Sidama Design and Construction Supervision Enterprise

Sidama Design and Construction Supervision Enterprise SiDCSE is a level-1 Public Construction consulting firm

ኢንተርፕራይዛችን ከሲዳማ ክልል ውጪ በመውጣት ሰርቶ ያስመረቀው ፕሮጀክት**************ሲደማ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ኢንተርፕራይዝ በሲዳማ ክልል ውስጥ በሚሰራቸው ሥራዎች ብቻ ሳይወሰ...
12/05/2026

ኢንተርፕራይዛችን ከሲዳማ ክልል ውጪ በመውጣት ሰርቶ ያስመረቀው ፕሮጀክት
**************
ሲደማ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ኢንተርፕራይዝ በሲዳማ ክልል ውስጥ በሚሰራቸው ሥራዎች ብቻ ሳይወሰን ከክልሉ ወጭ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጌዲኦ ዞን የጨለለቅቱ ከተማ ውሃና ሳቴሸን ፕሮጀክት በማማከር ግንቦት 1 ቀን 2018 ዓ/ም ለምረቃ አብቅቷል፡፡
ውጤታማ የነበረው የፕሮጀክት ግንባታ ቁጥጥር እና ከንትራት አስተዳደር ሥራችን ፕሮጀክቱ በላቀ ጥራት ተገንብቶ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን ሚና ተወጥቷል፡፡ ለዚህ ጥረት ውጤት የፌደራል ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የጌዲኦ ዞን መስተዳድር እንዲሁም ከከተማ አስተዳሩና ከነዋሪው ከፍተኛ ምስጋናና የሞራል ስንቅ አግኝተናል፡፡
ተቋማችን ከተመሠረተ አጭር ዕድሜ ብቻ ያስቆጠረ ቢሆንም ወደ አጎራባች ክልሎች ወጥቶ የመወዳደር፣ ገቢ የመሰብሰብ እና የመፈጸም አቅም መፍጠር ችሏል፡፡ የተቋማችን ጠንካራ የመፈጸም አቅም የክልላችን መንግሥት አፈጻጸም ጥንካሬ ነጻብራቅ ምስል ነው፡፡ ጠንካራ ክልል ጠንካራ ተቋማትን ይወልዳል፡፡

ኢንተርፕራይዛችን በአማካሪነት የተሳተፈበት የጨለለቅቱ ከተማ ንፁህ መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት በይፋ ተመረቀ******በሲዳማ ዲዛይና ግንባታ ቁጥጥር ኢንተርፕራይዝ አማካሪነት በጌዴኦ ዞን ...
09/05/2026

ኢንተርፕራይዛችን በአማካሪነት የተሳተፈበት የጨለለቅቱ ከተማ ንፁህ መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት በይፋ ተመረቀ
******
በሲዳማ ዲዛይና ግንባታ ቁጥጥር ኢንተርፕራይዝ አማካሪነት በጌዴኦ ዞን ጨለለቅቱ ከተማ አስተዳደር የተገነባው የንፁህ መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት በይፋ ተመረቀ።

በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የኢፌድሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ድኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አበባዬሁ ታደሰ(ዶ/ር)፣ የሲዳማ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ኢንተርፕራይዝ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የክልል፣ የጌዴኦ ዞንና የጨለለቅቱ ከተማ አስተዳደር አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል።

ፕሮጀክቱ ኢንተርፕራይዛችን ከሲዳማ ክልል ውጪ ወጥቶ ከሚሰራቸው የልማት ፕሮጀክቶች ቀዳሚው ነው።

በ182 ሚ/ን ብር በላይ ወጪ በጥራት ተገንብቶ የተመረቀው የከተማዋ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ከ49 ሺህ በላይ የከተማውንና የአከባቢውን ገጠር ቀበሌያት ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ያደርጋል።

ኢንተርፕራይዛችን ከ1.7 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ በመገንባት ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን በማማከር ላይ ነው *****ከተቋቋመ ሁለት ዓመታት ከጥቂት ወራት ብቻ ያስቆጠረው ሲዳማ ዲዛይንና ግንባታ ...
29/04/2026

ኢንተርፕራይዛችን ከ1.7 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ በመገንባት ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን በማማከር ላይ ነው
*****
ከተቋቋመ ሁለት ዓመታት ከጥቂት ወራት ብቻ ያስቆጠረው ሲዳማ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ኢንተርፕራይዝ በአጠረ ጊዜ በቢሊዮኖች ወጪ የሚገነቡ ተቋማትን የማማከር አቅም መገንባት ችሏል።

እየተገባደደ በሚገኘው የ2018 በጀት ዓመት እያማከረ ከሚገኝባቸው ትላልቅ የጥናት፣ የዲዛይንና የግንባታ ቁጥጥር ፕሮጀክቶች መካከል የክልሉ እና የፌደራል መንግሥት የሚያሰራቸው ትላልቅ የንጹህ መጠጥ የውሃ ፕሮጀክቶች ይገኙበታል።

እነዚህም በሀዋሳ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው የፋራ ሒጣታ፣ አለታ ወንዶ ከተማ፣ ሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ እና አለታ ጩኮ ከተማ ውስጥ እየተገነባ የሚገኘው የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ናቸው።

ኢንተርፕራይዛችን እያማከራቸው የሚገኙት የአራቱ ተቋማት በርካታ የክልሉን ነዋሪ ቀጥታ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሲሆን ድምር የግንባታ ወጪያቸው 1,723,747,594,.99 እንደሆነም ተመልክቷል።

የጂኦፊዚካል ናሙና አሰባሰብ ዙሪያ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ አዘጋጅነት ስሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ*****ኢንተርፕራይዛችንን ጨምሮ የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ አካዳሚክ አባላት እና የሲዳማ ክልል ውሃ፣ ...
25/04/2026

የጂኦፊዚካል ናሙና አሰባሰብ ዙሪያ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ አዘጋጅነት ስሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ
*****
ኢንተርፕራይዛችንን ጨምሮ የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ አካዳሚክ አባላት እና የሲዳማ ክልል ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ባለሙያዎችን በማሳተፍ ላለፉት 10 ቀናት ስስጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል።

ተግባር ተኮር እንደሆነ የተነገረው በዩኒቨርስቲው ለሁለተኛ ጊዜ የተዘጋጀው ስልጠና “የ ERT እና የTEM ዘዴዎችን በመጠቀም የጂኦፊዚካል ናሙና ማሰባሰብ፣ ማቀናበር እና መተርጎም” የሚል ርዕስ የተሰጠው ነው።

ዩኒቨርስቲው ስልጠናውን የRapid Groundwater Support Mapping ፕሮጀክት ጋር በመተባበር የዘርፉን ባለሙያዎች አቅም ማጎልበትን ኢላማ አድርጎ ማዘጋጀቱ በወቅቱ ተነስቷል።

በስብሰባው ማጠቃለያ ወቅት ተሳታፊዎች የElectrical Resistivity Tomography (ERT) እና Time-Domain Electromagnetic (TEM) ዘዴዎችን በመጠቀም የመስክ መረጃ አሰባሰብ፣ መተንተን እና መተርጎም ዙሪያ ተግባራዊ ልምድ ማግኘታቸውን አንስተዋል።

ስልጠናው በከርሰ ምድር ውሃ ፍለጋ ዙሪያ ያሉ ነባር ግንዛቤዎችን በማስፋት ኢትዮጵያ ውስጥ የበለጠ ውጤታማ የውሃ ሀብት አስተዳደር ሥርዓት ያጠናክራል ስል ዩኒቨርስቲው በዘገባው አስታውሷል።

የመንግስት ልማት ድርጅቶች የብልፅግና ፓርቲ ህብረት አባላት ኮንፍራንስ ተካሄደ*****ከሲዳማ ክልል የተወጣጡ ሁለቱ የመንግሥት የልማት ድርጅቶችና ተቆጣጣሪ ባለስልጣኑን ያካተተ የብልፅግና ፓር...
22/04/2026

የመንግስት ልማት ድርጅቶች የብልፅግና ፓርቲ ህብረት አባላት ኮንፍራንስ ተካሄደ
*****

ከሲዳማ ክልል የተወጣጡ ሁለቱ የመንግሥት የልማት ድርጅቶችና ተቆጣጣሪ ባለስልጣኑን ያካተተ የብልፅግና ፓርቲ ህብረት አባላት ኮንፍራንስ በዛሬው ዕለት ተካሂዷል።

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ባለስልጣን፣ ሲዳማ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ኢንተርፕራይዝ እና ሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽንን ያቀፈው የብልፅግና አባል ሠራተኞችን በጋራ ኅብረት “ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር” በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት ተከብሮ ውሏል።

በኮንፍራንሱ የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፖርቲ ቅ/ፅ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ኤልያስ ጨምሮ የሶስቱም ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች፣ አመራሮችና የህብረቱ አባላት ተሳታፊ ሆነዋል።

በአባላት የጋራ መድረኩ ላይ የፓርቲው ማኒፌስቶ እና ሪፖርት ቀርቦ የጋራ ውይይት የተደረገ ሲሆን የህብረቱ አመራሮች ምርጫም ተከናውኗል።

ጉባኤው የጋራ አቋም መግለጫ በማውጣት ፍጻሜውን አግኝቷል።

ሲዳማ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ኢንተርፕራይዝ ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበረከተለት*******የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በ2ኛውና 3ኛው ዙር የኮሪደር ልማት ከተማዋን ...
19/04/2026

ሲዳማ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ኢንተርፕራይዝ ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበረከተለት
*******
የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በ2ኛውና 3ኛው ዙር የኮሪደር ልማት ከተማዋን ውብ መዳረሻ ለማድረግ አስተዳደሩ የጀመረውን ራዕይ ከዳር ለማድረስ የነቃ ተሳትፎ ላደረጉ ግለሰቦች፣ ተቋማትና ድርጅቶች ዕውቅና ሰጥቷል።

ኢንተርፕራይዛችንም በአማካሪነት ላበረከተው አስተዋጽአ የተበረከተለትን እውቅናና ምስጋና በዋና ሥራ አስኪያጁ ኢ/ር ይርጉ ታደሰ በቦታው ተገኝተው ተቀብለዋል።

በዕለቱ ከኢንተርፕራይዛችን በተጨማሪ ከንቲባው የክልሉን አስተባባሪ ኮሚቴ በተለይም ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞንና የካቢኔ አባላትን፣ የሀዋሳ ከተማ አስተባባሪና ካቢኔ አባላት፣ ኮንትራክተሮችን ጨምሮ ግብዓት አቅራቢዎችና የመንግስት ተቋማትን እንዲሁም ለአጠቃላይ ለከተማዋ ነዋሪዎች በምስጋጋና እውቅና መልዕክታቸው ስለነቃ ተሳትፏቸው ይድረስ ብለዋል።

ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ                   ===ተቋማችን ባለው ክፍት የሥራ መደብ ላይ ብቃት ያለው ባለሙያ አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። ስለሆነም መስፈርቱን የምታሟሉ ተወዳዳሪ...
07/04/2026

ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ
===
ተቋማችን ባለው ክፍት የሥራ መደብ ላይ ብቃት ያለው ባለሙያ አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። ስለሆነም መስፈርቱን የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች በዋና ቢሮ በአካል ቀርባችሁ እንድትመዘገቡ እናስታውቃለን።

01/04/2026
በሀዋሳ ከተማ የተጀመረው የከባድ ጎርፍ መውረጅ ቦይ ግንባታ እየተፋጠነ መሆኑ ተመለከተ===== በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከዶሮ እርባታ እስከ ሀዋሳ ማዕከላዊ ማረሚያ ተቋም እና ከማዕከላዊ ማረ...
28/03/2026

በሀዋሳ ከተማ የተጀመረው የከባድ ጎርፍ መውረጅ ቦይ ግንባታ እየተፋጠነ መሆኑ ተመለከተ
=====

በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከዶሮ እርባታ እስከ ሀዋሳ ማዕከላዊ ማረሚያ ተቋም እና ከማዕከላዊ ማረሚያ እስከ ሪፈራል ሰርክል ድረስ ያለው የከባድ ጎርፍ መውረጃ ውቅር በሁለት ተቋራጮች እየተሰራ ይገኛል።

ኢንተርፕራይዛችን የጎርፍ መውረጃ ቦዮች ዲዛይን፣ የግንባታ ቁጥጥር እና የኮንትራት አስተዳደር ሥራዎች ተቀብሎ ወደ ሥራ ተገብቷል።

ሥራውን በአንድ ወር ውስጥ ለማጠናቀቅ በተቋራጭ፣ በአማካሪ፣ አሰሪ እና በህብረተሰቡ ድጋፍ ቀንና ማታ 24 ሰዓት በቅንጅት በተደራጀ ሁኔታ እየተሰራበትም ይገኛል።

ኢንተርፕራይዙ ለሥራው የሚያስፈልጉ ሙሉ ባለሙያዎችን በማሰማራት ዲዛይንኑም ግንባታ ቁጥጥሩንም በተቀናጀ ሁኔታ እያከናወነው ሲሆን በቀጣይም በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የሚሰሩ የልማት ሥራዎች ላይ አሻራውን ለማኖር አቅዶ እየተንቀሳቀሰ ነው።

የሲዳማ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ኢንተርፕራይዝ የ10 ዓመት እስትራቴጂክ ዕቅድ ዝግጅት የባለድርሻ አካላት ምክክር መድረክ ተካሄደ=====በዝግጅት ምዕራፍ ላይ የሚገኘው የሲዳማ ዲዛይንና ግንባ...
25/03/2026

የሲዳማ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ኢንተርፕራይዝ የ10 ዓመት እስትራቴጂክ ዕቅድ ዝግጅት የባለድርሻ አካላት ምክክር መድረክ ተካሄደ
=====
በዝግጅት ምዕራፍ ላይ የሚገኘው የሲዳማ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ኢንተርፕራይዝ የ10 ዓመት እስትራቴጂክ ዕቅድ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ለውይይት ቀርቦ ምክክር ተደርጓል።

መድረኩን ከተቋሙ ምስረታ ጀምሮ ጠንካራ ድጋፍ በማድረግ ለስኬት ያበቁት የተከበሩ አስፋው ጎኔሳ በንግግር አስጀምረውታል።

ተቋሙ የ10 ዓመት ዕቅዱን ኢቨር ግሪን ኮንሰልታንሲ ከተባለ ሀገር በቀል አማካሪ ጋር ውል በመግባት እያሰራ የሚገኝ ሲሆን አማካሪው ለስትራቴጂክ ዕቁዱ መነሻ የሚሆኑ የውይይት ነጥቦች አቅርቦ የባለድርሻ አካላት በቡድን ተከፋፍለው ውይይት በማድረግ ግብዓት አቅርበዋል።

በመድረኩ የተገኙ የባለድርሻ አካላት የተቋሙ ጥንካሬ፣ ድክመት፣ ዕድሎች እና ስጋቶችን ለይተው በዝርዝር በማቅረብ የእስትራቴጂክ ዕቅዱ አካል እንዲሆን ሲሉ ምክረ ሀሳባቸውን አቅርበዋል።

አማካሪው የተሰጡ ግብዓቶችን አካቶ ተቋሙን ተወዳዳሪ ለማድረግ የሚያስችል ስትራቴጂክ ዕቅድ እንዲያዘጋጅ በመድረኩ ላይ ተነስቷል።

ሁለተኛ ዙር ኢትዮ- ኮደርስ ስልጠና ተጀመረ====ሀለተኛ ዙር የኢትዮ- ኮደርስ ስልጠና ከሲዳማ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ ጋር በመተባበር እየተሰጠ ይገኛል።ስልጠናው የ5 ሚሊዮን ኢትዮ...
23/03/2026

ሁለተኛ ዙር ኢትዮ- ኮደርስ ስልጠና ተጀመረ
====
ሀለተኛ ዙር የኢትዮ- ኮደርስ ስልጠና ከሲዳማ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ ጋር በመተባበር እየተሰጠ ይገኛል።

ስልጠናው የ5 ሚሊዮን ኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በተለያዩ ምክንያቶች ያልወሰዱ፣ ወስደው ያላጠናቀቁና ሰርተፊኬት ያልወሰዱ የኢንተርፕራዙን ሠራተኞች ለመደገፍ ታስቦ ተዘጋጅቷል።

ኢንተርፕራይዙ ዘመኑ ከደረሰበት ዲጂታል ዕድገት የተላመደ ብቁ ሠራተኛ በማብቃት ለአገልግሎት አሰጣጥ ብርቱ አበርክቶ እንዲጫወቱ በማሰብ በልዩ ትኩረት ወስዶ እየሰራበት ነው። ለዚህም ሁሉንም ሰልጠና ወስደው ሰርተፊኬት ለሚወስዱ ሠራተኞች ለማበረታታት በምዘና ሥርዓት ውስጥ አንደ ዋነኛ ነጥብ አካቶ በመስራት ላይም ይገኛል።

Address

Awassa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sidama Design and Construction Supervision Enterprise posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Sidama Design and Construction Supervision Enterprise:

Share