13/06/2026
"ለወንጌል እና ለሰላም በአንድነት እንሩጥ" በሚል መሪ ቃል የጎዳና ላይ ሩጫ በአርባምንጭ ከተማ መካሄድ ጀምሯል
አርባምንጭ፡ሰኔ 6/2018 ዓ/ም
በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን በደቡብ ምዕራብ ቀጠና የአርባምንጭና አካባቢዋ ቃለ ሕይወት አጥቢያ ቤተክርስቲያናት ሕብረት ወጣቶች አገልግሎት ዘርፍ አዘጋጅነት "ለወንጌል እና ለሰላም በአንድነት እንሩጥ" በሚል መሪ ቃል የጎዳና ላይ ሩጫ በአርባምንጭ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።
መነሻውን ጋሞ አደባባይ እና መድረሻውን ለምለም አደባባይ(አብሌ ጨዶ አደባባይ ) ባደረገው የሩጫ ውድድር ላይ ከ15 ሺህ በላይ የወንጌል አማኞች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡
መርሃ ግብሩ ዘንድሮ ለ4ኛ ዙር እየተካሄደ እንደሚገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ።
በአሰፋ ጪሻ