Tana times

Tana times Amharic News page

31/08/2021

የጎብኚዎች ስብስብ በሀይቁ መኀል በተንሳፋፊ ነገር የአዞ እርባታ ይጎበኛሉ።
የእርባታው ጌታ "ሀይቁን ዋኝቶ ለወጣ የ10 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት እሰጣለሁ"
ብሎ አምባረቀ። ፀጥታው ሰፈነ።ድንገት ግን አንድ ሰው ወደ ሀይቁ ዘለለ፣ አዞዎችም አሳደዱት፣ ነገር ግን እንደ ዕድል ሳይጎዳ ተረፈ። ባለቤቱ "አሸናፊ ሰው አግኝተናል" ሲል አወጀ።
ሽልማታቸውን ከወሰዱ በኋላ እሱና ሚስትዬው ወደ ክፍላቸው ተመለሱ።

ሰውዬው "ከኋላ ተገፍቼ እንጂ በራሴ አልዘለልኩም" ብሎ ለሚስቱ ነገራት።
ሚስትም ፈገግ፣ ቀዝቀዝ ብላ "እኔ ነበርኩኝኮ" አለችው።Moral of the story: "ከያንዳንዱ ስኬታማ ወንድ ጀርባ፣ ዘወትር በትንሹ ገፋ የምታደርገው ሴት አለች"

ውሃው በግድቡ አናት ላይ መፍሰስ ጀምሯል‼️🗣ዶክተር ኢንጅነር ስለሺ በቀለዛሬ ሐምሌ 12 ቀን 2013 ዓም የሁለተኛውን አመት የህዳሴ ግድብ ሙሌት ተገባዶ ውሃው በግድቡ አናት ላይ መፈሰስ መጀ...
19/07/2021

ውሃው በግድቡ አናት ላይ መፍሰስ ጀምሯል‼️
🗣ዶክተር ኢንጅነር ስለሺ በቀለ

ዛሬ ሐምሌ 12 ቀን 2013 ዓም የሁለተኛውን አመት የህዳሴ ግድብ ሙሌት ተገባዶ ውሃው በግድቡ አናት ላይ መፈሰስ መጀመሩን የውሃ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።
ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጅነር ስለሺ በቀለ በትዊተር ገጻቸው ላይ ÷ ውሃው በግድቡ አናት ላይ መፍሰስ ጀምሯል ብለዋል።

16/07/2021

የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ ኤጀንሲ የሽያጭና የስጦታ ማረጋገጥ አገልግሎትን አቋረጠ‼️

የፌደራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ የማይንቀሳቀስ ንብረትን በተመለከተ ሽያጭና ስጦታን የሚመለከቱ አገልግሎቶችን በጊዜያዊነት አገልግሎት መስጠት ማቋረጡን አስታውቋል፡፡

የፌደራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ የአዲስ አበባ የውክልና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያለውን አሰራር ለማሻሻል እና ዘመናዊ ለማድረግ፣ ተቋሙ ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች መካከል የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን በተመለከተ የሽያጭና ስጦታን አገልግሎት ለተወሰነ ጊዜ ማቋረጡን ተከትሎ አገልግሎቱ የተቋጠበትን ምክንያት በተመለከተ ኢትዮ ኤፍ ኤም የኤጀንሲውን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን አማረን ስለጉዳዩ ጠይቋል፡፡

አቶ ሙሉቀን እንደነገሩን በተቋሙ የሚሰጡ አገልግሎቶችን በጋራ ለማቀናጀትና የዳታ ሲስተሙን በተሻለ መልኩ አንድ ላይ ለማጣመር የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ በመሆኑ አገልግሎቱን ለማቋረጥ እንዳስፈለገ ተናግረዋል፡፡የዳታ ሲስተሙን ለማዘመን የሚረዱ የማሻሻያ ስራዎችን እየተሰሩ መሆናቸውን ያነሱልን አቶ ሙሉቀን በሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ አገልግሎቱን በድጋሚ በተሻለ ፍጥነትና ጥራት ለማስጀመር ጥረት እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡
Tana times

13/07/2021

ሁለተኛው ዙር የኮሮናቫይረስ መከላከያ ክትባት ከነገ ጀምሮ በጤና ተቋማት ይሰጣል‼️

ሁለተኛው ዙር የኮሮናቫይረስ መከላከያ ክትባት ከነገ ጀምሮ በጤና ተቋማት እንደሚሰጥ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ገለጹ።

በአዲስ አበባ የመጀመሪያውን የኮቪድ ክትባት ከወሰዱ ሶስት ወር የሞላቸው ዜጎች ከነገ ጀምሮ እንደሚከተቡ እና በክልሎች ደግሞ ክትባቱን ከሐምሌ 9 ጀምሮ መውሰድ እንደሚቻል ሚኒስትሯ ተናግረዋል።

ክትባቱን ተደራሽ ለማድረግ መንግሥት ከአጋር አካላት ጋር እየሰራ ነው ያሉት ዶ/ር ሊያ 400 ሺህ የአስትራዜኒካ ክትባት ለሁሉም ክልሎች እየተሰራጨ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በቀጣይም 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን ክትባት ወደ ሀገር ውስጥ እንደሚገባ የጠቀሱት ሚኒስትሯ የትራንስፖርት ዘርፍ ሰራተኞች፣ ፖሊሶች፣ መምህራን፣ የባንክና የፍርድ ቤት ሰራተኞች፣ ተጓዳኝ የጤና ችግር ያለባቸው እና በእድሜ የገፉ ዜጎች እንዲሁም የመገናኛ ብዙኃን ሰራተኞች የመጀመሪያውን ዙር ክትባት እንዲወስዱ ሚኒስትሯ ጥሪ አቅርበዋል።

አዲሱ የኮቪድ ዝርያ ዴልታ በኢትዮጵያ ስለመከሰቱ ጥናት እየተደረገ እንዳለም ዶ/ር ሊያ በመግለጫቸው አንስተዋል።

እስካሁን ከ277 ሺህ በላይ ዜጎች ኮቪድ-19 ኮሮናቫይረስ የተገኘባቸው ሲሆን 4343 በኮቪድ-19 ለሞት ተዳርገዋል።

Tana times

13/07/2021

የ2013 የ12ኛ ክፍል ፈተና ጥቅምት አጋማሽ ይሰጣል‼️

የ2013 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሚቀጥለው ዓመት ጥቅምት ወር ይሰጣል።

ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ የ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከጥቅምት 2014 ዓ.ም አጋማሽ በኋላ እንደሚሰጥ ገልጿል።

በዘንድሮው የትምህርት ዘመን የትግራይ ክልል ተማሪዎችን ሳይጨምር 620 ሺህ ተማሪዎች ተመዝግበው ፈተናውን በመጠባበቅ ላይ ናቸው ተብሏል።

የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዲላሞ ኦቶሬ በሰጡት መግለጫ ኤጀንሲው በማንኛውም ሰዓት ፈተናውን መስጠት የሚያስችል ዝግጅት አድርጓል።

በሀገሪቱ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች የኢኮኖሚክስ ትምህርት ባለመሰጠቱ ፈተናው የማይሰጥ መሆኑን ገልፀዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

Tana times

የበቀለ ልጆች
13/07/2021

የበቀለ ልጆች

12/07/2021

የመተከል ዞን የተቀናጀው ግብረ ኃይል ኮማንድ ፖስት አመራሮች እና የየመስተዳድር አካላት የተካተቱበት ልዑክ ተፈናቃዮች በሚገኙበት አራት የጊዜያዊ የመጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ተፈናቃዮችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

በአካባቢው ተከስቶ በነበረው ግጭት ሳቢያ ከቀዬአቸው ተፈናቅለው ከነበሩ ወገኖች ጋር የጋራ ውይይት ማድረጋቸውም ተገልጿል። ውይይቱ በግዜያዊ መጠለያ ጣቢያው የሚያጋጥሙ ችግሮች እና መፍትሄዎች ላይ አተኩሮ የተካሄደ ነበር።

የመተከል ዞን የተቀናጀው ግብረ ኃይል ኮማንድ ፖስት አባል የሆኑት ብ/ል ጄኔራል አለማየሁ ወልዴ ተፈናቃዮችን ቋሚ ተፈናቃይ አድርጎ በማቆየት በግላቸው የሚጠቀሙ ሀይሎች መኖራቸውን የጠቆሙ ሲሆን የእነዚህን ሀይሎች ሴራ መረዳትና በጋራ መታገል አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።

ለህዝቡ የሚቀርበውን የምግብ እህሎችን ሸጠው ለግል ጥቅማቸው ለማዋል ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ግለሰቦችን በህዝቡ ተሳትፎ በመለየት ለህግ እንዲቀርቡ መደረጉንም አስታውሰዋል። ይሄ ተግባር በቀጣይነት ተጠናክሮ መቀጠል ይገባዋል ብለዋል።

ይሁን እንጂ ልዩ ልዩ የመመገቢያ ቁሳቆሶች እና ሰብአዊ እርዳታዎች መድረስ ከሚገባው ግዜ መዘግየቶች ማጋጠማቸውን የጠቆሙ ሲሆን አስቸኳይ መፍትሄ ሊሰጣቸው እንደሚገባ አሳስበዋል።



"የግድቡ ጉዳይ ምንም አይነት ወታደራዊ መፍትሄ የለውም" - አሜሪካ

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የቀጠናዊ ጉዳዮች ቃል አቀባይ ሳሙኤል ዋርበርግ፤ ትላንት እሁድ በሰጡት ቃል አሜሪካ ለታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴው ግድብ ጉዳይ ብቸኛው መፍትሄ ዲፕሎማሲ ነው ብላ ታምናለች ብለዋል።

ከTeN የሳተላይት ቻናል ቃለምልልስ የነበራቸው ዋርበርግ ፥ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ፀጥታው ምክር ቤት ስብሰባ የህዳሴው ግድብ ጉዳይ ለአፍሪካ አህጉር እጅግ በጣም አስፈላጊ መሆኑን አሳይቷል ሲሉ ተናግረዋል።

አክለውም ዓላም አቀፉ ማህበረሰብ የህዳሴው ግድይ ጉዳይ ለናልይ ተፋሰስ ቀጠና ምን ያህል ጠቃሚ እንደሆነ ተገንዝቧል ብለዋል።

ዋርበርግ፥ የግድቡ ጉዳይ ምንም አይነት ወታደራዊ መፍትሄ እንደሌለው በማንሳት "በአፍሪካ አህጉር ምንም አዲስ ጦርነት ልንገምት አንችልም" ብለዋል።

የተፋሰሱ አገራት እና የ ድርድርን እንደገና መጀመር እንዳለባቸው ጠቁመው አሜሪካ ማንኛውንም የፖለቲካ ወይም የቴክኒክ ድጋፍ ለመስጠት ዝግጁ መሆኗን ገልፀዋል።

ዋርበርግ፥ "ውይይቱን ለመቀጠል አሜሪካ ሁሉም ወገኖች ከማንኛውም መግለጫ እንዲታቀቡ ጥሪ ታደርጋለች ፤ የሚደረገው ማንኛውም ውይይት ድርድሮችን ወደፊት ለማስቀጠል ያለመ መሆን ይገባዋል" ብለዋል።

አሜሪካ ድርድሩ ላይ የበለጠ ጊዜ እንዲያልፍ አትፈልግም ብለዋል።

Tana times

"የግድቡ ጉዳይ ምንም አይነት ወታደራዊ መፍትሄ የለውም" - አሜሪካ

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የቀጠናዊ ጉዳዮች ቃል አቀባይ ሳሙኤል ዋርበርግ፤ ትላንት እሁድ በሰጡት ቃል አሜሪካ ለታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴው ግድብ ጉዳይ ብቸኛው መፍትሄ ዲፕሎማሲ ነው ብላ ታምናለች ብለዋል።

ከTeN የሳተላይት ቻናል ቃለምልልስ የነበራቸው ዋርበርግ ፥ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ፀጥታው ምክር ቤት ስብሰባ የህዳሴው ግድብ ጉዳይ ለአፍሪካ አህጉር እጅግ በጣም አስፈላጊ መሆኑን አሳይቷል ሲሉ ተናግረዋል።

አክለውም ዓላም አቀፉ ማህበረሰብ የህዳሴው ግድይ ጉዳይ ለናልይ ተፋሰስ ቀጠና ምን ያህል ጠቃሚ እንደሆነ ተገንዝቧል ብለዋል።

ዋርበርግ፥ የግድቡ ጉዳይ ምንም አይነት ወታደራዊ መፍትሄ እንደሌለው በማንሳት "በአፍሪካ አህጉር ምንም አዲስ ጦርነት ልንገምት አንችልም" ብለዋል

12/07/2021

በአማራ ክልል ሰንደቅ ዓላማ ማሻሻያ ላይ ህዝባዊ ምክክር ሊካሄድ ነው‼️

በአማራ ክልል አሁን በሥራ ላይ ያለው ሰንደቅ ዓላማ እንዲሻሻል በክልሉ ም/ቤት ከ4 ወራት በፊት ውሳኔ መተላለፉን ተከትሎ በአማራ ክልል ርዕሰ-መስተዳደር አገኘሁ ተሻገር ተሰይሞ ወደ ስራ ገባው የባለሞያዎች ቡድን ሲያካሂድ የቆየውን ጥናት አጠናቋል ተብሏል፡፡

ይህ በመሆኑም፣አጥኚ ቡድኑ በክልሉ ስራ ላይ ሊውሉ በሚችሉ የሰንደቅ ዓላማ አማራጮች ዙሪያ የህዝብ አስተያየት ለማሰባሰብ፣የሀይማኖት መሪዎች፣የከሀገር ሽማግሌዎች፣ተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች፣ምሁራን፣የክልሉ የመንግስት አመራሮች እና የሲቪል ማህበራት ተወካዮችን ጋብዞ ነገ ሀምሌ 6 ቀን 2013 ዓ.ም በባህር-ዳር ከተማ በሚገኘው የክልሉ ምክር ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ከጠዋቱ 3 ሰዓት ውይይት ለማካሄድ ቀጠሮ ይዟል፡፡

ከዚሁ ጎን ለጎን፣በዕለቱ በቦታው ተገኝተው የምክክሩ ተካፋይ መሆን የማይችሉ የክልሉ ነዋሪዎች እና ተወላጆች በማህበራዊ ትስስር ገፆች ሀሳብ አስተያየታቸውን እንዲያዋጡ ጥሪ መተላለፉን ብስራት ሬዲዮ ከአማራ ክልላዊ ም/ቤት ባገኘው መረጃ ተመልክቷል፡፡

የአማራ ክልላዊ መንግስት ከ4 ወራት በፊት በመጋቢት 6 ቀን 2013 ዓ.ም ባካሄደው 17ኛ መደበኛ ጉባዔው፣የክልሉን ህዝቡ እና መንግስት አይወክልም በሚል አሁን በስራ ላይ ያለው ሰንደቅ ዓላማ እንዲሻሻል ለቀረበው የውሳኔ-ሀሳብ በጎ ምላሽ በመስጠት የሰንደቅ ዓላማው ማሻሻያ በስድስት ወራት ውስጥ ተጠንቶ እንዲቀርብለት መወሰኑ የሚታወስ ነው፡፡
Tana times

12/07/2021

የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት፣ የምርምር ፣የቴክኖሎጂና ኢንዱስትሪ ትስስር ኮንቬንሽን አስጀመረ።

"ወደ እውቀት መር ኢኮኖሚ" የሳይንሳዊ ጥናት ውጤቶችን የማስተዋወቅ፣ ተግባራዊ እንዲሆኑ የማመቻቸት፣ በትምህርት ተቋማት መካከል በምርምርና ቴክኖሎጂ ልማት ትስስር የመፍጠር ዓላማ ያለው ነው ተብሏል። ኮንቬንሽኑ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሐምሌ 08/2013 ዓ.ም ድረስ ይቆያል።

ኮንቬንሽኑ ዓመታዊ ኾኖ የሚቀጥልና ውድድርና ሽልማቶች የሚኖሩት መርኃግብር ነው። የምርምርና ቴክኖሎጂ ተቋማት ፣ የመንግሥትና የግል ዩኒቨርስቲዎች ፣ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች ፣ሳይንቲስቶች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የቴክኖሎጂ ፈጣሪዎች፣ ባለሀብቶቾ፣ ፖሊሲ አውጪዎችና ሌሎችም ባለድርሻዎች እየተሳተፉበት ነው።

በማስጀመሪያ መድረኩ ላይ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶክተር ሳሙኤል ኡርቃቶ የሀገሪቱን የሳይንስና ምርምርና ግኝቶችን ማበረታት ለዘመኑ አዋጭ የሆኑ እሳቤዎችን ለመተግበርና በጥበብ የሚመራ ኢኮኖሚ ለመገንባት ያስችላል ብለዋል።

ጥራት ያለው የክህሎት ስልጠናዎችን በበቂ ደረጃ ማረጋገጥ አለብን ነው ያሉት። የተቋማት ትብብርም ያልዘመነና ያልተሠራበት በመሆኑ እንደዚህ አይነት ዝግጅቶች የጎላ ድርሻ እንደሚኖራቸው አንስተዋል።

ሳይንሳዊና ሀገር በቀል እውቀቶችን አቀናጅቶ ለመጠቀም የሚያስችል ሥርዓት ለመገንባት እንደሚሠራም ገልጸዋል።

የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በበኩላቸው የዚህ አይነት ኮንቬንሽን ኢትዮጵያ በዘርፉ የምትፈልገውን የሰለጠነ የሰው ሀብት ማግኘት የሚያስችል፣ የቴክኖሎጂ ፈጣሪዎችን የሚያበረታታ ፣ ሀገር በቀል እውቀቶችን አዘምኖ ለመጠቀምና ምርምርና ግኝቶችን ለተቋማትና ለፖሊሲ አውጪዎች ማድረስ የሚያስችል ነው ብለዋል።

በሀገሪቱ የአስር ዓመት የልማት መሪ እቅድ ውስጥ የተያዘውን የኢንዱስትሪና በእውቀት ላይ የተመሰረተ ማኅበራዊ እድገት ለማሳካት አጋዥ ይሆናል። ሳይንስ ተኮር በመሆን ግንዛቤው ያደገ ዜጋ ማፍራት ይገባናል፤
ለትምህርት፣ ለኢንዱስትሪ ፣ለቴክኖሎጂና ለምርምር ትስስር መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ይሠራል ነው ያሉት።

የማኅበረሰቡን የሳይንስ ባህል ለማሳደግ ተቋማት ተናበው እንዲሠሩ ማድረግ ይገባል፤ የትምህርት ሥርዓታችን ፈላጊና ተፈላጊን የሚያገናኝ እንዲሆን መሥራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

Tana times

12/07/2021

በህንድ ሰልፊ ሲነሱ የነበሩ 11 ሰዎች በመብረቅ የተነሳ ህይወታቸውን አጡ

በህንድ ሰሜናዊ ከተማ ጃፑር ከተማ በትላንትናው እለት ሰልፊ ሲነሱ የነበሩ 11 ሰዎች በመብረቅ የተነሳ ህይወታቸውን አጥተዋል።አደጋው ያጋጠመው በ12ኛው ክፍለ ዘመን በታነፀው አሜር ፎርት በተሰኘው ማማ ላይ የደረሰ ነው።

መብረቁ ሲወድቅ በጊዜው 27 ሰዎች በማማው ላይ የነበሩ ሲሆን አንዳንዶቹ ከማማው በመዝለል ህይወታቸውን ለማትረፍ ሞክረዋል።ከ2004 አንስቶ በመብረቅ 2000 ህንዳውያን ህይወታቸውን አጥትዋል።

ህይወታቸውን ላጡ ሰዎች ቤተሰብ 500ሺ ሩፒ ካሳ እንደሚከፈል መንግስት አስታውቋል።በህንድ ከወርሃ ሰኔ እስከ መስከረም ከባድ ዝናብ የሚያጋጥምበት የክረምት ወቅት ነው።

10/07/2021

ባንግላዴሽ ዉስጥ ቢያንስ 52 ሰዎች ከሞቱበት የእሳት አደጋ ጋር በተያያዘ ፖሊስ ስምንት ሰዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ዛሬ አስታወቀ

ፖሊስ ለለአሶሺየትድ ፕሬስ እንደገለጸው ቃጠሎ የደረሰበት « ሳጄብ ግሩፕ» የተባለው ፋብሪካ ባለቤት እና ስራ አስኪያጅን ጨምሮ ስምንት ተጠርጣሪዎች «በግድያ ወንጀል» በቁጥጥር ስር ውለዋል። እንደ ፖሊስ ገለፃ የእሳት አደጋው ሲደርስ ሰራተኞቹ ፋብሪካው ውስጥ ከውጭ በር ተቆልፎባቸው ይገኙ ነበር።

ባለ አምስት ፎቅ ያለው የመጠጥ እና የምግብ ማምረቻ ፋብሪካ ላይ ሀሙስ ሌሊት ቃጠሎው ሲደርስ ከሕንጻው ላይ የዘለሉ ከ 30 የሚበልጡ ሰዎች ጉዳት እንደደረሰባቸዉም ፖሊስ ዘግቦአል። በቃጠሎው የሞቱትን አስክሬን ለመለየት ስላስቸገረ የ 33 ሰዎች DNA ( ዘረ መል) እንደተወሰደ ተዘግቧል።ፋብሪካው ምርቶቹን ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ፤ ማሌዢያ፣ ህንድ፣ የመካከለኛው ምስራቅ እና የአፍሪቃ ሀገራት ይልክ እንደነበርም ተዘግቧል።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tana times posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share