Adey Business

Adey Business Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Adey Business, Business service, AA, Addis Ababa.

08/02/2024

ወንበር ላይ ያለ ሰው ማመን ያቆምኩበት አጋጣሚ!

ከዓመታት በፊት አንድ ወዳጃችን ታሞ አማኑኤል ይዘነው ሄድን ! በስርዓት እንግዳ መቀበያው ውስጥ ተቀምጠን እሱም በስርዓት ህመሙ በፈቀደለት መጠን የማይያያዙ ነገሮች እያወራ ነበር። ድንገት ግን ወንበር እያነሳ መወርወር ጀመረ! በተለይ እኔን ካልገደልኩ አለ!

ዘልየ ወንበር ላይ ቆምኩ (ደመነፍስ መሰለኝ) ከውጭ ሰዎች ሲንጫጩ እሱም ከእኔ ፊት ለፊት ያለ ወንበር ላይ ወጥቶ ቆመ! ታማሚም ወንበር ላይ አስታማሚም ወንበር ላይ ! ነርሶችና ሁለት ሰዎች ተሯሩጠው ገቡ! አንዱ የተቀባበለ ስሪንጅ ነገር ይዟል ....ወደኔ በቀስታ እየተጠጋ " ማንም አይነካህም አይዞህ ውረድ ወንድሜ " እያለ እንደህፃን ያባብለኛል! ሊወጋኝ!

"እንዴ እኔ አይደለሁም እሱ ነው...ይዘነው መጥተን ...ከዛ ድንገት እቃ ሲያነሳ ...ከዛ ወንበር ሲያነሳ ...ከዛ " አልኩ በፍርሃት በተረበሸና በተኮላተፈ ድምፅ! ደግሞ ስናገር በጣም ነበር የምጮኸው! ወደሱ ሲዞሩ ከእኔ በጣም በተረጋጋና ለስለስ ባለ ድምፅ ወደእኔ እየጠቆመ "እሱ ነው ዶክተርየ፤ እባካችሁ እርዱት " አለ። ሁሉም አምነውት ነበር ....ሌላ ጓደኛችን መሃል ገብቶ ባያተርፈኝ .... ከዛ ቀን በኋላ ነው በድምፅም በምስልም ከመድረክ የጠፋሁት! እና ወንበር ላይ ያሉ ሰዎችንም አላምንም! Alex abrham

02/02/2024
01/02/2024
31/01/2024

ደረስጌ ማርያም - በጥር የምትደምቀው ሌላዋ የቱሪዝም ሙሽራ

| የአስተርዮ ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል በታሪካዊቷ ደረስጌ ማርያም ኃይማኖታዊ ትዉፊቱን ጠብቆ እየተከበረ ነው።

ደረስጌ ማርያም በሰሜን ጎንደር ዞን ጃናሞራ ወረዳ ከመካነ ብርሃን ከተማ በሰሜን ምዕራብ አቅጣጫ 2 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች።

ደረስጌ ማርያም በ12ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በአድያም ሰገድ እያሱ እንደተመሰረተች ይነገርላታል። በ1818 ዓ.ም ደግሞ የስሜኑ ገዥ ራሥ ውቤ ኃይለማርያም እንደገና አነጿት። አሁን የያዘችውን ኪነ ሕንፃ እና ቅርስ በራስ ውቤ አማካኝነት ያገኘችው ነው።

በደረስጌ ማርያም የኢትዮጵያውያን የአንድነት መንፈስ ውጥኑ የተመሠረተበት እና አጼ ቴዎድሮስ በከፍታ ላይ ቆመው ለንግሥና የተቀቡበት ታሪካዊ ሰገነትም በቅጥር ግቢው ውስጥ በክብር ቆሞ ይገኛል።

የአጼ ቴዎድሮስ ሕጋዊ ባለቤት እና የልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ እናት የእቴጌ ጥሩወርቅ የትውልድ ቦታም ናት - ደረስጌ ማርያም። ታሪካዊቷ ደብር የዘመነ መሳፍንት ፍፃሜ የተበሰረባት ማማ በመሆኗም ትታወቃለች። ይህ የሆነው በወርሃ የካቲት 1847 ዓ.ም ነበር። በወቅቱ የሰሜን ገዥ የነበሩት ደጃች ውቤ የኢትዮጵያ ንጉሥ ለመኾን ከግብጽ አቡነ ሰላማ የሚባሉ ወጣት ጳጳስ አስመጥተው ለመንገሥ በዝግጅት ላይ ነበሩ፡፡

ኢትዮጵያን አንድ ለማድረግ ሲፋለሙ የነበሩት ካሳ ኃይሉ ይሄን ሲሰሙ ደጃች ውቤ ሊነግሱ ሁለት ቀን ሲቀራቸው ወደ ደረስጌ ገሥግሰው ገጠሟቸው።

ካሳ ኃይሉ በጦርነቱም ደጃች ውቤን ድል አድርገው ደጃች ውቤ ለመናገሻ ባሰሩት አዲስ ሕንፃ እና በአስመጧቸው ጳጳስ ተቀብተው “ዳግማዊ ቴዎድሮስ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ” ተብለው ነገሡ።

የዘመነ መሳፍንት መገርሰስ እና የአንዲት ኢትዮጵያ ሀገርነትም በደረስጌ ተበሰረ፡፡ በዚህም ደረስጌ ለዘመናዊቷ ኢትዮጵያ እና ለአጼ ቴዎድሮስ ትልቅ ህልም መነሻ መሠረት ኾና በታሪክ ተጻፈች።

በወርቅ ቅብ ጉልላት አጊጣ የተሠራቸው ደረስጌ ማርያም ከደጃች ውቤ እና ከዳግማዊ ቴዎድሮስ ጋር የሚገናኙ በርካታ ቅርሶችን የያዘች ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡

ደረስጌ ማርያም በወርቅ እና በብር የተንቆጠቆጡ ከበሮዎች፣ ከጎሽ ቀንድ የተሠሩ ዋንጫዎች የነገሥታት ዘውዶች፣ የንግሥና አክሊሎች እና ሌሎችም ቅርሶች ይገኛሉ። የተለያዩ የወርቅ እና ብር መስቀሎች፣ የብራና መጻሕፍት እና ሌሎችም ቅርሶች በቤተ ክርስቲያኗ እቃ ቤት የሚገኙ ሲኾን ቤተ ክርስቲያኗ ዙሪያ በእድሜ ጠገብ የጽድ ዛፎች የተከበበ ነው፡፡

ደረስጌ ማርያም በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ አቅራቢያ በመገኘቷ ከፍተኛ የመጎብኘት ዕድል አላት።

ሕዳር 21 እና ጥር 21 ዓመታዊ የንግሥና ክበረ በዓሏም ከተለያዩ አካባቢዎች በመጡ ምእምናን እና ሀገር ጎብኝዎች ጭምር ይከበራል። ደረስጌ ማርያም ዛሬ በድምቀት ከሚከበሩ የጥር ፈርጥ ከሆኑ ቦታዎች ውስጥ አንዷ ናት። በዓሉ እንደ ወትሮው ሁሉ ሃይማኖታዊ ይዘቱን ጠብቆ እየተከበረ ይገኛል።

አሚኮ

31/01/2024

"ኢማን ማለት እውነትን ልትናገረውና ልትኖረው ነው፤ መዋሸትህ እንጂ ብማያወጣህ ቦታ።"
© ኡስታዝ አቡበከር አሕመድ

Address

AA
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Adey Business posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share