01/02/2021
ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ
ቅዱስ ጊዮርጊስ አባቱ እንጦንዮስ እናቱ ትዮብስታ ትባላለች
ሕፃን ሆኖ ሳለ አባቱ አረፈ ሃያ አመትም በሆነው ጊዜ የአባቱን
ሹመት ሊቀበል ወደ ንጉስ ዱድያኖስ በሄደ ጊዜ ህዝቡን ጣዖት
እንዲያመልኩ ሠዎችን ሲያስገድድ አየ፡፡ ሰማዕቱ ቅዱስ
ጊዮርጊስም እጅግ አዘነ የአባቱንም ሹመት ተወ ገንዘብ ሁሉ
ለድሆች መፀወተ ሠማዕትነቱንም በንጉሡ ፊት በመቆም
በእግዚአብሔር ታመነ ንጉሱም እግዚአብሔርን እንዲክድና
ለጣዖት እንዲሰግድ አባበለው ቅዱስ ጊዮርጊስም በእምነቱ
ፀና፡፡ ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሦስት ጊዜ
እንደሚሞት ሦስት ጊዜም እንደሚያስነሳው፡፡ በአራተኛውም
የሰማዕትነት የድል አክሊል እንደሚያቀዳጀው ቃል ገባለት
ሰባት ዓመታትም ስለ ሃይማኖቱ እንደሚሰቃይ ነገረው፡፡ ንጉስ
ዱድያኖስ ቅዱስ ጊዮርጊስን ለመግደል አትናትዮስ የሚባል
ጠንቋይ አስመጥቶ መርዝ በፅዋ እንዲጠጣ ለቅዱስ
ጊዮርጊስ ሠጠው ቅዱስ ጊዮርጊስም ጠጣው ምንም
አልደረሰበትም ጠንቋዩ አትናትዮስም በቅዱስ ጊዮርጊስ
አምላክ አመነ፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም እረፍተ ሞቱ እስኪደርስ
ድረስ ብዙ ተአምራት አደረገ፡፡ ንጉስ ዱድያኖስ እና ሰባው
ነገስታት የተቀመጡባቸውን እንጨት ወንበሮች አለመለመ፡፡
በብረት ምጣድ ውስጥ አበሰሉት አቃጥለው አስረው ረጩት
ይድራስ በተባለ ተራራ አውጥተው በተኑት ጌታችንም ከሞት
አስነሳው ሙታን አስነሳ ብሩክታዊትን ከድራጎን አዳናት
ተጋድሎውን ፈጸመ ሚያዝያ ሰባት ቀን በሠይፍ ራሱን
ቆረጡት ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
የተጋድሎውን ፍፃሜ ሠባት አክሊላትን አጎናፀፈው፡፡
የልዳው ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ አባቶቻችንን በአድዋ
ጦርነት ሃይማኖት እንዳይበረዝ ሀገር
እንዳይወረር ርስታችን ለባዕዳን እንዳይሆን በተጋደሉበት
ዘመን ተራዳኢነቱን ገልፆአል፡፡ የመናገሻ ገነተ ፅጌ ጊዮርጊስ
ታቦት ይዘው ጠላትን ድል አድርገዋል በወቅቱ አቡነ ማቴዎስ
የእመቤታችን ታቦትና የቅዱስ ጊዮርጊስም ታቦታት ይዘው
ዘመቱ የአክሱም ካህናትም የእመቤታችን ሥዕልና ሠንደቅ
አላማ ይዘው ተሠለፉ የፅዮን እምቢልተኞችም በእቴጌ
ጣይቱ ፊት ይነፋ ነበር፡፡ ከለሊቱ 11፡00 ሠዓት ጦርነቱ
ሲጀመር እቴጌ ጣይቱ በማጅራታቸው ድንጋይ ተሸክመው
በጉልበታቸው ተንበርክከው በጋለ ፀሎት ወደ እግዚአብሔር
ይፀልዩ ነበር፡፡ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስም ስራሰላቸው
ለሀገሩ ለሃይማኖቱ የተሠለፈውን አላሳፈረውም የሰለጠነውን
የወራሪ ጦር በሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ተራዳዒነት
አባቶቻችን ድል ነሱ፡፡
በመፀሐፍ ኢያሱ 10፡1-10÷11 ላይ ኢያሱ ታቦተ ጽዮንን
ይዞ የአሞራውያን ነገስታት ድል እንዳደረገ እግዚአብሔርም
አሞራውያንን ለእስራኤላውያን አሳልፎ ሰጣቸው፡፡
አባቶቻችንም ይህን አብነት አድርገው ታቦት ይዘው ለሠልፍ
ወጡ፡፡
እነሱም በእምነት ነገስታትን ድል ነሱ ዕብ 11÷33
የሚበልጠውን ትንሳኤ እንዲያገኙ እስከሞት ድረስ ተደበደቡ
ሌሎችም መዘበቻ በመሆንና በመገረፍ ከዚህም በላይ
በእስራትና በወይኒ ተፈተኑ በድንጋይ ተወግረው ሞቱ ተፈተኑ
በድንጋይ ተወግረው ሞቱ ተፈተኑ በመጋዝ ተሠነጠቁ በሰይፍ
ተገድለው ሞቱ፡፡ ዕብ 11÷36
የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ተራዳኢነት የእመቤታችን
አማላጅነት ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡