Addis Belete Fan

Addis Belete Fan about ddis belete daily information

"ቆይ አንች ሴት ነሽ ጫካ ውስጥ ምን ትሰሪያለሽ"?ሸዋረገድ ገድሌ የጀግንነት ተምሳሌት በ1935 የኢጣሊያን ወረራ ጊዜ መረጃ ስንቅ በማቀበል ተርፎም መሳሪያ በመያዝ ጠላትን በመጣበት በመመለስ...
20/02/2021

"ቆይ አንች ሴት ነሽ ጫካ ውስጥ ምን ትሰሪያለሽ"?

ሸዋረገድ ገድሌ የጀግንነት ተምሳሌት በ1935 የኢጣሊያን ወረራ ጊዜ መረጃ ስንቅ በማቀበል ተርፎም መሳሪያ በመያዝ ጠላትን በመጣበት በመመለስ ጀግንነትን ያሳየች ሴት ዕንቁአችን ናት።

በ1935 ጦርነት ጊዜ ወደ ጅማ ሂዳ ከገረ ሱዱኪ ጦር ጋር ተቀላቅላ ተዋግታለች ታላቆ አርበኛ ሸዋረገድ ገድሌ ያን ጊዜ በነበረው ውጊያ ጣሊያኖች ማረኮት በጣሊያኑ ፊት ስትቀርብ በንቀት ነበር ያያት ምክንያቱም ሴት መሆኖና አርበኛ መሆኖን ስላልተቀበለ ጣሊያኑ "ቆይ አንች ሴት ነሽ ጫካ ውስጥ ምን ትሰሪያለሽ?" አላት እንግዲህ ልብ በሉ የጣሊያን ጦር አሸንፎል የእሶ ጦር ከሆላ ተሸንፎል።

ምን ብትል ነፃ ትወጣለች? ምንም አያስቸግርም "አስገዲደውኝ ነው።" ማለት ትችል ነበር።
ኢትዮጲያዊነት ሚስጥሩ ስለገባት "የአንበሶች መኖሪያ ጫካ ውስጥ ስለሆነ" አለቻቸው አያችሁ አርበኞቻችን ስለሀገራቸው ተሰውተው ነው ያቆሞት እነ ባልቻ ሳፎ አጨብጫቢ ሸላሚ በሌለበት ብቻውን ሂዶ የጣሊያንን የጦር መሪውንና ጠባቂዎቹን እረሽኖ የተሰዋ አርበኛ ያሉበት ሀገር ነው ያለነው።

እምየ ሚኒልክ የጊወርጊስን ታቦት አውጥተው በማሪያም ምለው ህዝቡን ቀስቅሰው አድዋ ላይ የነፃነታችንን በር የከፈትንበት ጊዜ ነው።
ኢትዮጲያየ3000 ዓመት ታሪክ ያላት እያልን አንሸወድ የ6000 ዓመት ታሪክ ነው ያላት ምንጭ መራራ እውነት ከሚለው መፅሀፍ ነው ያገኘሁት ኢትዮጲያ "ታሳልፋለች እንጅ አታልፍም"

ስለ አድዋ በእንግሊዘኛ ከተፃፈው መፅሀፍ ለአድዋ ድል ምክንያቱ አዋሉም የሚባል ለጣሊያኖች የተሳሳተ መረጃ የሚሰጥ ሰው ነው ይላል ግን ፍፁም ስህተት ነው። በጀግና ልጆቾ ነፃነት አግኝተናል። የመለኮታዊ ሀይል(spiritual power) እንዳለ ሁኖ የአርበኞቻችን ክብር መጠበቅ የእኛ ሀላፊነት ነው።

"ክብር ለአርበኞቻችን"

13/06/2013
ወገልጤና
አድስ በለጠ

ኦርቶዶክስ ተዋሕዶን እንወቅ!:ኦርቶዶክስ መልስ አላትክፍል_12ቤተክርስቲያን ለምን እንሳለማለን?ቤተክርስቲያን የሚለው ቃል  #በ3 ዓይነት ፍቺ አጠቃቀም በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እናገኛለን።    ...
24/06/2020

ኦርቶዶክስ ተዋሕዶን እንወቅ!:
ኦርቶዶክስ መልስ አላት
ክፍል_12
ቤተክርስቲያን ለምን እንሳለማለን?

ቤተክርስቲያን የሚለው ቃል #በ3 ዓይነት ፍቺ አጠቃቀም በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እናገኛለን። ሕንጻውን ቤተክርስቲያን እንለዋለን። የክርስቲያኖች ሕብረት ወይም አንድነት ቤተክርስቲያን ይባላል። እያንዳንዱ ግለሰብ ቤተክርስቲያን ይባላል። አምላካችን እግዚአብሔር አስቀድሞ ለሙሴ "በመካከላቸው አድር ዘንድ መቅደስ ሥሩልኝ " ብሏል ። (ዘጸ25:8) ይህም የሚያመለክተው መቅደሱን መሥራት ከፈቃደ እግዚአብሔር የተገኘ እንጂ ፈጠራ እንዳልሆነ ግልጽ ያደርግልናል ። ሕንፃ ቤተክርስቲያኑ ድንጋይ ነው ፣ ጭቃ ነው አይባልም ። እቃው የተሰራበት ድንጋይ ሆነ ፣ ጭቃ ሆነ ፣ ሣር ሆነ የሚከብርበት የሚመለክበት #ጌታ ነው ። በወንጌል ጌታ "ቤቴ የጸሎት ቤት ይባላል የአባቴን ቤት የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችሁት " (ዮሐ 2:13) በማለት ገርፎ ሲያስወጣቸው እናያለን ። ታዲያ ቤቱ የማይከብርበት ቢሆን ሕንጻው የማያስፈልግ ቢሆን ጌታ አምላካችን በጅራፍ ገርፎ ባላስወጣቸው ነበር ።
(እንሰግዳለን)
በህንፃ ቤተእግዚአብሔር ተገኝተን እንሳለማለን ፣ እንሰግዳለን ይኸውም ለባለቤቱ ያለንን ፍቅርና አክብሮት ለመግለጽ ነው ። የመስገዳችንም ምስጢር በቤተ እግዚአብሔር ፊት ስለሆነ የምንሰግደው ለእግዚአብሔር እንጂ ለሕንፃው አይደለም ። እስኪ መረጃ የሚሰጡንን ጥቅሶች እንመልከት ። 2ኛ ዜና መዋ 7:1 " ሰሎሞንም ጸሎቱን በፈፀመ ጊዜ እሳት ከሰማይ ወረደ የሚቃጠለውን መስዋዕትና ሌላ መስዋዕቱን በላ የእግዚአብሔርም ክብር ቤቱን ሞላ የእግዚአብሔርም ክብር ቤቱን የእግዚአብሔርን ቤት ሞልቶት ነበርና ካህናቱ ወደ እግዚአብሔር ቤት መግባት አልቻሉም ። የእስራኤልም ልጆች ሁሉ እሳቱ ሲወርድ የእግዚአብሔርም ክብር በቤቱ ላይ ሲሆን ያዩ ነበር በወለሉም ላይ በግምባራቸው ወደ ምድር ተደፍተው #ሰገዱ እርሱ መልካም ነውና ምህረቱም ለዘለዓለም ነውና ብለው እግዚአብሔርን አመሰገኑ " በማለት በግልፅ መፅሐፍ ቅዱስ የክብሩ መገለጫ የሰማይ ደጅ እንደሆነች በተለያዩ ቦታዎች ያስረዳናል ። መፅ.ሳሙ.ካል 12:20 "ዳዊትም ከምድር ተነስቶ ታጠበ ተቀባም ልብሱንም ለወጠ ወደ እግዚአብሔርም ቤት ገብቶ #ሰገደ " ይላል ። መዝ 5:7 " እኔ ግን በምሕረትህ ብዛት ወደ ቤትህ እገባለው አንተንም በመፍራት ወደ ቅድስናህ መቅደስ #እሰግዳለሁ " ። መዝ 28(29):2 "የስሙንም ክብር ለእግዚአብሔር አምጡ በቅድስናው ስፍራ ለእግዚአብሔር #ስገዱ " ይላል ።
ታዲያ ይህ የቅድስና ስፍራ ቤተክርስቲያን አይደለምን ? መዝ 131(132):7 "ወደ ማደሪያዎቹ እንገባለን እግሮቹ በሚቆሙበት ሥፍራ #እንሰግዳለን " ። ማደሪያው ቤቱና ታቦቱ እንደሆነ እና በዛ ሆኖ ሙሴን እንደሚያናግረው በዘጸ25:22 ላይ ገልፆታል ። በሐዲስ ኪዳንም ሐዋ18:22 ላይ "ወደ ቂሳርያም በደረሰ ጊዜ ወጥቶ ለቤተክርስቲያን ሰላምታ ከሰጠ ቡሃላ ወደ አንጾኪያ ወረደ " ይላል ። ይህም በሀዲስ ኪዳን ለቤተክርስቲያን መስገድ ወይም ሰላም ለኪ ብሎ መስገድ የተገባ መሆኑን ቅዱስ ጳውሎስ አስተምሮናል ።በመጨረሻም በ1ኛ ነገ. 9:3 " ...በፊቴ የጸለይከውን ጸሎትህንና ልመናህን ሰምቻለሁ ፡ ለዘላለምም ስሜ በዚያ ያድር ዘንድ ይህን የሰራኸውን ቤት ቀድሻለሁ ዓይኖቼና ልቤ በዘመኑ ሁሉ በዚያ ይሆናሉ " ። ብሎ ለሕንፃው ቤተመቅደስ እግዚአብሔር የሰጠውን ይህን ታላቅ ክብር ማስተዋል ይገባል ።

ማዕዶት ዘ ኦርቶዶክስ:(ትንቢተ ሕዝቅኤል ምዕ. 29)----------8፤ ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። እነሆ፥ ሰይፍ አመጣብሃለሁ፥ ሰውንና እንስሳንም ከአንተ ዘንድ አጠፋለሁ። 9፤...
21/06/2020

ማዕዶት ዘ ኦርቶዶክስ:
(ትንቢተ ሕዝቅኤል ምዕ. 29)
----------
8፤ ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። እነሆ፥ ሰይፍ አመጣብሃለሁ፥ ሰውንና እንስሳንም ከአንተ ዘንድ አጠፋለሁ።

9፤ የግብጽም ምድር ባድማና ውድማ ትሆናለች፥ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ፤ አንተ። ወንዙ የእኔ ነው የሠራሁትም እኔ ነኝ ብለሃልና።

10፤ ስለዚህ፥ እነሆ፥ በአንተና በወንዞችህ ላይ ነኝ፥ የግብጽንም ምድር ከሚግዶል ጀምሮ እስከ ሴዌኔና እስከ ኢትዮጵያ ዳርቻ ድረስ ውድማና ባድማ አደርጋታለሁ።

11፤ የሰው እግር አያልፍባትም የእንስሳም ኮቴ አያልፍባትም፥ እስከ አርባ ዓመትም ድረስ ማንም አይኖርባትም።

12፤ ባድማም በሆኑ ምድሮች መካከል የግብጽን ምድር ባድማ አደርጋታለሁ፥ በፈረሱትም ከተሞች መካከል ከተሞችዋ አርባ ዓመደ ፈርሰው ይቀመጣሉ፤ ግብጻውያንንም ወደ አሕዛብ እበትናቸዋለሁ በአገሮችም እዘራቸዋለሁ።

13፤ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ከአርባ ዓመት በኋላ ግብጻውያንን ከተበተኑባቸው አሕዛብ ዘንድ እሰበስባለሁ፤

በ አድስ በለጠ
👈

ማዕዶት ዘ ኦርቶዶክስ:ማዕዶት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ:በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን !ሚካኤል --------በዕብራይስጥ: מִיכָאֵל‎, ሲነበብ፡ ሚካኤልበግሪክ: Μιχ...
19/06/2020

ማዕዶት ዘ ኦርቶዶክስ:
ማዕዶት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ:
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን !

ሚካኤል
--------
በዕብራይስጥ: מִיכָאֵל‎, ሲነበብ፡ ሚካኤል
በግሪክ: Μιχαήλ, ሲነበብ፡ Mikhaḗl;
በላቲን: Michahel-ሲነበብ ሚካኤል;
በአረቢኛ: ميخائيل‎, ሲነበብ፡ ሚካኤል

በክርስትና በአይሁድ በእስልምና እንዲሁም በመላዕክት አማላጅነት በሚያምኑ ሃይማኖቶች የመላዕክት ሁሉ አለቃ ሊቀ መላእክት ተብሎ ይጠራል::

ሚካኤል ማለት በዕብራይስጥ ቋንቋ ሚ-መኑ’ ካ-ከመ’ ኤል- አምላክ ማለት ሲሆን በአንድነት ሲነበብ መኑ ከመ አምላክ (እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው) ማለት ነው፡፡

ይህ ታላቅ መልአክ ዮሐንስ ወንጌላዊ በራዕዩ ‹‹በእግዚአብሔር ፊት የሚቆሙትን ሰባቱን መላእክት አየሁ›› ብሎ ከተናገረላቸው መላእክት ውስጥ የሚመደብ ሲሆን የሰባቱም ሊቃነ መላእክት አለቃ እንዲሆን እግዚአብሔር መርጦ ሹሞታል፡፡ ይህ ታላቅ መልአክ ያደረጋቸው የሠራቸው እጅግ ብዙ የሆኑ ተአምራት አሉት፡፡

•በዛሬውም ዕለት ሰኔ ፲፪ የባሕራንን የሞት ደብዳቤ ወደ ሕይወት የቀየረበት ዕለት በመሆኑ በየዓመቱ በታላቅ ድምቀት ይከበራል::

በተጨማሪም ስለ መላእክት ከመጽሐፍ ቅዱስ ለመረዳት እነዚህን ጥቅሶች ተመልከቱ:-

•መላእክት ሰውን ይረዳሉ -ዘፍ.16፡7/ ዘፍ.18፡15/ ዘጸ.23፡20/ መሳ6፡11/ 1ኛነገ.19፡5/ 2ኛነገ 6፡15/ ዳን.8፡15-19/ ዳን.3፡17/ ት.ዘካ.1፡12/ ማቴ.18፡10/ሉቃ. 1፡26/ ሉቃ.13፡6/ ዩሐ.20፡11/ ሐዋ.12፡6/ ራዕይ 12፡7/

•ለመላእክት ስግደት ይገባቸዋል- ዘፍ.19፡1-2/ ዘኁ.22፡31/ ኢያሱ 5፡12/ መሳ.13፡2/ 1ኛ ዜና 21፡1-7/ ዳን.8፡15

•ዛሬ በተጨማሪም የጻድቁ የቅዱስ ላሊበላ በዓለ ዕረፍት ሲሆን ቅድስት አፎምያም በዛሬው ዕለት ትታወሳለች::

ከበዓሉ ረድኤትና በረከት ያሳትፈን !

ወስብሐት ለእግዚአብሔር !

ማዕዶት ዘ ኦርቶዶክስ:addis belete:በአዲስ አበባ ባለፉት 24ሰአታት በተደረገ ምርመራ 98 ሰዎች ቫይረሱ እንደተገኘባቸው የአዲስ አበባ ከተማ ጤና ቢሮ ገልጿል።‼️እስከዛሬ ድረስ በተደ...
16/06/2020

ማዕዶት ዘ ኦርቶዶክስ:
addis belete:

በአዲስ አበባ ባለፉት 24ሰአታት በተደረገ ምርመራ 98 ሰዎች ቫይረሱ እንደተገኘባቸው የአዲስ አበባ ከተማ ጤና ቢሮ ገልጿል።‼️

እስከዛሬ ድረስ በተደረጉ የላብራቶሪ ምርመራዎች 2577 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል።

-ዛሬ ከተገኙት ውስጥ 3ሰዎች የውጪ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያላቸው ሲሆኑ 5ሰዎች ከበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያላቸው ናቸው። 90ሰዎች ደግሞ የውጪ ሀገር ጉዞ ታሪክ እና ከበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር የታወቀ ግንኙነት የሌላቸው መሆናቸው ተረጋግጧል።

በክፍለ ከተማ ደረጃ አጠቃላይ እና ዛሬ የተያዙ ሰዎችን ቁጥር ስንመለከት

ክፍለ ከተማ አጠቃላይ ዛሬ
1. አዲስ ከተማ ---- 590------37
2. ቦሌ -----411------4
3. ጉለሌ ---- 286-----4
4. ልደታ ---- 265-----13
5. ኮልፌ ቀራኒዮ ---- 243-----8
6.ቂርቆስ ----155-----16
7. አራዳ ----149-----7
8.የካ ----144------2
9. ንፋስ ስልክ ላፍቶ---133 -----4
10.አቃቂ ቃሊቲ ----79 -----2
11.በመጣራት ላይ ያለ-122-----1
⏸ጠቅላላ ድምር -----2577--98

©አዲስአበባ ከተማ ጤና ቢሮ

ግእዝን እንማር0. - አልቦ 1. ፩ አሐዱ 2. ፪ ክልኤቱ 3. ፫ ሠለስቱ 4. ፬ አርባዕቱ 5. ፭ ሐምስቱ 6. ፮ ስድስቱ 7. ፯ ስብዓቱ 8. ፰ ስመንቱ 9. ፱ ተሰዓቱ 10. ፲ አሠርቱ 1...
08/06/2020

ግእዝን እንማር

0. - አልቦ
1. ፩ አሐዱ
2. ፪ ክልኤቱ
3. ፫ ሠለስቱ
4. ፬ አርባዕቱ
5. ፭ ሐምስቱ
6. ፮ ስድስቱ
7. ፯ ስብዓቱ
8. ፰ ስመንቱ
9. ፱ ተሰዓቱ
10. ፲ አሠርቱ
11. ፲፩ አሠርቱ ወአሐዱ
12. ፲፪ አሠርቱ ወክልኤቱ
13. ፲፫ አሠርቱ ወሠለስቱ
14. ፲፬ አሠርቱ ወአርባዕቱ
15. ፲፭ አሠርቱ ወሐምስቱ
16. ፲፮ አሠርቱ ወስድስቱ
17. ፲፯ አሠርቱ ወሰብዓቱ
18. ፲፰ አሠርቱ ወስመንቱ
19. ፲፱ አሠርቱ ወተሰዓቱ
20. ፳ እስራ
21. ፳፩ እስራ ወአሐዱ
22. ፳፪ እስራ ወክልኤቱ
23. ፳፫ እስራ ወሠለስቱ
24. ፳፬ እስራ ወአርባዕቱ
25. ፳፭ እስራ ወሐምስቱ
26. ፳፮ እስራ ወስድስቱ
27. ፳፯ እስራ ወሰብዓቱ
28. ፳፰ እስራ ወሰመንቱ
29. ፳፱ እስራ ወተሰዓቱ
30. ፴ ሠላሳ
31. ፴፩ ሠላሳ ወአሐዱ
32. ፴፪ ሠላሳ ወክልኤቱ
33. ፴፫ ሠላሳ ወሠለስቱ
34. ፴፬ ሠላሳ ወአርባዕቱ
35. ፴፭ ሠላሳ ወሐምስቱ
36. ፴፮ ሠላሳ ወስድስቱ
37. ፴፯ ሠላሳ ወሰብዓቱ
38. ፴፰ ሠላሳ ወሰመንቱ
39. ፴፱ ሠላሳ ወተሰዓቱ
40. ፵ አርብዓ
50. ፶ ሃምሳ
60. ፷ ስድሳ
70. ፸ ሰብዓ
80. ፹ ሰማንያ
90. ፺ ተሰዓ
100. ፻ ምዕት
101. ፻፩ ምዕት ወአሐዱ
102. ፻፪ ምዕት ወክልኤቱ
103. ፻፫ ምዕት ወሠለስቱ
104. ፻፬ ምዕት ወአርባዕቱ
105. ፻፭ መዕት ወሐምስቱ
106. ፻፮ ምዕት ወስድስቱ
107. ፻፯ ምዕት ወሰብዓቱ
108. ፻፰ ምዕት ወስመንቱ
109. ፻፱ ምዕት ወተሰዓቱ
110. ፻፲ ምዕት ወአሠርቱ
111. ፻፲ወ፩ ምዕት አሠርቱ ወአሐዱ
112. ፻፲ወ፪ ምዕት አሠርቱ ወክልኤቱ
113. ፻፲ወ፫ ምዕት አሠርቱ ወሠለስቱ
114. ፻፲ወ፬ ምዕት አሠርቱ ወአርባዕቱ
115. ፻፲ወ፭ ምዕት አሠርቱ ወሐምስቱ
116. ፻፲ወ፮ ምዕት አሠርቱ ወስድስቱ
117. ፻፲ወ፯ ምዕት አሠርቱ ወሰብዓቱ
118. ፻፲ወ፰ ምዕት አሠርቱ ወስመንቱ
119. ፻፲ወ፱ ምዕት አሠርቱ ወተሰዓቱ
120. ፻፳ ምዕት ወእስራ
130. ፻፴ ምዕት ወሠላሳ
140. ፻፵ ምዕት ወአርብዓ
150. ፻፶ ምዕት ወሃምሳ
160. ፻፷ ምዕት ወስድሳ
170. ፻፸ ምዕት ወሰብዓ
180. ፻፹ ምዕት ወሰማንያ
190. ፻፺ ምዕት ወተሰዓ
200. ፪፻ ክልኤቱ ምዕት
201. ፪፻ወ፩ ክልኤቱ ምዕት ወአሐዱ
202. ፪፻ወ፪ ክልኤቱ ምዕት ወክልኤቱ
203. ፪፻ወ፫ ክልኤቱ ምዕት ወሠለስቱ
204. ፪፻ወ፬ ክልኤቱ ምዕት ወአርባዕቱ
205. ፪፻ወ፭ ክልኤቱ ምዕት ወሐምስቱ
206. ፪፻ወ፮ ክልኤቱ ምዕት ወስድስቱ
207. ፪፻ወ፯ ክልኤቱ ምዕት ወሰብዓቱ
208. ፪፻ወ፰ ክለኤቱ ምዕት ወስመንቱ
209. ፪፻ወ፱ ክልኤቱ ምዕት ወተሰዓቱ
210. ፪፻ወ፲ ክልኤቱ ምዕት ወአሠርቱ
211. ፪፻፲ወ፩ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወአሐዱ
212. ፪፻፲ወ፪ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወክልኤቱ
213. ፪፻፲ወ፫ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሠልስቱ
214. ፪፻፲ወ፬ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወአርባቱ
215. ፪፻፲ወ፭ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሐምስቱ
216. ፪፻፲ወ፮ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወስድስቱ
217. ፪፻፲ወ፯ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሰብዓቱ
218. ፪፻፲ወ፰ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሰመንቱ
219. ፪፻፲ወ፱ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወተሰዓቱ
220. ፪፻፳ ክልኤቱ ምዕት ወእስራ
230. ፪፻፴ ክልኤቱ ምሪዕት ወሠላሳ
240. ፪፻፵ ክልኤቱ ምዕት ወአርብዓ
250. ፪፻፶ ክልኤቱ ምዕት ወሃምሳ
260. ፪፻፷ ክልኤቱ ምዕት ወስድሳ
270. ፪፻፸ ክልኤቱ ምዕት ወሰብዓ
280. ፪፻፹ ክልኤቱ ም

30/05/2020

addis Belete
​​👉 ጋዜጠኛ ሰላማዊት ደጀን EBS TV የቅዳሜን ከሰዓት አዘጋጅ በነበረችበት ወቅት በEBS TV ህግ መሰረት ወደ Studio ለቀረጻ ከመግባቷ በፊት አንገቷ ላይ ያለውን መስቀልም ሆነ ማህተብ እንድትፈታ ትደረግ እንደነበር ተናግራለች።

ሰላማዊት ደጀን ከEBS አስቀድሞ ከዓመታት በፊት Ebc/etv Sport ዘጋቢም ነበረች ፥ በዛን ወቅትም እንዲሁ ከአንገት ላይ ማህተብ መፍታት ግዴታ ነበር። ይሄን ጉዳይ ሌሎች ጋዜጠኞችም በተደጋጋሚ እንደቅሬታ የሚያነሱት ተግባር ነው በተለይ በመንግስት ሚዲያዎች።

ይሄ ጉዳይ ምን ታስቦ እንዲህ እየተደረገ እንዳለ ግራ ገብቶኛል። ሙስሊም ሴት አንከሮች ሂጃባቸውን እንደለበሱ ዜና ያነባሉ ቢያነቡም ችግር የለውም፤ አንድ የኦርቶዶክስ ጋዜጠኛ የግድ Studio ለመግባት ከአንገት ላይ መስቀል እንዲወልቅ የሚደረግበት ለምንድነው? ምንስ ታስቦ እንደሆነ ፈጽሞ አልገባኝም።

ሌሎች ሴት ጋዜጠኞች ተራቁተው ጡታቸውን ሳይቀር አጋልጠው እያሳዩ ሚሊየኖች በሚታደሙበት የTv ቻናሎች ላይ ሲቀርቡ ማህበረሰባዊ ና ሞራላዊ ህግና ስነስርዓት እንደተጣሰ ተቆጥሮ እርምጃ ሊወሰድ ሲገባ ሃይማኖታዊ መብትን በሚጋፋ መልኩ ከአንገት ላይ መስቀል እንዲበጥሱ ማድረግ ግን በተጻፈ ህግ ሳይቀር ፕሮግራም አስፈጻሚዎችና ዳይሬክተሮች የእለት ተዕለት ክትትል የሚያደርጉበት ተግባር ሆኖ ሲታይ የሆነ ነገር እንዳለ መረዳት አይከብድም።

ጉዳዩ ሃይማኖታዊ መለያዎችን የጋራ በሆኑ ሚዲያዎች ላይ መታየት የለበትም ከሆነ ይሄ ህግ ሁሉም የሃይማኖት ተከታዮች ላይ በእኩል ሁኔታ ስለምን አንተገበርም? ለአንዷ ሂጃብ ለብሶ መዘገብ ሲፈቀድ ለሌላዋ ከአንገቷ ላይ መስቀል እንድት በጥስ ማድረግ ምን ማለት ነው?

ሌላው ያለን ሃይማኖተኛ ህዝብ ነው ለምንድነው ህዝቡን የሚመስል ሁሉም በራሱ መለያና ማንነት ሆኖ እንዲቀርብ የማይደረገው? ያሌለን ማንነት መዋስ ለምን ያስፈልጋል።

❗️ይሄ ተግባር በመንግስትም በግልም ሚዲያዎች በተደጋጋሚ እየተፈጸመ እንዳለ ይሰማል። በቀደመው ጊዜ ሀገሪኛ ፊልሞችና ሲሰሩ እንዲሁ ተዋኖያን ከአንገታቸው ላይ መስቀላቸውን እንዲፈቱ ለማድረግ ተሞክሮ በአርቲስቶቹ ትግል እንዲቀር ሆኗል፤ ።

ተከታታይ ዓመታት የዘለቀውንና ጋዜጠኞች ላይ እየተደረገ ያለውን ማህተም የማስፈታት ተግባር ለማስቆም መደረግ ያለበት ሁሉ ሊደረግ ይገባል። ከቤተክርስቲያናችን የላይኛው አካል ጀመሮ ትኩረት ተስጥቶት እስከ ምዕመን ድረስ እየተደረገ ያለውን ሊያውቅ ይገባል።

#ሼር

24/05/2020

share

Mehreteab assefa "አዋጅ አዋጅ"   share
13/05/2020

Mehreteab assefa "አዋጅ አዋጅ" share

Ethiopian Orthodox Tewahedo Song By memeher meheretab assefa "Awaj Awaj" © Mahtot Tube is the only Channel that has exclusive rights for all Lyrics produced ...

መልካም የጥምቀት በዓል
20/01/2020

መልካም የጥምቀት በዓል

merry christmas
07/01/2020

merry christmas

Address

Dessie
1234

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Belete Fan posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share