17/12/2025
ታላቁ አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ በድሬዳዋ ጎዳናዎች ላይ እንደማንኛውም ተራ ሰው ሲንቀሳቀስ መታየቱ የብዙዎችን ቀልብ ስቧል። በዓለም አቀፍ ደረጃ በክብር የሚጠራ፣ በሀገራችንም ቀዳሚ ከሚባሉ ባለሀብቶች አንዱ የሆነው ኃይሌ፣ በትህትናውና በዝቅተኛነቱ ለብዙዎች አርአያ መሆኑን ዳግም አስመስክሯል። በኮንቴይነር ምግብ ቤቶች ውስጥ ተቀምጦ ሲመገብ፣ በባጃጅ ሲጓዝና ከህዝብ ጋር ተቀላቅሎ ሲዘዋወር ማየቱ ለዝናና ለሀብት ያልተንበረከከ ትልቅ ማንነት እንዳለው ያሳያል። በአሁኑ ወቅት ሀገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ ሰው በመያዝ፤ ገንዘብ መቀበል ኖርማል በሆነበት በዚህ አስቸጋሪ ወቅት፣ እንደ ኃይሌ ያለ ስመ ጥር ሰው ያለምንም ስጋት ከህዝቡ ጋር ተቀላቅሎ መታየቱ ትልቅ ትርጉም አለው። ይህ ድርጊቱ ለሰው ልጆች ያለውን ፍቅርና በራሱ ላይ ያለውን መተማመን የሚያሳይ ሲሆን፣ ክብርና ስልጣን ሰውን ከወገኑ ሊለዩት እንደማይገባም አስተምሮናል:: ክብሩና ዝናው ሳይጋርደው እንዲህ በነፃነት መታየቱ እውነተኛ ታላቅነት ከትህትና እንደሚመነጭ ማሳያ ነው።