለጠ የሙዚቃ እውቀት አለው። ሁላችንም በዘልማድ የምንዘፍን ሲሆን፣ እሱ ግን ሙዚቃን በማወቅ ከኛ ብልጫ አለው። ፕሮፌሽናል ኢንተርናሽናል (በአለም አቀፍ ደረጃ ባለሙያ) ዘፋኝ ያለን እሱ ነው ብዬ የምኰራበት ሰው ነው።
“በድምፅ ደሞ እንደ ምኒልክ ወስናቸው ያለ ዘፋኝ የለንም። የኦፔራ ዘፋኝ ድምጽ ነው ያለው … ጥላሁን፣ ዓለማየሁ፣ ምኒልክ፣ ብዙነሽ፣ ሂሩት፣ ማህሙድ – እነዚህን የሚተኩ ድምጻውያን መብቀል አለባቸው። ይኸ የአገሪቱ ኃላፊነት ነው … ይህን ሙያ ሲበዛ ነው የምወደው። በየዕለቱ ይበልጥ እያወቅከው … እየተማርከው ትሄዳለህ። ማቆሚያ የለውም … ሙዚቃን በትምህርት ሳይሆን በልማድ ነው የማውቀው።
“አንደኛ የሚባል ዘፋኝ የለም። ሊኖርም አይችልም። ቢበዛ ‘የዓመቱ ኮከብ’ መባል ይችላል እንጂ … እያንዳንዱ ዘፋኝ የራሱ አይነት ልዩ ተሰጥዎ አለው።”
[ምንጭ] – “ኪነት ዓምድ”። ፀደይ መጽሔት። ኅዳር ፲፱፻፸፫ ዓ.ም። ገጽ 12-14፣ 20።
March 19, 2018 አንድምታ
ሙሉቀን መለሰ በ70 አመቱ ሚያዚያ 1ቀን 2016 ዓ.ም በሚኖርባት አሜሪካ ከዚህ አለም በሞት ተለየ፡፡

27/07/2023

Creative writing Prompt (19)

If you could visit any planet in our solar system, which would it be and why? Would you prefer to live there, if you could fill the air with oxygen?

What if somebody offered you one million dollars to betray a friend? Would you do it, and if so, how would you explain your actions to them?

14/07/2023

Creative writing Prompt (18)

If you could only talk to one person for the rest of your life, who would you choose and why? Would you ever run out of things to say?

15/06/2023

Creative writing Prompt (17)

If you could choose one fictional character to be your best friend in real life, which character would it be? What would you do together?

23/03/2023

Creative writing Prompt (16)

What if somebody offered you one million dollars to betray a friend? Would you do it, and if so, how would you explain your actions to them?

17/02/2023

Creative writing Prompt (15)

If you could read people's thoughts, what would you do and why? Whose thoughts would you want to read most, and why?

17/01/2023

Creative writing Prompt (14)

If you could change your name, what would you change it to? Do you think this name suits your personality more than your current name?

30/11/2022

Creative writing Prompt (13)

If you could change the length of a day, would you lengthen it or shorten it? How would the world change as a result?

25/11/2022

Creative writing Prompt (12)

If you could be locked in any shop for a night, and you couldn’t get in trouble for anything you did, what type of shop would you choose? What would you do?

23/11/2022

Creative writing Prompt (11)
Imagine that a new, deadly disease is infecting humans; you only have one vaccine, but aren’t infected yourself. The vaccine is for an elderly relative, but on the way home you see a child you’ve never met who also has the disease, what would you do?

19/11/2022

Creative writing Prompt (10)

If you were a song, what type of song would you be and why? If you can’t define it by genre, tempo or mood, describe it in any way you can.

18/11/2022

Creative writing Prompt (9)

What if you were offered a choice between a short life with a peaceful death and a long life with a horrific death? Which would you choose and why?

Address

Fikru Kassa, Arada Sub City
Addis Ababa
55754

Telephone

+251 9 22 87 52 32

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ቤተ ተውኔት የተውኔት ጽሁፍ አማካሪዎች posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ቤተ ተውኔት የተውኔት ጽሁፍ አማካሪዎች:

Share