16/09/2025
” የመፍትሔወን መንገድ ውስንነት ለማረምና ዘገምተኛውን ገብ ለማፍጠን የሚችል ቀመር ሆኖ መጥቷል፡፡ ከመደመር ዕሳቤ የሚቀዳው የመደመርመንግሥት ኢትዮጵያዊ የፖለቲካዊ ኢኮኖሚ ዕሳቤ ነው፡፡ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ማረጋገጥ የሚቻለው ትብብርን ያስቀደመ ሥርዓት በመዘርጋትና ፖሊሲዎቾን ገበር ነበብ በሆነ መንገድ አውጥቶ በቅንጅት በመተግበር ነው ብሎ ያምናል።
በዚህ የለውጥ ጊዜ ውጥናችንን ለማሳካት የሄድንበትን መንገድ ቃኝተናል፡፡ ከፍተቶችንና ጥንካሬዎችን ለይተናል፡፡ ከፍተቶቹን አሻጋሪ በሆነ መልኩ የሚቀርፍ፤ ጥንካሬዎችን በተሻለ ሁኔታ የሚያስቀጥል፤ አዲስ ዕሳቤና አዲስ መንገድን ቀምረናል። መደመር ሀገር ከገባቾበት ችግር በማላቀቅ ወደ ትከከለኛው የለውጥ ምሕዋር የሚመራ ዕሳቤ ነው። የመደመርመንግሥት፣ ሀገራዊ ጸጋዎቻችንን በማቀናጀትና በማስተባበር ረገድ ካለው ሚና ባልተናነሰ፤ በፍጥነት የምንጓዝበትንም መንገድ የቀመረ አስተሳሰብ ነው፡፡
የመደመር መንግሥት ነገን የተሻለ ለማድረግ የትናንት፣ የዛሬና የነገ ተደራራቢ ኃላፊነቶቻችንን በአስቸኳይ እንድንወጣ ያደርጋል፡፡ እንዲሁም ተለዋዋጭ በሆነው የዓለም ሁኔታ ውስጥ ጥንካሬያችንን ለማረጋገጥና ከግባችን ለመድረስ እንድንፈጥን ያስችላል። የመደመር መንግሥት ፍጥነትና ፈጠራን መሠረት ያደረገ ዕሳቤ ነው። የዚህ መጽሐፍም ዋነኛ ጭብጥ ይህንን የፍጥነትና የፈጠራ ፍኖት ማብራራት ነው፡፡
ከመጸሐፉ የተወሰደ
PM Dr. Abiy Ahmed Ali