30/08/2026
#እውነተኛ ዋስትና
የኑሮ ውድነት፣ ውዝፍ እዳዎች እና ስለነገ እርግጠኛ አለመሆን ሁልጊዜ ወደ አእምሯችን የሚያመጣው አንድ የሐሰት መልእክት አለ፦ “አይበቃችሁም፣ ያንሳችኋል፣ አትሻገሩትም!” የሚል። የሚያኖረን ስራችን ብቻ እንደሆነና ምንጫችን ጉልበታችን እንዲሁም እውቀታችን እንደሆነ ሊያሳምነን ይዳዳዋል።
ነገር ግን የሁሉ ነገር ባለቤት የሆነው ፈጣሪ የሚነግረን እውነት ይለያል፦
“ብሩም የእኔ ነው፤ ወርቁም የእኔ ነው፤ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር!” ሐጌ 2:8
የሕይወታችን ዋስትና የሚለካው ባከማቸነው ንብረት መጠን ሳይሆን፣ ማለቂያ የሌለው ሀብት ባለው ፈጣሪ አምላካችን አቅርቦት ላይ ነው!
💡 5ቱ ወርቃማ መመሪያዎች፡
1. በእጥረት ጊዜ ➔ መታመናችንንና ተስፋችንን በእግዚአብሔር ላይ እናድርግ!
2. ሲያትረፈርፈን ➔ትህትና እንላበስ!
3. መንገዶች ሲዘጉ ➔በጸሎት እንትጋ!
4. በረከት ሲፈስ ➔ ምስጋናችንን ሙሉ በሙሉ ለእርሱ እንስጥ!
5. ለሌሎች ስናካፍል ➔ ያለ ስግብግብነት በቅን ልብ እንስጥ!
እነዚህ ከላይ የጠከስኳቸው ሁኔታዎች በሁሉም ሰው ሕይወት ውስጥ አቀሬ ናቸው። ወቅታቸውን ጠብቀው እየተፈራረቁ እስከ እለተ ሞቱ ድረስ ይከሰታሉ።
ቁሳቁስን ከማሳደድ ይልቅ የሀብት ሁሉ ምንጭ የሆነውን እግዚአብሔርን እንከተል! የተሰጠንን በጥበብ እያስተዳደርን፣ በታማኝነት እንሥራ። ሁኔታዎች ቢቀያየሩም እግዚአብሔር ሁሌም ታማኝ ነው!
“እንግዲህ፦ ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፤ ... ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና። ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።”
ማቴዎስ 6:31-33
መልካም ሰንበት ይሁንላችሁ💐❤️🙏
SundayInspiration GodsPromises