Sabit Nura

Sabit Nura personal blogs

30/07/2025

በአላህ ቤቶች ላይ የሚፈፀሙ ተከታታይና የማያባሩ ጥቃቶች በአስቸኳይ ይቁም!

ከኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጋራ ፎረም የተሰጠ መግለጫ

ሐምሌ 21 ቀን 2017: አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጋራ ፎረም በተለያዩ ጊዜያትና በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች በአላህ ቤቶች በሆኑት መስጂዶች ላይ እየተፈፀመ ያለውን ተደጋጋሚና ስልታዊ ጥቃት እጅግ እያሳሰበው ይገኛል። መስጂድ ሙስሊሞች ግንባራቸውን ለአላህ የሚያስጠጉበት፣ የመንፈስ እርጋታን የሚያገኙበትና የማህበረሰብ አንድነታቸውን የሚያፀኑበት የተቀደሰ ስፍራ ሆኖ ሳለ በመንግስት ዉስጥ የተሸሸጉ አንዳንድ አካላት ድርጊት እጅግ አሳሳቢና የሀገርን ሰላም የሚያናጋ አደገኛ አካሄድ ነው። የዚህ ስልታዊ ጥቃት ሰለባ የሆነው በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ መልካ ኖኖ ክፍለ ከተማ ውስጥ ህጋዊ የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት የነበረው አቡዘር መስጂድ ሐምሌ 19 ቀን 2017 በሌሊት ጨለማ ተገን ተደርጎ በህገ-ወጥ መንገድ መፍረሱ ነው።

ይህ መስጂድ ለአካባቢው ማህበረሰብ ብቸኛ የመስገጃ ስፍራ ከመሆኑም በላይ፣ ከ260 በላይ ህፃናት የዲን ትምህርት እየቀሰሙበት ትውልድ የሚታነፅበት የመድረሳ ማዕከል ነበር። ከዚህም በላይ ይህ የጥፋት ድርጊት የተፈፀመው ማህበረሰቡ ለመጅሊስ አመራሮች ምርጫ በሚንቀሳቀስበትና በመስጂዱም የምርጫ ሂደት እየተከናወነ በነበረበት ወሳኝ ወቅት መሆኑ፣ የድርጊቱን ክብደትና ዓላማ ይበልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል። ይህ ድርጊት ከዚህ ቀደም በዚሁ ከተማ ብቻ ከ31 በላይ መስጂዶች ከፈረሱበት አሳዛኝ ታሪክ የማይነጣጠል የማህበረሰባችንን ትዕግስት የሚፈታተን ነው።

በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ አስተዳደር የተቀደሰ የአላህ ቤት ሲደፈር ይህ የመጀመሪያው አይደለም፤ ዛሬም ይህን የማፍረስ ፍላጎት ባለመግታት በክልሉ ሸገር ከተማ የሚገኙ በወቅፍ የተሰጡ መስጂዶችን የማፍረስ ዝግጅት መኖሩ በልዩ ልዩ መልኩ እየተገለፀ ይገኛል። ይህ ተግባር በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች በመስጂዶች ላይ እየተፈፀመ ያለ የስልታዊ ዘመቻ አካል መሆኑን እንገነዘባለን። በአዲስ አበባ ከተማ በተባረክ መስጂድ ላይ በሌሊት የተፈፀመው ተመሳሳይ የፈረሳ ድርጊትና መስጂዱን የማፍረስ ዛሬም ያለው ፍላጎት፣ በአፍንጮ በር አቅሳ መስጂድ ላይ የተሞከረው ህገ ወጥ ተግባር፣ በካዛንቺስ ባንቢስ ከፍ ብሎ የሚገኘው አሊፍ መስጂድን የማፍረስ ዕቅድ እንዲሁም ሌሎች በርካታ መስጂዶችን ለማፍረስ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን የሚጠቁሙ መረጃዎች ጥቃቱ በአጋጣሚ ሳይሆን ታቅዶ የሚፈፀም፣ ሙስሊሙን ዒላማ ያደረገ ዘመቻ አካል መሆኑን በግልፅ ያመላክታሉ።

ህዝበ ሙስሊሙ አደራ የሰጣቸው የኦሮሚያ ክልል መጅሊስና የሸገር ከተማ መጅሊስ አመራሮች ጆሮ ዳባ ልበስ ማለታቸውና በዝምታ ማለፋቸው፣ ዝምታቸው ከወንጀሉ ተባባሪነት የማይተናነስ ታሪካዊ ስህተት መሆኑን ሊገነዘቡ ይገባል።

ህዝበ ሙስሊሙ በሀገር ደረጃ እየተሰሩ የሚገኙ የልማት ስራዎች ላይ በሰፊው እየተሳተፈና ለውጤታማነቱ ትብብር እያደረገ በሚገኝበት በዚህ ወቅት፣ የመንግስት አካላት ለሃይማኖት ተቋማቱ ጥበቃና ምቹ ሁኔታን መፍጠር ሲገባቸው፣ የማፍረስ እርምጃ ውስጥ መገኘታቸው የህዝቡን ቀናኢነት ወደኋላ የሚጎትት ነው። በተለይ የሸገር ከተማ ከንቲባ አቶ ተሾመ አዱኛ በሚመሩት አስተዳደር ውስጥ ከዚህ ቀደም "ከአሁን በኋላ መስጂዶች አይፈርሱም" ተብሎ የተሰጠው ህዝባዊ ቃል ተቀልብሶ ጨለማ ተገን በማድረግ ህጋዊ መስጂድን ማፍረስ ህዝብን ከመንግስት ጋር በቀጥታ የሚያጋጭና በቀጣይ በሚኖሩ ግንኙነቶች እምነትን የሚሸረሽር አደገኛ ተግባር ነው። ይህ ድርጊት ከዚህ በኋላ በማህበረሰቡና በአስተዳደሩ መካከል በሚደረጉ ስምምነቶች ላይ ከባድ የጥርጣሬ ጥላ የሚያጠላና ተዓማኒነትን የሚያሳጣ ይሆናል። የመስጂድ ፈረሳን እንደ ቀላል የአስተዳደር እርምጃ መመልከት አይቻልም፤ ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ድርጊት የሰው ህይወት እንደጠፋ፣ በርካታ ሙስሊሞች ፈረሳውን በመቃወም ሂደት ውስጥ የአካል ጉዳተኛ እንደሆኑ መዘንጋት የለበትም።

በመሆኑም የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጋራ ፎረም ይህንን አጥፊ ድርጊት በፅኑ እያወገዘ የሚመለከተው የመጅሊስ መዋቅር እንዲሁም በየደረጃው የሚገኙ የመንግስት አካላት ይህንን በመስጂዶች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት በአስቸኳይ እንዲያስቆሙና ወንጀለኞችን ለህግ እንዲያቀርቡ አጥብቆ ይጠይቃል። የክልሉ መጅሊስ አመራሮችም የህዝቡን አደራ እንዲወጡና ግልፅና ጠንካራ አቋም እንዲይዙ እናሳስባለን። በመጨረሻም መላው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች፣ በተለይም የመስጂድ አስተዳደሮች የአላህን ቤቶች ከጥቃት ለመጠበቅ ከምንጊዜውም በላይ በላቀ ንቃትና ጥንቃቄ ቀን ከሌሊት እንድትጠብቁ የአደራ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

የአላህን ቤቶች መጠበቅ የሁላችንም ሃላፊነት ነው!

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጋራ ፎረም
ሐምሌ 21 ቀን 2017
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

30/07/2025
27/07/2025
09/07/2025

ጥሪ አደርጋለሁ! Waamichan Taasisa!
🎯🎯🎯🎯🎯🎯🎯🎯🎯🎯🎯🎯

እውነት ለዑለሞቻችን የሚታሰብ ከሆነ የሚከተሉትን በአፋጣኝ እንዲተገበሩ ጥሪ አደርጋለሁ።እነርሱም: -

1) ለሁሉም ዑለሞቻችን የአካዳሚክ ትምህርት የሚያገኙበትን፥ የአስተዳደርና አመራር፥ የሀገሪቱንና የሙስሊሞችን ታሪክ፥ ነባራዊ ሁኔታን፥ ስነማህበረሰብ ሳይንስና የችግር አፈታት ስልቶች ዙሪያ ላይ እውቀትና ግንዛቤያቸውን የሚያሳድጉበትን መንገድ በአጫጭር ስልጠና፥ በኦንላይንና በርቀት ትምህርት ወይም በየመስጊዱ ኢማሞችን በየዘርፉ የማብቃት ስልቶች ይቀየሱ።ከነርሱ ዉስጥ ደግሞ ለመብቃት ቅርብ የሆኑት ደግሞ ተለይተው የአጭር ጊዜ ተከታታይ ስልጠና ይሰጣቸው።

2) በተግባር ደረጃ ደግሞ ሰፊና በነጻነት የሚሠሩበት የዑለማ ምክር ቤት መዋቅርን አሁን ካለው ለይስሙላ ከተቀመጠው መዋቅርና አካሄድ ወጥቶ ከፌደራል እስከ መስጂድ የተዋቀረ የራሱ በጀትና አቅም ያለው ሆኖ ይዋቀር!

3) ዓሊሞች የአስተዳደርና የአመራር ልምድ እንዲያገኙ በመላ ሀገሪቱ በሁሉም መስጂዶች በአስገዳጅ ደረጃ የመስጂድ ኢማሞችን በመስጂዱ የአስተዳደር ኮሚቴው ዉጭ የሆኑበት አሰራር ተሽሮ በመስጂድ ኮሚቴ ዉስጥ እንዲሳተፉ ይደረግ።

4) በሁሉም እርከን ለእርከኑ የሚመጥን የአስተዳደር ተሞክሮ ያላቸው ዓሊሞች፥ ኢማሞች፥ ዱዓቶችና መሻይኮች እየተመረጡ በመጅሊስ ዉስጥ የመጅሊስ የሥራ አስፈጻሚ አባል ይደረጉ።

5) በሀገር ዓቀፍ ደረጃ መሪና አስተዳዳሪ የመሆን ከፍተኛ ተስፋ የሚጣልባቸው ዓሊሞችና ዱዓቶችን ከየክልሉ መርጦ ቢያንስ ለሁለት ዓመት የሚያሰለጥን የመጅሊስ የአመራር ማሰልጠኛ ማዕክል ይቋቋም።

6) የመስጂድ ኢማሞች፥ የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ቃዲዎች፥ ዑለሞችና ዱዓቶች የግድ ዘመናዊ ትምህርት የተማሩ እንዲሆኑ ቢቻል ቀድሞ ከኢልሙ ጎን ለጎን በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች በዲግሪ የተመረቁ የሚሆኑበት ሁኔታ ይታሰብበት።አልያም ሁለቱንም በአንድነት ያጣመረ ዩኒቪርሲቲ ይቋቋም።

ከላይ ይሁን ሁሉ ያነሳሁነት የሚከበሩ፥ የሚደመጡና ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆኑ ዓሊምም መሪም የሆኑ የሰላት(የመስጂድ) ብቻ ሳይሆን የሁሉም ነገር ኢማም(መሪ) እንዲኖሩን ከመፈለግ ነው።

ዓሊሞች ይህን ያሟሉ ስልም አካዳሚክ የተማሩ ሁሉ የመሪነትና የአስተዳዳሪነት ብቃት አላቸውም እያልኩ አይደለም። ለመሪነትና አስተዳዳሪነት የራሱ ስነልቦና፥ የተነሳሽነት፥ የእውቀት፥ የክህሎትና የልምድ ዝግጁነት እንደሚያስፈልግ አጥቼው አይደለም።

Waamichan Taasisa
🎯🎯🎯🎯🎯
Dhuguma Ulamaa'ota keenyaaf kan yaadamu yoo ta'e kanneen itti aanan kun hatattamatti akka raawwataman waamichan taasisa. Isaa isaanis:-

1) Tooftaaleen ulamaa'onni keenya hundi barnoota akaadaamii ittiin argatan, ga'umsa hooggansaa, seenaa biyyaa fi Muslimootaa, haala qabatamaa, saayinsii hawaasaafi maloota rakkoo furuu irratti beekumsaafi hubannoo isaanii karaa ittiin gabbifatan leenjii gaggabaabaa, barnoota toora onlaayiniifi fageenyaa ykn masjiidatti imaamota roga hundaan ga'oomsuuf tooftaaleen dandeessisan haa diriiran. Isaan keessaa ammoo kanneen ga'oomuutti dhihoo ta'an adda ba'anii leenjiin gabaabaan walitti fufaan haa kennamuuf.

2) Sadarkaa hojii qabatamaatti ammoo caaseffamni Mana Maree Ulamaa’otaa bal’aafi bilisaan keessa hojjachuu danda'an adeemsa caaseffama fakkeessaa ykn kan maqaa qofaa amma jiru keessaa ba'ee, federaalaa hanga masjiidaatti kan baajataa fi dandeettii mataa isaa qabu ta'ee haa caaseffamu!

3) Hayyoonni muuxannoo bulchiinsaa fi hooggansaa akka horataniif, masjiidota guutuu biyyattii hunda keessatti sadarkaa dirqisiisaatti hojmaatni imaammanni masjiidaa koree koree bulchiinsa masjiidaatiin ala itti ta’an haqamee koree masjiidaa keessatti akka hirmaatan haa godhamu.

4) Roga maraanuu aalimonni, imaamoonni, du'aatonnii fi mashaa'ikkan rogichaa muuxannoo bulchiinsaa qaban filatamanii majlisa keessatti miseensa koree hojii raawwachiiftuu majlisa haa taasifaman.

5) Sadarkaa biyyalessaatti Giddugalli leenjii hooggansa Majlisaa aalimotaafi du'aatota gaggessaafi bulchiinsa akka ta'an abdataman naannolee mara irraa filee xiqqaatu waggaa lamaaf leenjisu haa ijaaramu.


6) Imaamonni masjiidaa, manni murtii sheri'aafi qaadiin, ulamaa’onniifi du'aatonni dirqama barnoota ammayyaa kan baratan akka ta'an, yoo danda'ame ammoo duursee ilmiidhaan cinaatti dameewwan barnootaa garaa garaatiin digiriidhaan kan eebbifaman haalli isaan itti ta'an itti haa yaadamu. Yookaan ammoo Yunivarsiitiin lamaan isaaniiyyuu walitti hammate haa hundaa'u.

Kanin kanaa olitti waan kana mara kaase aalimoota dhageettii qaban, dhiibbaa uuman, aalimas hoogganaas ta'an, kan salaata (masjiidaa) qofa osoo hin taane imaamota (gaggeessaa) waanuma maraa akka qabaannu barbaaduu irraa ka'ee tani.

Aalimonni kana haa guuttatan yoon jedhu kanneen akkaadaamii baratan marti dandeettiifi ga'umsa gaggeessummaafi bulchinsaa qabu jechaa hin jiru.

Gaggeessummaafi bulchiinsaaf qophaa'ummaa xiinsammuu, kaka’umsaa, beekumsaa, dandeettii fi muuxannoo mataasaa akka barbaachisu wallaalee miti.

04/05/2025

የተባረክ መስጂድ እጣ ፋንታ‼ #ሼር ‼

ተባረክ መስጂድ የመጨረሻ ደረጃ ላይ ደርሷል ። ዛሬ ቦታው ላይ ሰጣ ገባ እየተደረገ ውሏል። ይህም ቦታው ላይ ስራ ካልሰራን የሚሉ አካሎች ሊረብሹ ሙካራ ጀምረዋል።

ዛሬ በቦታው ላይ እቃ እናወርዳለን የሚል የዱባይ ካምፓኒ ኤግል በመምጣት በምታዩት መልኩ ክፍተት ለመፍተር ታድቦ የነበረ ቢሆንም በርብርብ የተወሰነ መረጋጋት እንዲሰፍን ተደርጓል ።

ይህ ሂደት ነገ ከነጎዲያ ቦታውን ለመውሰድ የታሰበ እና መስጂዱን አደጋ ላይ ለመጣል የታቀደ መሆኑን የአካበቢው ማህበረሰብ እየተናገረ ይገኛል።

እስካሁን ከመጅሊስም ሆነ ከሚመለከተው አካል የተሰጠ ምላሽ የለም። መጅሊስ ወደ ከንቲባ ቢሮ የላከው ደብዳቤ መልስ አልተሰጠውም ። ቀጣይ እጣ ፋንታው ምን ይሆን?

ንቁ በጋራ ተንቀሳቀሱ ‼

26/04/2025

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sabit Nura posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Sabit Nura:

Share