08/05/2024
#ሰበር!
በሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ላይ የተወሰ ድርሻቸውን ለሕዝብ የሚሸጡ ስድስት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች መለየታቸውን የኢትዮጵያk ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ (Ethiopian Investment Holdings – EIH) ኃላፊዎች ገለጹ፡፡
በኢትዮጵያ የካፒታል ገበያን መጀመር አስመልክቶ የተወሰኑ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች (State Owned Enterprises) ውስን ድርሻዎቻቸውን በኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ላይ እንደሚሸጡ ሲገለጽ መቆየቱ ይታወሳል፡፡
ድርሻቸው ለሽያጭ የሚቀርበው የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት (አባትሎአድ)፣ የኢትዮጵያ መድኅን ድርጅት፣ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት፣ የትምህርት ማምረቻና ማሠራጫ ድርጅትና የኢትዮጵያ የቱሪስት ንግድ ሥራ ድርጅት ሲሆኑ፣ አምስቱ ተጨማሪ የልማት ድርጅቶች፣ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመሆን ስድስት ድርጅቶች ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ላይ ድርሻቸውን ይሸጣሉ፡፡
Via, Reporter
በሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ላይ የተወሰ ድርሻቸውን ለሕዝብ የሚሸጡ ስድስት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች መለየታቸውን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ (Ethiopian Investment Holdings - EIH) ኃላ.....