Jimma Coffee Quality inispection and Certification Center

Jimma Coffee Quality inispection and Certification Center This page help Coffee exporting farmers and exporters at large

08/10/2025
08/10/2025

የኢትዮጵያ ቡና በዓለም አቀፍ ገበያ ተፈላጊና ተመራጭ ነው-የውጭ ዜጎችና ዳያስፖራዎች

ዲላ፤መስከረም 27/2018
የኢትዮጵያ ቡና ተፈጥሯዊ ጣዕሙ የተለየ በመሆኑ በዓለም አቀፍ ገበያ ተፈላጊነቱና ተመራጭነቱ ከፍተኛ መሆኑን የውጭ ዜጎችና ዳያስፖራዎች ገለጹ።

የቡናን ተፈጥሯዊ ጣዕም በመጠበቅና እሴት ጨምሮ ለውጭ ገበያ በማቅረብ ተፈላጊነትንና ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝም ተመላክቷል።

የውጭና የሀገር ውስጥ ባለሃብቶች በተገኙበት የጌዴኦ ዞን የኢኮኖሚ እድገት ፎረም መካሄዱ የሚታወስ ነው።

በፎረሙ ላይ የተሳተፉ የውጭ ዜጎችና ዳያስፖራዎች የኢትዮጵያ ቡና ተፈጥሯዊ ጣዕሙ የተለየ በመሆኑ በዓለም አቀፍ ገበያ ተፈላጊነትና ተመራጭነቱ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

ከፎረሙ ተሳታፊዎች መካከል ከአሜሪካ የመጡት ዊልያም ኢሲሚዝ ለኢዜአ እንደገለጹት የኢትዮጵያ ቡና ተፈጥሯዊ ጣዕሙ የተለየ ነው።

በዓለም አቀፍ ገበያ ጭምር ተፈላጊና ተመራጭነቱ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው፥በሚኖሩበት አሜሪካ የኢትዮጵያና የኮሎንቢያ ቡናን በስፋት እንደሚጠቀሙ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያን ቡና ከመጠጣት ባለፈ እዚህ መጥተው የቡና ልማቱን በአካል በመመልከታቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል።

በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ልዩ ጣዕም ቡና የኢትዮጵያ ቡና የተለየ ለመሆኑ ጥሩ ማሳያ ነው ያሉት ዊልያም ኢሲሚዝ፣ የኢትዮጵያን የቡና አቅም ለዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ በአግባቡ ማስተዋወቅ ከተቻለ የተሻለ ገበያ መፍጠር ይቻላል ብለዋል።

በቀጣይ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት በግብርና ዘርፎች በተለይ በቡና ልማት ለመሰማራት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያን ልዩ ጣዕም ቡና እሴት ጨምሮ ለውጭ ገበያ ማቅረብ አዋጭ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በአሜሪካ መርክ የመድሃኒት ድርጅት መሪ ሳይንቲስትና የጌዴኦ ዲያስፖራ ማህበር ሰብሳቢ ሄኖክ ታደሰ (ዶ/ር) ናቸው።

ማህበሩ በጌዴኦ ዞን በቡና፣ በእንሰት ተረፈ ምርትና በቱሪዝም ዘርፎች ያሉ እምቅ የኢንቨስትመንት አቅሞችን ለመጠቀም በአግሮ ኢንዱስትሪ ዘርፎች እየተሳተፈ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

በቀጣይ የኢንቨስትመንት ተሳትፎውን በማጠናከር ተጠቃሚ ለመሆን እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።

ሬማ የቡና ቀማሾች ማህበር ሰብሳቢ አቶ አቤነዘር ሙሉጌታ በበኩላቸው፥ ቡናን ተፈጥሯዊ ጣዕም ጠብቆና እሴት ጨምሮ ለውጭ ገበያ በማቅረብ ተፈላጊነቱንና ተወዳዳሪነቱን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የተቆላ፣የተፈጨና በፈሳሽ መልክ የተዘጋጁ ከ600 ኪሎ ግራም በላይ እሴት የተጨመረበት ቡና ለተመረጡ የውጭ ገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ይህም የኢትዮጵያን ቡና ተፈጥሯዊ ጣዕም ጠብቆ በማቅረብ ሀገርን ከማስተዋወቅ ባለፈ የውጭ ገዥዎች የመግዛት ፍላጎታቸው እንዲጨምርና ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ ማድረጉን አስረድተዋል።

በዞኑ እሴት በሚጨምሩ የኢንቨስትመን ዘርፎች የግሉን ባለሃብት ተሳትፎ ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን ያነሱት ደግሞ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ናቸው።

በተለይ ዞኑ በቡና፣ በእንሰት ልማትና ተረፈ ምርት እንዲሁም በቱሪዝምና ማዕድን ያሉትን ጸጋዎች ከኢንዱስትሪው ጋር ለማስተሳሰር የግሉን ባለሀብትና የዳያስፖራውን እውቀት፣ ልምድና ካፒታል ለመጠቀም እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

በዚህም ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ በተደረገ ጥረት ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 150 አልሚዎች ወደ ሥራ ገብትዋል ብለዋል።

በተያዘው ዓመት ይህንን ለማጠናከር የመሬት አቅርቦት ሥራ በማጠናቀቅ አልሚዎችን እየጠበቁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደርና ሥራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ በክልሉ ክህሎት መር ስራና የቁጠባ ባህል እንዲዳብር የተደረገው ጥረት የኢንቨስትመንት አቅምን እያሳደገ ነው።

በቀጣይ ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ በአግሮ ኢንዱስትሪ ዘርፎች የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቱን ተሳትፎ ለማጠናከር መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

ምንጫችን ኢዜአ ነው።

19/08/2025

Celebrating my 9th year on Facebook. Thank you for your continuing support. I could never have made it without you. 🙏🤗🎉

09/07/2025

Address

Jimma

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
17:30 - 18:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00

Telephone

+251912157060

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Jimma Coffee Quality inispection and Certification Center posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Jimma Coffee Quality inispection and Certification Center:

Share