Gemstone Buy & Sale In Ethiopia

Gemstone Buy & Sale In Ethiopia Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gemstone Buy & Sale In Ethiopia, Business service, Addis Ababa.

22/05/2026
10/05/2026

የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳኗ ዘወትር ይታሰባል 🙏

ኪዳን የሚለው ቃል ተካየደ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጉሙም ተማማለ፣ ተስማማ፣ ውል ገባ ማለት ነው፡፡ ኪዳነ ምሕረት ማለትም ደግሞ የምሕረት ቃል ኪዳን ማለት ነው፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ስለሰው ልጆች ይቅርታ የገባላት ኪዳን ነው፡፡ እግዚአብሔርን ለሚፈሩት፣ ለሚያከብሩት፣ ለሚወዱትና ለሚወዳቸው ሁሉ በተለያዩ ጊዜያት ብዙ ኪዳናትን ሰጥቷል፡፡ የኪዳነ ምሕረት ሥዕል በመባል የሚታወቀው ሥዕል በቤተ ክርሰቲያናችን በስፋት ከሚሳሉት የወላዲተ አምላክ ሥዕል ጭብጦች ውስጥ አንዱ ሲሆን። ከጌታችን ኢየሱስ ቃልኪዳን ስትቀበል በጎሎጎታ የሚያሳየው ሥዕል ትክክለኛው ገላጭ ሥዕል ሲሆን፤ ይህ ሥዕል እንደ ቤተ ክርስቲያኑ ስፋት የሚጨመረው ጭብጥ ሊለያይ ይችላል፡፡

ለምሳሌ በዚህ ሥዕል ዘይቤ ላይ የሚታዩት መላእክት ቁጥራቸው ሊበዛ አሊያም ሊያንስ ይችላል፡፡ በዚህ ሥዕል እመቤታችንና ጌታችን ቆመው አሊያም ተቀምጠው ጌታችን በቅዱሳን እጆቹ የእናቱን ቅዱሳን እጆች በመያዝ ቃል ኪዳን ሲገባላት አሊያም በቅዱሳት እጁ ቃል ሲገባላት የሚያሳይ ዓይነት ሥዕል ነው፡፡ በዚህ መልኩ እመቤታችን ከተሳለችባቸው አብያተክርስቲያናት መካከል ጎርጎራ ደብረ ሲና (17ኛው መ.ክ.ዘ)፣ አብርሐወ አጽብሐ (19ኛው መ.ክ.ዘ)፣ መቐለ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (20ኛው መ.ክ.ዘ)፤ ከጥንታውያን ብራና መጻሕፍት ከተመለከትን በአክሱም ጽዮን ቤተክርስቲያን ግምጃ ቤት የሚገኘው የ17ኛው መ.ክ.ዘ ተአምረ ማርያም ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ገዳማውያንም ዘወትር በሥዕሏ ፊት ቆመው ይለምኗታል፡፡ እርሷም ልመናና ጸሎታቸውን ታሳርጋለች፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸውመ እንካፈል፡፡

ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተሰጠው ኪዳን፣ ቀድመው ለነበሩ ኪዳናት ማለትም ኪዳነ አዳም፣ ኪዳነ ኖህ፣ ኪዳነ መልከ ጸዴቅ፣ ኪዳነ አብርሃም፣ ኪዳነ ሙሴና ኪዳነ ዳዊት መደምደሚያ ነው፡፡ ዘለዓለማዊ ስለ ሆነው የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳን እየታሰበም ዕለቱ በመዝሙር፣ በማኅሌትና በቅዳሴ ይከበራል፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን ለምንባል ለእኛ ለሐዲስ ኪዳን የቤተ ክርስቲያን ልጆችም ይህ አዲስ ውል የተደረገልን ለነፍሳችን ድኅነት በመሆኑ በስሟ እየተማጸንን እንዲሁም መታሰቢያዋን እያደረግን ለተራቡት ማብላት፣ ለተጠሙት ማጠጣትና የተቸገሩትን መርዳት ይገባናል፡፡ ገዳማውያን በበቃል ኪዳኗ ታምነው፣ ዘወትር በሥዕሏ ፊት በጸሎት ይተጋሉ፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና ከበረከታቸው እንካፈል፡፡

ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

22/04/2026

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Fuad Tamkin, Maru Misganaw

06/10/2025

☞ሰውን ሰው ያደረገው ስራ አይደለም
↩አህያም ይሰራል::
☞ሰውን ሰው ያደረገው ንግግር አይደለም.
↩በቀቀንም ይናገራል::
☞ሰውን ሰው ያደረገው እብደት አይደለም
↩ውሻም ያብዳል::
☞ሰውን ሰው ያደረገው ብልሐትአይደለም.
↩ዶልፊንም ብልሕ ነው::
☞ሰውን ሰው ያደረገው እንባ አይደለም
↩አዞም ያነባል::
☞ሰውን ሰው ያደረገው ጭንቀት አይደለም.
↩ፍየልም ይጨነቃል።
☞ሰውን ሰው ያደረገው ስለነገ ማሰቡ አይደለም
↩ጉንዳኖችም. ስለመጪው ክረምት አስበው በበጋ በቂ ምግብ ያዘጋጃሉ።

....
➡አስተሳሰቡ🔙 እና.
➡ አመለካከቱ ነው።
ሰውን ሰው ያደርገው ፈጣሪ ብቻ ነው ምክንያቱም
መልካም ጥበብ እና ማስተዋል ከፈጣሪ ዘንድ ነውና።

“የቀይ ባሕር ወሰን ተጋሪ ለመሆን ያነሳነውን ጥያቄ እንደስህተት ቆጠረዉ እዚህም እዚያም የሚንጫጩ አካላት አሉ፤ እንደተንጫጩ ይቀራሉ እንጂ የቀይ ባህር ጠረፍ ወሰን ተጋሪ መሆናችን አይቀሬ ነ...
03/06/2025

“የቀይ ባሕር ወሰን ተጋሪ ለመሆን ያነሳነውን ጥያቄ እንደስህተት ቆጠረዉ እዚህም እዚያም የሚንጫጩ አካላት አሉ፤ እንደተንጫጩ ይቀራሉ እንጂ የቀይ ባህር ጠረፍ ወሰን ተጋሪ መሆናችን አይቀሬ ነው.”

ጀኔራል አበባዉ ታደሰ (ትልቁ)

29/11/2024

31/10/2024

Opal

31/10/2024
01/06/2024

ጥላ ወጊ መተት /የሞት አጋንንት ድግምት/
/ማታ ተኝተው ጠዋት ሞቶ መገኘት፣ ጠዋት ታይቶ ከሰዓት መሞት/
/በድንገት እና ባልታወቀ ምንክያት መሞት/
/ልቤን እያሉ ወጋኝ እያሉ በጥላ ወጊ ድግምት በድንገት መሞት/
የጥላ ወጊ መተት በየትኛው ሕመም እራሱን ይደብቃል?
የጥላ ወጊ ወይም የሞት አጋንንት ሁነኛ መፍትሔ ምንድነው?
ቀጥሎ እንመለከታለን

ጸሐፊ ቀሲስ መ/ር ሄኖክ ወ/ማርያም
አቅራቢ አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

የአጋንንት ዓላማ እኛን የሰው ልጆች በሥጋም በነፍስም ገድለውን በሲዖል የራሳቸው ማድረግ ነው፡፡ ጥላ ወጊ የሚባለው አጋንንት ጎታቾች በአጋንንታዊ ድግምታቸው አጋንንትን በመሳብ በሰው ላይ በማቆራኘት እንዲሞቱ የሚያደርጉበት ነው፡፡
ጥላ ወጊ አጋንንት ከሞት አጋንንት ጋር በዓላማ አንድ ቢሆንም ጥላ ወጊ የራሱ ገቢር አለው፡፡ ይህም ገዳዩ ወይም አስገዳዩ ባስደገመው ለምሳሌ በትር፣ አንካሴ፣ ጦር የሚገለው ሰውን ጥላ በመውጋት ለሞት የሚዳርግበት ክፉ አጋንንታዊ ተግባር ነው፡፡ የሞት አጋንንት ግን እንደ ማንኛውም አጋንንት በድግምት የሚሳብና ሰውን እንዲገድል የሚላክ አጋንንት ነው፡፡ ጥላ ወጊ አጋንንትም ልክ እንደ ሞት አጋንንት ያለ ገቢር ታዞም ይገድላል፡፡

የጥላ ወጊም የሞት አጋንንትም ዋና ተግባራቸው ሰውን መግደል እና መግደል ብቻ ነው፡፡
እዚህ ላይ ልብ ልንለው የሚገባው የሞት አጋንንትን ከመላከ ሞት መለየት ነው፡፡ መልአከ ሞት የሚባለው ሰዎች እድሜ ዘመናቸውን ኃጢአትን ሲሰሩ ኖረው ጊዜ ሞታቸው ሲደርስ ነፍሳቸውን ከሥጋቸው ለመለየት ከእግዚአብሔር የሚላኩ ናቸው፡፡ ዘመናቸውን በጽድቅ ሥራ ያሳለፉ እና በመጨረሻ ዘመናቸው በንስሐ የተመለሱ ሰዎችን ደግሞ ነፍስ ከሥጋ ሊለይ የሚመጣው መልአከ ብርሃናት ናቸው፡፡ ስለዚህ መልአከ ሞት ታዛዥነቱ ለሰው ሳይሆን ለእግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡ በመተት እና በድግምት የሚታዘዘው የሞት አጋንንት በሰው ሰውን ለመግደል የሚላክ ነው፡፡

ጌታችን በእለተ አርብ በቀራንዮ አደባባይ በተሰቀለበት ጊዜ የጌታችንን ቅድስት ነፍሱን ከክብር ሥጋው እለያለሁ ብሎ በድፍረት የመጣው መልአከ ሞት ሳይሆን የሞት አጋንንት የሆነው ሰይጣን ነው፡፡ መልአከ ሞት በእግዚአብሔር ትእዛዝ የሰውን ነፍስ ለይና አምጣ ሲባል ብቻ የሚታዘዝ እንጂ በራሱ ፈቃድ የሞት መዘዝ የሚያመጣ አይደለም፡፡ የሞት አጋንንት ተግባሩን በሁለት መልክ የሚሠራ አጋንንት ነው፡፡
አንደኛው በራሱ አጋንንታዊ ፍቃድ በሰው ላይ በመቅናት ለጥፋት እኛ ለሞት የሚዳርግ ነው፡፡ ሁለተኛው ለርዕሳችን የመረጥነው በሰው ታዞ ሰውን ለጥፋት እና ለሞት የሚዳርግ ነው፡፡

የሰው ልጅ አጋንንትን ለክፋት፣ ለጥፋት እና ለሞት ማዘዝ ከጀመረ ቆይቷል፡፡ ለዚህም ነው እግዚአብሔር ሙሴን ‹‹አስማተኛ፣ መተተኛ፣ በድግምት የሚጠነቁልም፣ መናፍስትንም የሚጠራ፣ ጠንቋይም፣ ሙታን ሳቢም በአንተ ዘንድ አይገኝ›› ብሎ ያዘዘው፡፡ በዛን ዘመን የሰው ልጅ ከአጋንንት ጋር ምን ያህል ቁርኝት እንዳለውና ሰዎች በዛን ጊዜ አጋንንትን ለክፉ ተግባራት እና ለሞት ይጠቀሟቸው እንደነበር የሚያሳየን ነው፡፡ /ዘዳ 18÷11/
እግዚአብሔር ለሙሴ ከገለጠለት ውስጥ ‹‹መናፍስት የሚጠራ፣ሙታን ሳቢ›› የሚለው ለትምህራትችን ትልቅ ግብአት ነው፡፡ መናፍስት ጠሪ የሚባሉት አጋንንትን ለክፉ ተግባራት የሚገለገሉባቸው እና የሚያዟቸው ሰዎች ናቸው፡፡ ሙታን ሳቢ የሚባሉትም የሞተ ሰውን በአጋንንት ጥበብ እየጠሩ የሚያናግሩና አጋንንትን ለሞት የሚጠቀሙ ናቸው፡፡ ስለዚህ በጥቅሱ መግቢያ ላይ እንዳነበባችሁት የሞት መናፍስትን የሚጠሩት፣ ሙታንን የሚስቡት አስማተኞች በመተታቸው እና በድግምታው መሆኑን ነው፡፡

በተለያየ ገድለ ቅዱሳን ላይ ጠንቋዮች፣ አጋንንት ጎታቾች፣ መተት መታቾች አጋንንትን እየሳቡ ቅዱሳንን ለማጥፋት ሲሞክሩ ይታያል፡፡ ቅዱሳኑም በጸሎት የበረቱና በእግዚአብሔር መለኮታዊ ጥበቃ ሥር ስለተጠለሉ በመሆናቸው አጋንንቱ እንኳን ሊገድላቸው ቅዱሳኑ አጋንንቱን ሲያጠፏቸው ይታያል፡፡

ወዳጆቼ እግዚአብሔር ወዳጆቹን ከሚፈትንበት መንገድ አንዱ በመከራና በአጋንንት ነው፡፡ አንዳንዴ በመንፈሳዊ ሕይወታችን፣ በጸሎት እና በሰማያዊ አምልኮታችን የጸናን፣ በእምነታችንም በእርሱ ላይ የተደገፍን ብንሆን እንደ ኢዮብ አጋንንት ሥጋዊ ሕይወታችንን ለማመሰቃቀል፣ ነፍሳችንን ከሥጋችን ለመንቀል እንደ ፈተና ሊታዘዝብን ይችላል፡፡ ስለዚህ በጸሎት የተጋን፣ በእግዚአብሔር ላይ የተደገፍን የሞት አጋንንት ሰለባ ባንሆንም ለፈተና ሊቃጣብን ይችላል፡፡

በመተት መታቾች፣ በድግምት ደጋሚዎች የሞት አጋንንት የሚላከው ተቀናቃኜ፣ ጠላቴ በሚሉን ሰዎች ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች የእኛን ነገር እና እኛን ለማጣፋት፣ በሞት ሕይወታችንን ለመቀማት ገንዘብ በመክፈል፣ የተለያዩ ነገሮችን በመገበር ጥቃት ሊያደርሱብን ይችላሉ፡፡ ሰውን በጥላ ወጊ ወይም በሞት አጋንንት ለማጥፋት የሚፈልጉ ክፉ ሰዎች ጠንቋዩች፣ ድግምተኞች ጋር በመሄድ ‹‹እከሌን አጥፋልኝ›› በማለት አንዳንዴም ደጋሚው እራሱ ‹‹ምን ችግር አለው አጠፋልሃለሁ›› በማለት በመጠየቅ የሚፈጽሙት ነው፡፡ ሰውን በጥላ ወጊ ወይም በሞት አጋንንት ለመግደል እና ለማስገደል የሚጠይቁትን ሰዎች ነብዩ ኢሳይያስ ‹‹በድግምት የሚጠነቁሉትንም መናፍስት ጠሪዎቻቸውንም ጠንቋዮቻቸውንም ይጠይቃሉ›› ብሏል፡፡ /ኢሳ 19÷3/

ወዳጆቼ በጥላ ወጊ ሰዎች ጥቃት ሲደርስባቸው በአስደንጋጭ እና በድንገት ሊሞቱ ይችላሉ፡፡ በጥላ ወጊ ወይም የሞት አጋንንት የተደገመበት ሰው ሞቱ ይናገራል ወይም ምልክት አለው፡፡

በጥላ ወጊ የሞተ ሰው፦
አንደኛ የሚሞተው በጤናው ነው፡፡ ሳይታመም፣ ቤተሰብ ሳያስታምመው በድንገት ነው የሚሞተው፡፡
ሁለተኛ በድንገት ተዝለፍልፎ በላብ ተዘፍቆ ጸጥ ይላል ከዛም ይሞታል፡፡
ሦስተኛ ልቤን ወጋኝ ብሎ በድንገት ይሞታሉ፡፡ /የልብ ድካም በሽታ እንዳለ ሆኖ/
አራተኛ እራሴን ወጋኝ ይላሉ፡፡
አምስተኛ ሰውነቴን አቃጠለኝ፣ ተንገበገቡኩ ብሎ ይሞታሉ፡፡
በአጠቃላይ በጥላ ወጊ ወይም በሞት አጋንንት የመጣ ሞት ጊዜ የማይሰጥ፣ ለማስታመም እና ለሐኪም ቤት የማያዳርስ ነው፡፡

ወዳጆቼ ስንቾቹ በጥላ ወጊ ወይም በሞት አጋንንት ያለ ቀናቸው፣ ያለ ጊዜያቸው በሰው ተንኮል ለሞት በቅተዋል፡፡ ስንት እውቀት እና ሐብት እያለው ለስንት ሰው መትረፍ እየቻለ በራሱ፣ የቅርቤ በሚላቸው ሰዎች በሞት አጋንንት ለሞት በቅቷል፡፡ ስንቱ ማታ በሰላም ተኝቶ ጠዋት ሞቶ ተገኝቷል፡፡ ስንቱ ጠዋት ታይቶ ከሰዓት መሞት ለሰሚ አሟሟቱ ጉድ ተብሏል፡፡ ይህ ሁሉ አንድም በጥላ ወጊ ወይም በሞት አጋንንት ነው፡፡ ሌሊት በተኙበት የሞት አጋንንት እያነቀ፣ እየደፈቀ ስንቱን ገሏል፡፡

በክፍል ፪
የጥላ ወጊ መተት በየትኛው ሕመም እራሱን ይደብቃል? የሚለውን እናያለን።

ይቀጥላል

አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

  From wolo delanta area.
17/05/2024


From wolo delanta area.

Address

Addis Ababa

Telephone

+251988746363

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gemstone Buy & Sale In Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gemstone Buy & Sale In Ethiopia:

Share