20/10/2019
ኤሪሚያስ ለገሰ በአፋር ክልል ስለተገደሉት 17 ዜጎች የሰጠው አስተያየት:-
=================================
"... 17 ዜጎች በተደራጀ ሃይል ያውም ድንበር ተሻግረው ከውጭ በመጡ ስዎች ጥቃት ሲፈፀምባቸው የሃገር ውስጥ የመንግስት ሚድያዎች ምንም ትኩረት አልሰጡትም:: የመንግስት የሚድያ ተቋማት መከላከያው ሲዋሽ የመከላከያውን ውሸት እያስተጋቡ አፋር ክልል ያለውን ሁኔታ ችላ በማለት እንዳለፉት ነው ያስተዋልነው::በተቃራኒው ግን 17 ዜጎች ሞተው ጠቅላይ ሚንስትሩ ችግኝ ውሃ ሲያጠጡ ነበር ብለው ሲዘግቡ ነበር:: በጣም arrogant የተባሉት Donald Trump እንኳን 17 ዜጎች አይደለም አራት ሶስት ወይም አንድ ዜጋ ላይ ጥቃት ሲፈፀም ስለ ጥቃቱ ወጥቶ ያወራል:: 17 ስዎች ተገደሉ እየተባለ ጠቅላይ ሚንስትሩ ክረምት ላይ የተከሉትን ችግኝ ውሃ አጠጡ የሚል ዜና የሚያስነግር ሃገር ነው ያለን:: የ17 ዜጎች መገደል ተስምቷቸው ፈጥነው በ አደጋው ላይ ሃዘናቸውን መግለጽ ሲገባ ግራ በሚገባ መልኩ አትክልት ውሃ ሲያጠጡ አመሹ::
በአንድ በኩል ለፖለቲካ አላማና ለገፅታ ግንባታ ይጠቅመኛል ብለው ሲያስቡ አንድ የሆነ ግለሰብ ታሟል ብለው ደውለው እግዚአብሔር ይማርህ አሉት ተብሎ ጫጫታ ይፈጠራል:: ወይም ደግሞ አንድ የሆኑ አሮጊት ቤታችው ፈርሶ ሲሰሩ ነው ተብሎ ዶማ ይዘው ሲቆፍሩ ፎቶ ይነሳሉ ቪድዮ ይለጥፋሉ:: 17 ሰው ሞተ ሲባል ጉዳዮ ለፖለቲካና ገፅታ ግንባታ ስለማይጠቅም አጀንዳውን መቅበሪያ ሌላ አጀንዳ ይፈጥራሉ:: አንድ ኢትዮጵያዊት ታመመች ብለህ ከሃገር ውጭ ድረስ ሄደህ እየጠየክ አንድ አሮጊት ቤታቸው ፈረሰባቸው ብለህ እያዘንክ 17 አፋሮች ተገደሉ ሲባል ደግሞ የክረምት ችግኞችን ልንከባከብ ብሎ ትልቅ የውሃ ማጠጫ መኪና ይዞ ፎቶ እየተነሳ ቪድዮ እየለጠፈ ሲያሳይህ ኢትዮጵያ ምን ያህል ያልታደለች ሃገር እንደሆነች ይሰማሃል.."
ኤሪሚያስ ለገሰ
ኢትዮ 360 ሚድያ
ዛሬ ምን አለ
ጥቅምት 5, 2012