አርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ባህልና ስፖርት መምሪያ

አርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ባህልና ስፖርት መምሪያ we promote culture,sport

"ለወንጌል እና ለሰላም በአንድነት እንሩጥ" በሚል መሪ ቃል የጎዳና ላይ ሩጫ በአርባምንጭ ከተማ መካሄድ ጀምሯል አርባምንጭ፡ሰኔ 6/2018 ዓ/ም በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን በደቡብ...
13/06/2026

"ለወንጌል እና ለሰላም በአንድነት እንሩጥ" በሚል መሪ ቃል የጎዳና ላይ ሩጫ በአርባምንጭ ከተማ መካሄድ ጀምሯል

አርባምንጭ፡ሰኔ 6/2018 ዓ/ም

በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን በደቡብ ምዕራብ ቀጠና የአርባምንጭና አካባቢዋ ቃለ ሕይወት አጥቢያ ቤተክርስቲያናት ሕብረት ወጣቶች አገልግሎት ዘርፍ አዘጋጅነት "ለወንጌል እና ለሰላም በአንድነት እንሩጥ" በሚል መሪ ቃል የጎዳና ላይ ሩጫ በአርባምንጭ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።

መነሻውን ጋሞ አደባባይ እና መድረሻውን ለምለም አደባባይ(አብሌ ጨዶ አደባባይ ) ባደረገው የሩጫ ውድድር ላይ ከ15 ሺህ በላይ የወንጌል አማኞች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡

መርሃ ግብሩ ዘንድሮ ለ4ኛ ዙር እየተካሄደ እንደሚገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ።

በአሰፋ ጪሻ

‎የጋሞ ጨንቻ እግር ኳስ ክለብ የቦርድ አመራር የ2018 የውድድር ዘመን አፈፃፀምና የ2019 ቀጣይ አቅጣጫ ዙርያ የምክክር መድረክ እያካሄደ  ይገኛል።‎‎​ዋጫ፦ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም ‎‎​...
10/06/2026

‎የጋሞ ጨንቻ እግር ኳስ ክለብ የቦርድ አመራር የ2018 የውድድር ዘመን አፈፃፀምና የ2019 ቀጣይ አቅጣጫ ዙርያ የምክክር መድረክ እያካሄደ ይገኛል።

‎​ዋጫ፦ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም

‎​የጋሞ ጨንቻ እግር ኳስ ክለብ በ2018 የውድድር ዘመን ያስመዘገበውን የሻምፒዮናነት ታሪካዊ ውጤት በማስቀጠል፣ በ2019 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ላይ ጠንካራ ተፎካካሪ ሆኖ ለመቅረብ በሚያስችሉ ተቋማዊና ስነ-ልቦናዊ ዝግጅቶች ዙሪያ ከክለቡ የቦርድ አባላት ጋር ምክክር እየተደረገ ይገኛል ።

‎​የምክክር መድረኩ የ2018 የውድድር ዘመን አፈፃፀም ሪፖርትን ማድመጥ እንዲሁም ለ2019 የውድድር ዓመት አዲስ የቦርድ ምስረታን በማካሄድና ይሁንታ ሰጥቶ ወደ ሥራ ማስገባት የሚሉ ሁለት ዋና ዋና ግቦችን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።

‎​የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪና የክለቡ የበላይ ጠባቂ ዶክተር ደምሴ አድማሱ በውይይቱ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ክለቡ በ2018 የውድድር ዓመት ከፍተኛ ትግል በማድረግና የከፍተኛ ሊጉ ሻምፒዮን በመሆን ወደ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉ ለመላው የጋሞ ሕዝብ ትልቅ ኩራትና ደስታን የፈጠረ ስኬት ነው ብለዋል።

‎​ይህንን የተገኘውን አንጸባራቂ ድልና ውጤታማነት በላቀ ደረጃ ለማስቀጠልም አሳታፊ፣ ግልጽነት ያለው፣ ቅንጅታዊና ሚዛናዊ አሰራር ሊጠናከር እንደሚገባ ዋና አስተዳዳሪው አሳስበዋል።

‎አክለውም በቀጣዩ የፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዓመት ክለቡን ይበልጥ ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ ግልጽ ግብ ተቀምጦ በትኩረት መንቀሳቀስ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

‎​"ክለቡ የአካባቢውን መጠሪያ ይዞ የጋሞን ሕዝብና ባህል በብሔራዊ ደረጃ የሚያስተዋውቅ እንደመሆኑ መጠን፤ ተጫዋቾችና የአሰልጣኝ ቡድኑ ሜዳ ላይ የሚጠበቅባቸውን ሙያዊ ብቃት ብቻ እንዲወጡ ምቹ ሁኔታ መፍጠር ያስፈልጋል ብለዋል።

‎​በመድረኩ የክለቡ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰቦ ሶንቆ የጋሞ ጨንቻ እግር ኳስ ክለብ የ2018 የውድድር ዘመን ዝርዝር አፈፃፀም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን፤ በቀረበው ሪፖርትና በቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት እንደሚደረግበት ይጠበቃል።

‎​በዚሁ የምክክር መድረክ ላይ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶክተር ደምሴ አድማሱ፣ የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ሀኪሜ አየለ፣ የአርባምንጭ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ ሊዲያ ከንቲባ ፣የጋሞ ልማት ማህበር ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ኢንጂነር ማንደፍረው ዱባለ፣ የዞንና የወረዳ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የተጠሪ ተቋማት ኃላፊዎች ፣የክለቡ አሰልጣኞች፣ ተጫዋቾች እና ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

‎በስመኝ አክሊሉ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአርባምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ  በነገው ዕለት ይመረቃል መሶብ በርካታ አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል በመሰብሰብ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ፣ ብቃት ያለ...
08/06/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአርባምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ በነገው ዕለት ይመረቃል

መሶብ በርካታ አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል በመሰብሰብ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ፣ ብቃት ያለው ፣ ፈጣንና ከሙስና የፀዳ፣ ዜጎችን የሚመጥን አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ኢንሼቲቭ ነው።

የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚስተዋሉ ቢሮክራሲዎችን በመቀነስ የዜጎችን እርካታ ለማሳደግ ተደራሽ ታስቦ የተጀመረው መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ዜጎች በማዕከሉ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ከቤታቸው ወይም ከሥራ ቦታቸው ሆነው በኮምፒውተርና በሞባይል እንዲያከናውኑ የሚያስችል ነው።

የአርባምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል ውስጥ 4 የፌደራል 5 የክልል ተቋማት በውስጡ የያዘ ሲሆን በአጠቃላይ 32 የተለያዩ የአገልግሎት አይነቶችን ይሰጣል።

በክልሉ ሀለተኛው የሆነው የአርባምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ፣ የፌደራል እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በነገው ዕለት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል።

የማዕከሉ ግንባታ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን እንዳከናወነውም ተመላክቷል።

#ርዕሰመስተዳድርጽቤት

በአርባምንጭ ከተማ የኮሪደር ልማት አካል የሆነው ዘመናዊ የመንገድ ዳር መብራት ዝርጋታ በምስል
29/05/2026

በአርባምንጭ ከተማ የኮሪደር ልማት አካል የሆነው ዘመናዊ የመንገድ ዳር መብራት ዝርጋታ በምስል

ወጣቱ በአካለና በአዕምሮ ብቁ ሆኖ እንዲያድግ የስፖርታዊ ማዘውተሪያ ስፍራዎች መገንባታቸው ለስፖርቱ እድገት አስፈላጊ መሆናቸው ተጠቆመአርባምንጭ : ግንቦት 21 / 2018 ዓ.ም. ()በአርባም...
29/05/2026

ወጣቱ በአካለና በአዕምሮ ብቁ ሆኖ እንዲያድግ የስፖርታዊ ማዘውተሪያ ስፍራዎች መገንባታቸው ለስፖርቱ እድገት አስፈላጊ መሆናቸው ተጠቆመ

አርባምንጭ : ግንቦት 21 / 2018 ዓ.ም. ()

በአርባምንጭ ከተማ የኮሪዴር ልማት አካል የሆኑ ስፖርታዊ ማዘውተሪያ ስፍራዎች በከፍተኛ ፍጥነትና ጥራት እየተገነቡ ይገኛሉ

አስተያየታቸውን ለጋሞ ቴሌቪዥን የሰጡት የአርባምንጭ ከተማ ባህልና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ገበየሁ ጻራ ወጣች በአካልና በአዕምሮ ብቁ ሆነው እንዲያድጉ የስፖርታዊ ማዘውተሪያ ስፍራዎች መገንባት አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።

በአሁኑ ሰዓት ወጣቱ የማህበራዊ ሚዲያ ጥገኛ ከመሆን ወጥተው ስፖርት በመስራት ጤናውን ጠብቆ ጊዜውን አልባለ ቦታ ከማሳለፍ እንድቆጠቡ እንደሚረዳም ተናግረዋል።

በከተማው በርካታ የእግር ኳስ ተጫዋቾች የሚፈልቁት መሰል ስፖርታዊ ማዘውተሪያዎች በአግባቡ ባልበጁበት አቧራማና ጠጠር ሜዳዎች እንደነበር የሚያስታውሱት የጋሞ ጨንቻ እግር ኳስ ክለብ አሰልጣኝ ማቴዎስ ለማ እየተገነቡ የሚገኙ ማዘውተሪያ ስፍራዎች ለከተማው ወጣቶች ተስፋን የሚሰጥ እንደሆነ ገልፀዋል።

የአርባምንጭ ከተማ በሁሉም አቅጣጫ በከፍተኛ ሁኔታ እየለማች ትገኛለች የምትለው የቀድሞ የአርባምንጭ ከተማ ተጫዋች ምስር ላቀው ነች።

የከተማዋ ሁለንተናዊ እድገት አግራሞት እንደፈጠረባት ገልፃ ሁሉን ያማከለ እጅግ ዘመናዊ ማዘውተሪያ ስፍራዎች በከተማዋ ሁሉም ስፍራዎች መገንባታቸው ለእግር ኳሱ እድገት ጉልህ አስተዋፆ እንዳለው ትናገራለች ።

የከተማው የቀድሞ ተጫዋቾች በበኩላቸው የማዘውተሪያዎቹ መገንባታ ለወጣቱ ትውልድ ብሩህ ተስፋን ይዞ የመጣ መሆኑን ገልፀዋል።

የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎችም በስፖርታዊ ማዘውተሪያዎች መገንባት የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል።
ጋሞ ቴቪ

አርባ ምንጭ ከነማ  መቻል እግር ኳስ ክለብን 2 ለ1 አሸነፈአርባምንጭ፦ ግንቦት 20/2018 ዓ.ም በየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 34ኛ ሳምንት የውድድር መርሃ ግብር መሰረት ዛሬ ምሽት 12፡00...
28/05/2026

አርባ ምንጭ ከነማ መቻል እግር ኳስ ክለብን 2 ለ1 አሸነፈ

አርባምንጭ፦ ግንቦት 20/2018 ዓ.ም

በየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 34ኛ ሳምንት የውድድር መርሃ ግብር መሰረት ዛሬ ምሽት 12፡00 ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ በአርባ ምንጭ ከነማ 2 ለ1 አሸናፊነት ተጠናቋል።

ለአዞዎቹ የድል ጎሎችን አሸናፊ ተገኝ በ32ኛው ደቂቃ እንዲሁም ቴዎድሮስ ባንቴ በ60ኛው ደቂቃ አስቆጥረዋል። ለመቻል እግር ኳስ ክለብ ብቸኛዋን ግብ ፈቱዲን ጀማል በ46ኛው ደቂቃ አስቆጥሯል።

በዚህ ድል አርባ ምንጭ ከነማ ነጥቡን ወደ 32 ከፍ በማድረግ በሊጉ ለመቆየት ጠቃሚ ውጤት አስመዝግቧል።

በዳዊት አቦዬ

በአርባምንጭ ከተማ የኮሪደር ልማት አካል የሆነው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ በከፊል
28/05/2026

በአርባምንጭ ከተማ የኮሪደር ልማት አካል የሆነው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ በከፊል

አርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ባህልና መምሪያ ዞናዊ ብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍና የምርጫ ቅስቀሳ መርሐ ግብር አርባምንጭ፡ግንቦት 18/2018 ዓ.ም በመጪው ግንቦት 24 ለሚካሄደው ታሪካዊው ...
26/05/2026

አርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ባህልና መምሪያ ዞናዊ ብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍና የምርጫ ቅስቀሳ መርሐ ግብር

አርባምንጭ፡ግንቦት 18/2018 ዓ.ም

በመጪው ግንቦት 24 ለሚካሄደው ታሪካዊው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ፣ እጅግ ደማቅና ታላቅ የብልጽግና ፓርቲ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በአርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል ።

ሻምፒዮኑ አርሰናል ክሪስታል ፓላስን 2ለ1 አሸነፈ*****************ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የዘለቀው የመድፈኞቹ የዋንጫ ጥማት ዛሬ በደመቀ ሁኔታ ተቋጭቷል።አርሰናል በ38ኛው ሳ...
24/05/2026

ሻምፒዮኑ አርሰናል ክሪስታል ፓላስን 2ለ1 አሸነፈ
*****************

ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የዘለቀው የመድፈኞቹ የዋንጫ ጥማት ዛሬ በደመቀ ሁኔታ ተቋጭቷል።

አርሰናል በ38ኛው ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታው ክሪስታል ፓላስን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የሊጉን የክብር አክሊል ይረከባል።

በመጀመሪያው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ገብርኤል ጀሱስ ያስቆጠራት ግብ የድሉን መንገድ የጠረገች ሲሆን፣ ቡድኑ እስከ ጨዋታው ፍጻሜ ድረስ ብቃቱን በማስመስከር የለንደን ጎዳናዎችን በደስታ እና በእልልታ እንዲሞሉ አድርጓል።

በሌሎች የዛሬው የመጨረሻ ሳምንት መርሃ ግብሮች ማንቸስተር ሲቲ በአስቶን ቪላ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ሲሸነፍ ፣ ማንቸስተር ዩናይትድ ብራይተንን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት ሲረታ፣ ፉልሃም ኒውካስትልን 2 ለ 0 ሲያሸንፍ እንዲሁም ዌስትሃም ሊድስን በ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ቢያሸንፍም ወደታችኛው ሊግ ወርዷል።

በሌላ በኩል ሊቨርፑል ከብሬንትፎርድ ጋር 1 ለ 1 ሲለያይ፣ ሰንደርላንድ ቼልሲን 2 ለ 1 በማሸነፍ ያልተጠበቀ ውጤት አስመዝግቧል።

ቶተንሃም ኤቨርተንን 1 ለ 0 አሸንፎ በሊጉ ሲቆይ ፣ በርንሌይ ከዎልቭስ እንዲሁም ኖቲንግሃም ፎረስት ከቦርንማውዝ ጋር 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት የውድድር ዘመኑን አጠናቀዋል።

በዘረንቶስ ሰለሞን

በአርባምንጭ ከተማ በአዲስ መልክ እየለማ የሚገኘው የአባያ ሐይቅ ሞጬ ደሴት የቱሪዝም መስህብ ውብና ማራኪ ገፅታ፡-
24/05/2026

በአርባምንጭ ከተማ በአዲስ መልክ እየለማ የሚገኘው የአባያ ሐይቅ ሞጬ ደሴት የቱሪዝም መስህብ ውብና ማራኪ ገፅታ፡-

Address

Arbaminch
Arba Mintch
230305

Telephone

+251960490301

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ባህልና ስፖርት መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share