03/09/2024
ለሁሉም መገናኛ ብዙሃን /ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንድትሳተፉ ስለመጋበዝ/
ተቋማችን በ2016 በጀት ዓመት አፈፃፀም፣ በ2017 በጀት ዓመት ዋና ዋና የትኩረት መስኮች ዙሪያ እንዲሁም በአዲሱ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ማሻሻያ ላይ ነገ ረቡዕ ነሃሴ 29 ቀን 2016 ዓ.ም ጠዋት 4፡00 ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል፡፡
ጋዜጣዊ መግለጫው ሜክሲኮ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ንግድ ሥራ ት/ቤት ፊት ለፊት በሚገኘው ንብ ባንክ ዋና መስሪያ ቤት ህንፃ 17ኛ ፎቅ ላይ ስለሚሰጥ፤ ሁሉም መገናኛ ብዙሃን በቦታው ተገኝታችሁ በጋዜጣዊ መግለጫው እንድትሳተፉና መረጃውንም ተደራሽ እንድታደርጉልን በአክብሮት እንጋብዛለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት