29/01/2025
በአስቸኳይ ይታረም ❎
ያስተምሩ ሰዎችን ግን አያታልሉ!
"ያለምንም መነሻ ገንዘብ ዶላር የሚያስገኝ ቢዝነስ⁉️"
ሰሞኑን
"ያለምንም መነሻ ገንዘብ ዶላር የሚያስገኝ ቢዝነስ" በሚል በebs Tv የተሰራጨው አደገኛና አሳሳች መልዕክት ከአንድ ኃላፊነት ሊወስድ ከሚገባው ሚድያ(Mainstream Media) የሚጠበቅ አይደለምና ቶሎ እርምት ሊወሰድበት ይገባል።
Commercial እንደመሆኑ ሚድያው የአንድን ድርጅት አገልግሎትም ሆነ ምርት ማስታወቂያ መስራቱ ችግር ባይኖረውም ከእውነታው እንዲሁም ከሀገራችን ህጋዊ ማዕቀፍ ጋር የሚቃረን ሐሳብ ለኅብረተሰቡ በዚህ ሁኔታ መልቀቁ ግን አግባብ የሌለው መሆኑ መታወቅ አለበት።
ይህ ማስታወቂያ አሳሳች እንዲሁም ከእውነታው የራቀ ሲሆን አንድን ውስብስብ ጉዳዮች (Trading, investment, crypto,....) ለ2 ወር በሚሰጥ ቁንፅል ስልጠና እንደ አስተማማኝ የገቢ መንገድ አስመስሎ መሳልና በዚህ ሚድያ መተላለፉ ልክ አይደለም።
ለማታወቂያ በሚመስል ሁኔታ የተዘጋጀው ፕሮግራም የዘነጋቸው ዋና ዋና ጉዳዮች በአጭሩ ለማስቀመጥ ያህል፦
1. ያለ ካፒታል የሚደረግ ምንም ንግድ አለመኖሩ፡
ልክ እንደ ማንኛውም ንግድ ካፒታል የሚፈልግ መሆኑና ይልቁንስ ሰፊ ልምምድና የስሜት ብስለት የሚጠይቅ እንዲሁም ሰዎችን በቀላሉ ወደ ስሜት ስለሚከት አንድ ጊዜ ብቻ ሳይሆን ብዙ ጊዜ ለኪሳራ ሊዳርግ የሚችል አደገኛ ቢዝነስ መሆኑ።
2. ከፍተኛ የመክሰር አደጋ ያለበት ዘርፍ መሆኑ
ጥናቶች እንደሚጠቁሙት ከ80% ጀማሪዎች በመጀመርያ አመታቸው እንደሚከስሩና ዘርፉ የአጭር ጊዜ ትርፍ ሳይሆን ረጅም ጊዜ ሀብት እሳቤን ለተላበሱ ጥቂት ኢንቨስተሮች(ዋረን ባፌቶችን (Warren Buffets)) የሚመች መሆንና በተለይም እንደ crypto, forex, የመሳሰሉ ግምታዊ(Speculative) ገበያዎች አደጋቸው የከፋ በመሆኑ።
3. ዘርፉ ላይ የሰፋ ማጭበርበርና ማሳሳት ያለ መሆኑ።
የኦንላይን ንግድ በብዙ አሳሳች ደላሎች ፣ የውሸት ሐተታ ሰጪዎች ፣ ስካመሮች ... የሞሉበት በመሆኑና ዘርፉ በባህሪው ከፍተኛ የሆነ ስሜትን የመቆጣጠር ክህሎትና የዳበረ የቢዝነስ ትንተና የሚጠይቅ ስለሆነ ለመጭበርበር የተጋለጠ መሆኑ።
4. ህጋዊነት ያልተከተለ እንዲሁም ስነ ምግባርን የጣሰ
እስክ አሁን ባለን መረጃ የክሪፕቶም ሆነ ሌላ የኦንላይን የግብይት ስራ ጥንቃቄ የተሞላበትና ከህግ አኳያ ጥብቅ ክትትል የሚደረግበት መሆኑ በተለይ እንደ Crypto አይነቶቹ የንግድ እንቅስቃሴዎች በህግ በጥብቅ የተከለከሉ መሆናቸውንና በኢትዮጵያ ህጎች (የሸማቾች ጥበቃም ሆነ የብሔራዊ ባንክ ደንብ) በሚከለክለው መልኩ የቀረበና ስነ ምግባርን የጣሰ መሆኑ ታውቆ እንዲታረም ለማለት እንፈልጋለን።
ምናልባት ይህ ዝግጅት በሌሎች ማኅበራዊ ሚድያዎችና በግለሰቦች የቀረበ ቢሆን ኖሮ ማኅበረሰቡን የማሳሳት አቅሙ (ማህበራዊ ሚድያውን ከመጠራጠር የተነሳ) አነስተኛ ስለሚሆን ይህን የእርምት ፅሑፍ ማውጣት ላያስፈልግ ይችል ነበር ሆኖም ebs የእውነት ግዴታ (Obligation to the Truth) ያለበት ሚድያ በመሆኑ እኛም እንደአንድ ከሙያው ጋር ተያያዥ እንደሆንን ሰዎች እንዲታረም አቅጣጫ መስጠቱ አስፈላጊ ሆኖ ስላገኘነው ነው።
🤔🤔🤔🤔
በዚሁ አጋጣሚ በአሁኑ ወቅት በተለይም በአጭር ጊዜና በትንሽ ወጪ ትልቅ ትርፍና ገቢ የሚገኝበትን መንገድ አለ በሚል የተስፋ ዳቦ እየሰጡ በየማኅበራዊ ሚድያ የሚለቀቁ ማስታወቂያዎች በሚገባ ማጣራትና ተገቢ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳንረሳ ለማሳሰብ እንወዳለን።
💥💥💥