አቮላ

አቮላ Adet

05/08/2025

‹‹…በጎጃም መሬት በጣና ደሴት ዳጋ ከሚባል አገር ገቡ፡፡››
‎-------------------------------------

‎አለቃ ተክሌ ታዋቂ ሠዓሊና ቀራጺ ሲሆኑ ከዚህ በሻገር በታሪክ ጸሐፊነታቸውም ይታወቃሉ፡፡የታሪክ ጽሑፎቻቸው እነ ተክለ ጻዲቅ መኩሪያው፣ብላቴን ጌታ ማህተመ ስላሴ፣አለማየሁ ሞገስ፣ሮጀር ካውሊና ሌሎች ጸሐፍት ላሳተሟቸው የታሪክና የስነ ጽሑፍ ስራዎች በምንጭነት አገልግለዋል፡፡አለቃ ተክሌ ሁለት መጽሐፎችን ለትውልድ አበርክተው አልፈዋል፡፡የመጀመሪያው ስራቸው‹‹የጎጃም ትውልድ በሙሉ፣ከአባይ እስከ አባይ›የሚል ርዕስ ያለው ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ‹‹የጎጃም ታሪከ ነገስት››በመባል የሚታወቀው በኋላ በዶክተር ስርግው ገላው አማካኝነት ሀተታ ተሰርቶለት‹‹የኢትዮጵያ ታሪክ›› በሚል ርዕስ ለህትመት የበቃ ስራቸው ነው፡፡
‎የመጀመሪያ የጽሑፍ ስራቸው የሆነው‹‹የጎጃም ትውልድ በሙሉ፣ከአባይ እስከ አባይ››የተሰኘው መጽሐፋቸው 11(አስራ አንድ) ዓመታትን የፈጀ ጥናትና ምርምር ተደርጎበት በ1889 የተጠናቀቀ የጎጃምን ትውልድ የሚያትት ስራ ነው፡፡አለቃ ተክሌ መጽሐፉን ሲያዘጋጁ በዘመናቸው የነበሩ ታሪክ አዋቂ ሽማግሌዎችንና በየገዳማቱ የሚገኙ ጥንታዊ መጽሐፍትን በመረጃ ምንጭነት ተጠቅመዋል፡፡ይህ ስራቸው በግርማ ጌታሁን ተዘጋጅቶ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬስ አማካኝነት በ2003 ዓ.ም ለህትመት በቅቷል፡፡
‎አለቃ ተክሌ የጎጃምን የግዛት ወሰን አስመልክቶ በዝርዝርና በሰፊው በሁለቱም ስራዎቻቸው የገለጹ ሲሆን ለዛሬ ‹‹የጎጃም ትውልድ በሙሉ፣ከአባይ እስከ አባይ››በሚለው መጽሐፋቸው የጎጃም ንብረት ስለሆነው ጣና ሀይቅ ያሰፈሩትን ላካፍላችሁ፡፡አለቃ ተክሌ ከታች ያሰፈርኩላችሁን ቅንጫቢ ታሪክ የጻፉት የጎጃምን ደግነት ለማሳየት ቢሆንም ቅንጫቢው የጣና ሀይቅ ፣ በአጼ ዘርዓ ያቆብ ጊዜም(1434–1468) ሆነ ከዚያ በፊት የየትኛ ግዛት አካል እንደነበር የሚያሳይ ነው፡፡
‎‹‹…….አጼ ዘርዓ ያቆብ ከሞቱ በኋላ አጽማቸው በዋሻ ተቀምጦ ሳለ እንደ ቀዳሚ ሰማዕት እስጢፋኖስ ዳ እያለ ይናገር ነበር፡፡ዳ እያለ መናገሩ በየቀኑ ቢያስቸግር እግዚአብሄር የሚያርፉበትን ቦታ ቢያመለክተን ሲሉ አሽከሮቻቸው አጽማቸውን በሳጥን ይዘው አገር ላገር ይዞሩ ጀመር፡፡ወህኒ በሚባለው አገር ሰባት አመት ከተቀመጡ በኋላ ግን ጊዜው ሲደርስ እግዚአብሄር አመለከታቸውና በጎጃም መሬት በጣና ደሴት ዳጋ ከሚባል አገር ገቡ፡፡ከዚያ ቦታ አጽማቸው ሲደርስ ዛቲ ይእቲ ምዕራፍየ ለአለም(ማረፊያ ስፍራየ ይቺ ናት)ብለው ተናገሩ፡፡ከዚህ በኋላ አሽከሮቻቸው ደጉ ቦታ ይህ ነው ሲሉ ዳጋ እስጢፋኖስ አኖሯቸው፡፡የጎጃምን ደግነት እንኳንና በህይወት ያሉት ነገሥታት፣የሞቱትም እንዲህ ይመሰክራሉ፡፡›› ገጽ 34-35

‎በዚህ ቅንጫቢ ታሪክ ሶስት ዘመናትን እናገኛለን፡-
‎1.የመጽሐፉ ጥናት ከተጀመረበት 1878 እስከ ተጠናቀቀበት 1889 ያለውን(የዛሬ
‎ 133 ዓመት)
‎2.የአጼ ዘርዓ ያቆብ ዘመንን(1434–1468) ና
‎3.ከአጼ ዘርዓ ያዕቆብ በፊት የነበረውን
‎የአጼ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ቀጥታ በታሪኩ ሲገለጽ፣ መጽሀፉ የተጻፈበትና ከአጼ ዘርዓ ያዕቆብ በፊት የነበረው ዘመን ደግሞ በጸሐፊው አዘጋገብ ተገልጽዋል፡፡በነዚህ የታሪክ ዘመናት ሁሉ ጣና ሀይቅ የጎጃም ግዛት አካልና ንብረት እንደሆነም ጽሑፉ ላይ በማያወላዳ መልኩ ሰፍሮ ይገኛል፡፡‹‹....በጎጃም መሬት በጣና ደሴት ዳጋ ከሚባል አገር ገቡ፡፡››

24/09/2024

ድንጋይን እንደኩበት የሚያንሳፍፈውን ታምረኛ ሀይቅ ይጎብኙ!
🇪🇹
የጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሚገኙ 17 የገጠር ወረዳዎች ውስጥ አንዱ ሲኾን ይህ ወረዳ 40 ቀበሌዎችን አቅፎ ይዟል፡፡

ወረዳው የባህረ-ጊዮርጊስ ሐይቅን ጨምሮ በተፈጥሮ መስህቦች ዝርዝር ውስጥ ሰፍረው የሚገኙ በርካታ ሀብቶች አሉት፡፡ ከእነዚህ የመስህብ ሃብቶች መካከልም ጎንቻ ሲነሳ ስሙ ሳይጠቀስ የማይታለፈውን ታምረኛው የባህረ-ጊዮርጊስ ሐይቅን እናስተዋውቃችሁ፡፡

ባህረ-ጊዮርጊስ ሐይቅ የጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ ዋና ከተማ ከሆነችው ግንደወይን 12 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ሀይቅ ሲኾን ይህ ሃይቅ “አርብ ገበያ” በተባች የገጠር ከተማ አቅራቢያ ሶስት ቀበሌዎችን አዋስኖ የሚገኝ ሀይቅ ነው፡፡ የቡችር የወያ፣ እነሴ ቆል፣ እና ጌቴሰማኒ ዋፋ የሚባሉትን ቀበሌዎች የሚያዋስነው ይህ ሀይቅ ያለበት ቦታ ከባህር ጠለል በላይ 2ሺህ 611 ሜትር የሚደርስ ከፍታ አለው፡፡

ባህረ-ጊዮርጊስ ሐይቅ 112 ሄክታር ስፋት ሲኖረው በዚህ ስፋቱ ከጣና ሀይቅ፣ ከሀይቅ ስጢፋኖስ እና ከአርዲቦ ሐይቅ ቀጥሎ በክልላችን ከሚገኙት ሀይቆች መካከል በ4ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ ይህ ሀይቅ በስፋቱ ብቻ ሳይኾን በጥልቀቱም ተጠቃሽ ሐይቅ ነው፡፡ ሀይቁ በዳር አካባቢ 5 ሜትር ጥልቀት ያለው ሲኾን ወደመሀል 30 ሜትር ከፍ ይላል፡፡

ይህ ሀይቅ በሌሎች አካባቢዎች ከሚገኙ ሀይቆች ለየት የሚያደርገው የተንቀሳቃሽ ደሴቶች ባለቤት መኾኑ ሲኾን እነዚህ ደሴቶች “መቃ” በተባለ የሳር አይነት የተሞሉ ናቸው፡፡ ደሴቶቹ ወይም መቃዎች በተለያየ አቅጣጫ ተንቀሳቃሾች ናቸው፡፡ ሲያሰኛቸው ተሰባስበው በሃይቁ መካከል ይከማቻሉ፤ ሲያሻቸው ኅብረታቸውን አፍርሰው በተለያየ አቅጣጫ ወደ ሀይቁ ጠረፍ ጉዞ ይጀምራሉ፡፡

የመቃዎች እንቅስቃሴ በአካባቢው ኅብረተሰብ ዘንድ የራሱ የኾነ ትርጓሜ ያለው ሲኾን፤ ተንቀሳቃሽ መቃዎች በአንድ አካባቢ ተሰባስበው ቆይተው ሲበተኑ ጦርነት ይኾናል የሚል ትርጉም አለው፡፡ የመቃዎች ቅጠል ወደ ውስጥ፤ ስራቸው ደግሞ በተቃራኒው ወደ ላይ ኾነው በሚገለበጡበት ወቅት የመንግሥት ለውጥ እንደሚከሰት ይነገራል፡፡ ሌላው እና የሚያስገርመው የዚህ ሃይቅ መገለጫ ደግሞ የአባይና ጣናን አይነት ግንኙነት፤ አባይ ጣናን ጋልቦ ሲያልፍ የሚታየውን አይነት ትዕይንት “ሽገዝ” የተባለው ወንዝ ከባህረ-ጊዮርጊስ ሀይቅ በስተ ምስራቅ አቅጣጫ ይመጣና ይዞት የሚመጣውን የውሃ መልክ ሳይቀይር፣ መጠኑን ሳይቀንስና ሳይጨምር ባህረ-ጊዮርጊስ ሃይቅን “ቼ... ፈረሴ” ብሎ ደብሎበት ሲያልፍ ማየት የተዘወተረ ትዕይንት ነው፡፡

ከዚህ ሌላ በባህረ-ጊዮርጊስ ሀይቅ አካባቢ አንድ አስጋራሚና “ምን ታዕምር ነው” የሚያስብል ነገር ይከሰታል፡፡ በሃይቁ ዳር ለዳር ከሚገኝ አንድ ድንጋይ አንስቶ ወደ ሃይቁ ቢወረውሩ ድንጋዩ ልክ እንደ ኩበት ሁሉ ትንሽም ይሁን ትልቅ በውሀው ላይ ይንሳፈፋል፡፡ ያኔ….ድንጋይ ወይስ ኩበት የወረወርኩት በማለት እራስን መጠየቅ አይቀርም ፡፡ ይህ ተንሳፋፊ ድንጋይ በአካባቢው ኅብረተሰብ ዘንድ “ሰረዝ” በመባል ይታወቃል፡፡ ይህን ድንጋይ ቢለዋ፣ መጥረቢያ እና የመሳሰሉ ብረት ነክ ነገሮችን ለመሳል ይጠቀሙበታል፡፡ በሃይቁ ውስጥ የተለያዩ በመጠናቸው አነስተኛ የኾኑ በየብስና በውኃ ውስጥ የሚኖሩ እንስሳት እንደሚገኙ የአካባቢው ሰዎች ሲናገሩ ይሰማል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ዝቅተኛ ይሁን እንጅ የአሳ ምርት ምልክቶችም ይታያሉ፡፡

በባህረ-ጊዮርጊስ ሃይቅ አካባቢ የተለያዩ የእፅዋት ዓይነቶች የሚገኙ ሲኾን በእነዚህ እፅዋቶች በተሸፈነው ዳገት ስር ሶስት ዋሻዎች ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ዋሻዎች ቁጥር1፣

24/09/2024

አውራ - አውራ ሸተተን - የጥንት የጎጃም ሰዎች ቅኔ

የጎጃሙ ልዑል ንጉሥ ተክለሃይማኖት ጥር 3 ቀን 1893 ዓ/ም ደብረ ወርቅ ማርያም ለጸበል በኼዱበት አረፉና ደብረ ማርቆስ ከተማ፣ ከቅዱስ ማርቆስ ቤተክርስቲያን በደማቅ ሥነ ሥርዓት ተቀበሩ።

ከንጉሥ ኀልፈት በፊት ጎጃም ግዛቱ ሰፊ ነበር፥የአሁኑ ወለጋ እና ከፋ የግዛቱ አካል ነበር። የንጉሡ ሙት ዓመት እንዳለፈ አጤ ምኒልክ የጎጃም ግዛት የኾነውን ዳሞትን እና አገው ምድርን ለራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከም፣ የቀረውን የጎጃም ክፍል ( ዛሬ ምሥራቅ ጎጃም ተብሎ የታጠረውን)ለደጃዝማች ሥዩም ( በኋላ ራስ ኃይሉ) እና በጎጃም ሥር ይተዳደር የነበረውን ወለጋ ወለጋን ለደጃች ደምስ ሰጡት።

ደጃዝማች ሥዩም ጎጃምን በሙሉ ጠቅልለው ለመግዛት ካላቸው የጸና ፍላጎት የተነሳ ከራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከም ጋር ገጠሙ። ይኼ በአጤ ምኒልክ ዘንድ አልተወደድም እና ክስ ቀርቦባቸው ደጃዝማች ሥዩም ሸዋ ውስጥ፣ አፍቀራ ኮረብታ ላይ ታሰሩ። ከአጤ ምኒልክ የደጃዝማች ሥምን ወንድም፣ የንጉሥ ተክለሃይማኖት ልጅ የኾኑትን ራስ በዛብህን በወንድማቸው ግዛት መደቧቸው።ይኼ ብቻ አልበቃም። አጤው የፖለቲካ ጋብቻን እንደ ነገር ማርገቢያ ሊጠቀሙ ፈለጉና የልጅ ልጃቸውን ወይዘሮ ዘነብወርቅ ሚካኤልን ለራስ በዛብህ ዳሩላቸው። ወይዘሮ ዘነብወርቅ እንደ ስማቸው ውብ ቆንጆ ናቸው ይባላል።

ራስ በዛብህ ሲፈልጉት የነበረውን የአባታቸውን ግዛት ብቻ ሳይኾን የወርቅ ፍልቃቂ የመሰለች ደርባባ ሴት ስላገኙ ደስታቸው ወደር አልባ ኾነ። ሚስታቸው እና የግል ጠባቂዎቻቸውን ይዘው የግዮን ወንዝን ተሻግረው ጎጃም፣ ደብረ ማርቆስ ገቡ። ከትቂት ጊዜያት በኋላ ራስ በዛብህ ልባቸው ሸፈተ። ወንድማቸው ደጃዝማች ሥዩም እንዳሰቡት ሁሉ እሳቸውም ራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከምን አስወግደው ሙሉውን ጎጃም በብቸኝነት ማስተዳደር ፈለጉ። ይኼ ሴራ በማስረጃ ተረጋግጦ ወንድማቸው ካለበት አፍቀራ ኮረብታ ታሰሩ።

በዚኽ ጊዜ ግራዝማች ወልደ ዮሐንስ የተባሉ የሸዋ ( ይፋት) ተወላጅ ጎጃምን በወንበርነት እንዲያስተዳድሩ ከአዲስ አበባ ወደ ጎጃም ምድር ተላኩ። ጎጃሞች ተቆጡ፣ ቁጣቸውን በውስጣቸው ይዘው ትቂት ቀናት ነጎዱ። የጎጃም ዝምታ አስፈሪ ነው። አጤ ምኒልክ የእናታቸውን አገር ሰው ባህርይ በደንብ ያውቁታልና ለዘመዶቻቸው ( ለጎጃሞች)
"የግራዝማች ወልደዮሐንስ አገዛዝ እየተመቻችሁ ነውን?ችግር አለባችሁ? አገዛዙ ተመችቷችኋል ወይ?" ብለው ደብዳቤ ላኩ።

ጎጃሞች በዚኽ ጊዜ "ጉዳትስ የለብንም፣ግን አውራ- አውራ ሸተተን" ብለው መለሱ። አውራ - አውራ ሸተተን ቅኔያዊ ንግግር ነው። ጎጃሞች አውራ - አውራ ሸተተን ሲሉ በራሳችን ጀግኖች እንመራ፣ ጎጃሞች ይምሩን፣ ጎጃም ለጎጃም አያንስም" ማለታቸው ነው። አጤው ብልጥ ናቸው፣ አማካሪያቸዉ እቴጌ ጣይቱም ቢኾኑ የዋዛ አይደሉም።

በአጤ ምኒልክ ዙፋን አስቸኳይ ምክክር ተካኼደ። ለጎጃሞች የሚፈልጉትን፣ የራሳቸውን አውራ ይላክላቸው የሚል ውሳኔ ላይ ተደረሰ። ደጃዝማች ሥዩም ከአፍቃራ ኮረብታ ፈትተው ወደ ጎጃም እንዲመለሱ ተደረጉ።

ጣይቱ ደጃዝማች ሥዩምን ወደ አዲስ አበባ አስጠርተው አብራቸው የምትኖረውን ዘመዳቸው ወይዘሮ አሰለፈችን አጋብተው " ከቀደምት አባቶችህ የሚመጥንህም ሥም ምረጥና እንስጥህ" ብለው ጠየቋቸው። ደጃዝማች ሥዩም ኃይሉ መባል እንደሚፈልጉ ተናገሩ። ኃይሉ የሚለውን ሥም የፈለጉበት ምክንያት የታላቁን ራስ ኃይሉ ዮሴዴቅ ሥም ማውሳት ስ

24/09/2024

ኮስትር በአንድ ወቅት፣

ጸሐይ ወደ ምድቧ ለመግባት የምዕራብን አቅጣጫ ይዛ ትጣደፋለች። ወይዘሮ ሸክሚቱ ለአርበኛች ስንቅ በመሰነቅ ተጠምዳለች። አባ ኮስትር ለግዳጅ ዝግጁ የኾኑ አርበኞችን ሰብስቦ “ሞት ለማንም የማይቀር ጽዋ ነው። ሥም ያለው፣ ታሪክ የሚያወሳው ሞት መሞት ኀያውነት ነው። የጀግና ሞት እንጅ የወራዳ ሞት እንዳትሞቱ እወቁበት። ድል ማድረግን እንጅ እሞታለኹ ማለትን በልቡናችኹ አታሳድሩ። የዲማው ጅዎርጂስ ይከተላችኹ” የሚል ትዕዛዝ ሰጥቶ ለሌላ ተግባር ዘወር ሲል አንድ የበላይ ጠባቂ "ጌቶች!" ሲል በጥድፊያ ተጣርቶ ከእጅጉ ዘንዳ መልክተኛ እንደመጣ ተናገረ።

በላይ ዘለቀ ኮስተር ባለ ድምጽ " ምነው፥ እነ እጅጉ ደኽና እማይደሉ?"ሲል ጠየቀ። መልዕክተኛው ሰላምታ ከሰጠ በኋላ " የጣሊያን ጦር በደጀን በኩል ወደ ጎጃም እንዳይሻገር በቃፊርነት ከቆሙት መካከል ሁለቱ ለጠላት ገብረው ጠላትን ወደ ጎጃም አሻግረውታል፥ ጌታዬ" አለ ንዴት እና እልህ በተቀላቀለበት ድምጸት።

"ይቺን ይወዳል የዘለቀ ልጅ፥ በየት በኩል ነው የተሰለፉት?" የበላይ ጥያቄ ነበር። በውሻ ጥርስ በኩል እንደኾነ እና ኃይሉ ብዛት እንደሌላቸው ተናገረ መልዕክተኛው። በላይ ትዕዛዝ ሰጠ፥ " በሉ ገስግሳችሁ ኺዱ፥ እኔ እመጣለኹ፥ እስከዚያ እጅጉን በርትተኽ ጠብቅ በሉት" ሲል።

ሰዓቱ ለዓይን ያዝ ሲያደርግ የበላይ ፈረስ በሚያብረቀርቅ አዲስ ግላስ የተለበጠ ኮርቻ ተጫነ። ኮስትር እርካብ ረግጦ ከፈረሱ ላይ ወጣ፥ አጃቢዎች ተከተሉ፥ ጉዞው ጠላት ሰፈረበት ወደ ተባለው ምድር ኾነ። የወገን ጦር ደጀን ገባ። ወዲያውኑ የውጊያ ዕቅድ ተነደፈ። ምሽት ሸጋ-ሸጋ ምሽግ ተዘጋጀ። አርበኛው በየአዝማቹ በመደራጀት የደጀን አፋፍን ከበበ። ነጋ። ጣሊያ አልፈው ጎጃም ለገቡ ወታደሮቹ ሽፋን ለመስጠት ከጎጃም ማዶ ኾኖ መድፍ ተኮሰ፥ አውሮፕላኖች ቦንብ አዘነቡ። የመድፉ ማጓራት፣ የመትረየሱ መንጫጫት፣ የአውሮፕላኑ መራኮት፣ የጥይቱ እና የቦንቡ ውርጅብኝ ለአርበኞቹ ብርታትንና ልበሙሉነትን አላበሳቸው። የበላይን ትዕዛዝ የሰሙ አርበኞች ረጭ ብለው ቆዬ። ጠላት የማይበረክት ልብ ገዛና የግዮንን ወንዝ ተጠጋ። አርበኞች ከአደፈጡበት እየተነሱ የጠላትን ልብ ራስ ይመቱት ጀመር። ባንድ ልኩን ተሰፍሮ ተሰጠው። ጠላት ውልደቱን ረገመ። ታሪክ ጸሐፊዎች እንደገለጹት " በላይ የወንድ ልክ አሳያቸው"።

አርበኞቹ ሞትን ተጸይፈው፣ መስዋዕትነትን መርጠው በጋለ የአርበኝነት መንፈስ ተዋጉ፣ አገር ነጻ ኾነች። ይኼንን የታዘቡ የአገሬው ገጣሚዎች እንዲኽ አሉ፥

ተላይ በሩቢላ ቦንብ ተጣለበት፣
ተታች መትረየሱ እየፈሰሰበት፣
ኮስትር አልተነሳም ከተቀመጠበት።
እዚኽ ጉች - ከዚያ ጉች የዝንጀሮ ዱለት፣
እጅጉ ሲመጣ ብትንትን ለማለት።

07/04/2023

እህት የወንድሟ ግርግም

ኮርቶ መሞት እንጂ አልመኝ መርመጥመጥ
በ'ሳት አልሸነፍ እንኳንስ በረመጥ።

አውቃለሁ! መመጠን እንደሙሽራ ሆድ
መግደርደር፣ መገደር... ከጎንደሬ ልማድ።
ቢያምረኝ ንቆ መተው!
ኮርቶ ሥም ማሥከበር! ልክ እንደሊጋባው።
አዛኝን አውቃለሁ!
ያቃተኝ...? ያቃተኝን መተው።

ያቃትሽኝ አንቺ ነሽ የጦም ኋላ ምሳ
አንቺን ባየሁ ቁጦር ርሃቤን 'ምረሳ፤
መጣች ብዬ ሁሌ ሙት የምቀሰቅስ
እንደንሥር ዕድሜ ባንቺ የምታደስ።

አንቺም ነሽ እንደኔ....የባሰብሽ ከኔ!

እንዳልለይሽ መንገዱን አላውቅ
ባውቅም ካንቺው ዘንድ አልርቅ
እንዳትለይኝ እኔን አትለቂ
ስለይሽ ደሞ ተነፋራቂ።

እንደቡሔ ጅራፍ ፍቅራችን ተገምዶ፣
የሁለታችን ሕይወት ባንድ ላይ ተዋዶ፤
እንደ እትብት ተቀብሮ፣
በኔው____ባንቺው ጓሮ፤
ኩርፊያችን ነው እንደጉንፋን
በቀን ዕድሜ የሚለቀን።
በፍቅር ሳል ጥል 'ሚያስተፋን
ናፍቆታችን የሚያስታርቀን
ትዝታችን ሸምጋያችን።

ታናሽ እኔ አንቺን አዛዥ
ታላቅ አንቺው ለኔው ታዛዥ፤
እኔ ኩሩ ለኔ ጉዳይ
አንቺ ለማኝ ለኔ ብለሽ።
አንዳቺን ብንሆን፣ ያንዳቺን በዳይ
ገበናችን ሁሌ 'ማይታይ እንደመዞሪያ፣ እንዳደባባይ
ካንዳቺን ቢወጣ፣ ካንዳችን ይገባል ተመስሎ ፀሐይ።

ጳጳስ የእምነት እንጂ የዘር ልጅ ላይኖረው
እኔም መኖር ላልችል ባትኖሪኝ አንቺ ሰው፣
አርባራቱን ታቦት ባንቺው እሳላለሁ
እንደ ንጉሥ ግልገል እጠብቅሻለሁ
እንደ ሥዕለት ህፃን እሳሳልሻለሁ።

አንቺም ነሽ እንደኔ...የባሰብሽ ከኔ!
ውብ ተፈጥሮሽ እስክትሸሽ፣ በ'ራ እንደዋኔ
ምዕራብሽ ሆኜ እንኳ፥ ዕድሜሽ ሲመሽ በኔ
ጀምበር ሆኜ ኖርኩኝ፤ ምሥራቅ ሆነሽ ለኔ።

ለብርቱካን ታፈረ
ከእናርጅና እናውጋ ውስጥ

28/03/2023
02/11/2022

ወስፌና ስንደዶ፣ሳርና ብረቱ
ቀልባቸው ተዋ'ዶ፣ፍቅር ሲጫወቱ
ሰፌድ ወለዱና፣ተበጠረ ስንቱ።
***
* ከድረ ገጽ ያገኘሁት።

ምዕራብ ጎጃም በዘንድሮው ዓመት እየለማ ያለ ስንዴ
28/10/2022

ምዕራብ ጎጃም በዘንድሮው ዓመት እየለማ ያለ ስንዴ

22/10/2022

የቻግኒዋ ኮኮብ- ታሪክ ነጋሪዋ አቀንቃኝ- እጅጋየሁ ሽባባው.........................................
አንዳንድ ዘመን ደግሞ አለ፣ ድንቅ ሰዎች ተለይተው የተፈጠሩበት።አንዳንድ ሰዎችም አሉ በየዘርፉ ምሳሌ ይሆኑ ዘንድ የተፈጠሩ::ከእነዚህ ምድብ ውስጥ ትገኛለች፥ እጅጋየሁ ሽባባው።እጅጋየሁ ሽባባው(በመድረክ ሥሟ ጂጂ) የተወለደችው ጎጃም፣ ቻግኒ ከተማ ወጣ ብላ ከምትገኘው "ስጋዴ ሚካኤል" ከተባለችው መንደር ነው። በልጅነቷ ከብት ጠብቃ፣ ከእምቦሳዎች ጋር ቦርቃ፣ ከሽምብራው ማሳ እሽት ቅምሳ፣ ከወንዙ ተዝናንታ ነው ያደገችው። ጥንት ዕለት ገና በጠዋቱ ለወንድሟ ተቀጥሮ ከነበረው መምህር ዘንድ ሀ-ብላ ፊደልን ተማረች። እናቷ ቀለም የቆጠሩ ነበሩና የተረት እና ልብ ወለድ መፅሐፍትን እያነበቡላት፣ በቅርብ ርቀት ላይ ከሚገኘው ቤተ ክርስቲያን ዝማሬ እየሰማች ነው አስተዳድጓ።

በኋላም ከቤተስቦቿ ጋር ወደ አዲስ አበባ ዘለቀች። የልጅነት አስተዳደጓ ለደረሰችበት የኪነ ጥበብ ከፍታ እርሾ ቢያዋጣም የጥበብ ልክፍቷ ከሸገር ነው የተፀነሰው።ስለ ጥበብ ከኬንያ እስከ አሜሪካ ማትራለች። ሥራዎቿ ገጠር ያዘወትራሉ። ሜዳው ሸንተረሩን ያማትራሉ። ቢሆንም የግጥም ዕሳቤዋን ከተራራ እና ሽለቆ ብቻ አስሬ ላስቀምጥ አልፍልግም። ታሪክ፣ ፍቅር፣ እንድነትን በእጅጉ ሰብከዋልና።አንዳንዱ ድንቅ ድምፅ፣ ሌላው የግጥም ችሎታ፣ አንዳንዱ የድርሰት አቅም ይሰጠዋል። ጂጂ ሁሉንም ሰብስባ ይዛለች። ታሪክ አዋቂ ናት። ምን ማወቅ ብቻ! ታሪክ ነጋሪም ናት። ቃላት ሰድራ፣ዜማ አበጅታ፣በውብ ድምፅ ታሪክን ለትውልድ የምታስተላልፍ ድንቅ ነፍስ ነች፥ ጂጂ።

ጂጂ ዛሬ ልደቷ መሆኑን ሰማሁ። እንኳን ተወልደሽ፥ በውልደትሽ አትርፈናል ልላት ተነሳሁ። ለነገሩ ግን አንዳንዶች ልደቷ ዛሬ ጥቅምት 11 ሳይሆን ጥቅምት 13 ነው ይላሉ። የሆነ ሆኖ የቀናት ልዩነት ስለ ጅጅ ከመፃፍ አላገደንም። ጥያቄው ሌላ ነው። ስለ ትልቅ ሰው፣ስለ ክቡር ሃሳብ፣ ስለገናና ፍጡራን መፃፍ ወይም መናገር ፈልጋችህ “ከየት ልጀምር?” የሚል ጥያቄ ተፈጥሮባችሁ ያውቃል? ይኼ የሚሆነው ከነገሩ ክብደት የመነጨ ነው። ታዲያ እኔ ስለ “ጂጂ” ስፅፍ ከየት ልጀምር? ከፍቅር እስከ መቃብር ልጀምር ይሆን?

አዎ። ፍቅር የነገሮች ሁሉ ቁንጮ ነው። ፍቅር እስከ መቃብር ሲዘልቅ ደግም ሌላ ልዕልና ነው። “ጂጂ እና ፍቅር እስከ መቃብር ምን አገናኛቸው?” የሚል አይጠፋም። ነገሩ ወዲህ ነው። ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ዘመን አይሽሬ የሆነውን ፍቅር እስከ መቃብር መፅሐፍ አንብቦ በተረዳው ልክ ሲዘፍን ብቸኛም የመጀመሪያም አይደለም።ፍቅር እስከ መቃብርንን በመዝፈን ጂጂ የጥበብ ተጋሪው ናት።ፍቅር እስከ መቃብርን ያነበበ ሁሉ "አባ አለም ለምኔን" ያውቃቸዋል። ታዲያ ይኽች ንግስት (ጂጂ) "አባ እለም ለምኔ" ስትል በሰየመችው ዘፈን በጎነትን፣ ለፈጣሪ መገዛትን፣ አመስጋኝነትን ከፍ ያለ ዋጋ ሰጥታ አቀንቅናለች።

አባ ዓለም ለምኔ አባ ዓለም ለምኔ፣
ጀምበር ወጣ አትገባም ሳልሰራ ኩነኔ።
ሰው በአፉ እያነሳ በእጁ ይጥለኛል፣
የልቡን አላውቅም ግራ ይገባኛል።
የልብን ጥያቄ ማነው የሚፈታ፣
ካንተ በቀር አባት ካንተ በቀር ጌታ።

ጂጂ ራሷን ተኮናኝ፣ ጥፋተኛ ታደርጋለች። ጥፋተኛ ነኝ ብሎ ማመን የመፍትሔ ፈላጊዎች ጥሩ መንገድ ነው። የችግሮች ሁሉ ሁሉ መድሃኒት ራስን መፈተሽ ነው። "ሰው በአፉ እያነሳ በእጁ ይጥለኛል" ስትል ሐሜተኞች ያስቸገሯት ትመስላለች። በዚያውም የልብን ጥያቄ ለፈጣሪ ትሰጣለች። በዚሁ ዘፈን ሰብለወንጌል ወክላ ብቅ ብላለች።

ዛሬ ቀጭን ኩታ ነገ ራቁቴን፣
ያገኙትን ወዳጅ ደግሞ ማጣት

20/10/2022

Address

Adet

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አቮላ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share